Friday, November 16, 2012

የፌድራል ፖሊሶች ህፃን በናትዋ ጀርባ ላይ እንዳለች በዱላ መተው መግደላቸው ተዘገበ by GPS » Today, 04:51 ህዳር ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም



ኢሳት ዜና:- በሀና ማሪያም አካባቢ መንግስት የሚያደርገውን መኖሪያ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ አስፈፃሚ የሆኑ የፌድራል ፖሊሶች ህፃን በናትዋ ጀርባ ላይ እንዳለች በዱላ መተው መግደላቸው ተዘገበ።

ከ30.000 ሺህ በላይ አባ ወራ በተፈናቀለበት የንፋስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 መኖሪያ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ ትላንት በናትዋ ጀርባ እንዳለች በፌድራል ፖሊስ ተመታ ከሞተችው ህፃን ጋር የሞቱት ቁጥር አራት ደርሰዋል።

መጠለያም ሆነ ተለዋጭ ቤት ሳያገኙ ቤታቸውን ከነንብረታቸው በግሬደር እየተደረመሰ ያለው የወረዳ 01 ነዋሪዎች ለብርድና ለሀሩር ከመዳረጋችን አልፎ በፌድራል ፖሊሶች የሚደርስባቸው ድብደባ ፣ እስራትና ግድያ ባስቸኮይ እንዲቆምላቸው ጥሪ አድርገዋል ።

በፌድራል ፖሊስ ወደ ተገደለችው ህፃን መጠለያ ለቅሶ ለመድረስ እንኮን አልተፈቀደልንም ያሉ ነዋሪዎች መንግስት የበደል በደል እየፈፀመብን ነው ሲሉ ምሬታቸውን ገልፀዋል።

በንፋስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ከሳምንት በላይ በዘለቀው ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ ከ30 ሺህ በላይ ቤቶች ፈርሰው ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሜዳ ላይ ወድቀው እንደሚገኙ ካአካባቢው ሰዎች የሚደርሰን መረጃ ያመለክታል።

በዚህ የማፍረስ ዘመቻ ቤተክርስቲያንና መስኪድ ሳይቀር መፍረሳቸውንም መዘገባችን ይታወሳል።

No comments:

Post a Comment