Thursday, February 28, 2013

የሕወሐት ፍጥጫ ቀጥሏል « አሁን ያለው ሕወሐት ቆዳ ነው » እነ ስብሃት « የሕወሐት ወራሾች እኛ ነን » እነ አባይና አዜብ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

 

ሁለት ቦታ የተከፈለው የሕወሐት አመራር ልዩነቱን በማስፋት እየተወዛገበ መሆኑን ከመቀሌ ታማኝ ምንጮች ገለፁ። ስብሃት እና አዜብ የሚመሩት ሁለቱ ቡድን አነጋጋሪ አቋም ይዞ መውጣቱን ምንጮቹ ጠቁመዋል። በስብሃት ነጋ የሚመራው ቡድን ባስቀመጠው አቋም « መለስ ሕወሐትን ገድሎ ነው የሔደው! አሁን ያለው ሕወሐት ቆዳ ነው። ጥያቄው ግልፅ ነው፤ ሕወሐት መቀጠል አለበት.. ወይስ የለበትም?» ሲሉ በድርጅቱ ቀጣይ ሕልውና ላይ ጥያቄ አሳርፈዋል። ከዚህ በተቃራኒ የቆመውና አባይ ወልዱ፣ አዜብና ከጀርባ በረከት ስምኦን ያሉበት ቡድን በበኩሉ « የሕወሐት ወራሾች እኛ ነን፤» ሲል ለነስብሃት ምላሽ መስጠቱ ታውቋል። በተጨማሪ በሁለቱም ቡድኖች በልዩነት ነጥብ ተደርጎ የተወሰደው በ1993ዓ.ም ከፓርቲው የተባረሩት አመራሮች « ይመለሱ» ፣ « አይመለሱም» የሚለው እንደሚገኝበት ተጠቁሟል። የሁለቱም ጐራ ፖለቲካዊ ግብ አንዱ ሌላኛውን ገፍትሮ ከሜዳው ማስወጣትና ፓርቲውን ብሎም አገሪቱን በፈላጭ ቆራጭነት ለመቆጣጠር ያለመ እንደሆነ አንድ የፓርቲው ቅርብ ሰው ጠቁመዋል።
በፓርቲው በተለኮሰው ስር የሰደደ ፖለቲካዊ ፍጥጫ ካድሬው ለሁለት ተከፍሎ ሲነታረክ መሰንበቱን ምንጮች ጠቁመዋል። በፓርቲው አባላት « አደገኛ» የተባለውን ይህን ፍጥጫ መሰረት በማድረግ በቴውድሮስ አድሃኖምና ብርሃነ ገ/ክርስቶስ የሚመራ ቡድን ራሱን « የአስታራቂ ሽማግሌዎች ቡድን» በሚል ሰይሞ ባለፉት ቀናት ሲነቀሳቀስ መቆየቱን ገልፀዋል። ሆኖም ሁለቱን ጎራዎች አቀራርቦ ለማነጋገርና ለማስማማት የተጀመረው ጥረት በሁለቱም በኩል በሚታየው አክራሪ አቋም ምክንያት ተስፋ ሰጪ ሁኔታ እንደማይታይ ምንጮቹ አስታውቀዋል። አሁንም ድርድሩ መቀጠሉን ምንጮቹ አልሸሸጉም።
የሕወሐት ሕልውና አጣብቂኝ ውስጥ በገባበት በአሁኑ ወቅት በሌላ ጐራ የተነሱ ወጣት የፓርቲው ካድሬዎች ባነሱት ጥያቄ ፥ ሁሉም አንጋፋ አመራሮች ከድርጅቱ እንዲለቁ ጥያቄ ማቅረባቸውንና ይህን ለማድረግ ፈቃደኛ ካልሆኑ ግን ሕወሐት ሊፈርስ እንደሚችል ማስጠንቀቂያ ጭምር መስጠታቸውን ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።
በተያያዘም « ጉባኤ ይጠራ» በሚል በካድሬዎች የቀረበውን ጥሪ እነ አባይ ወልዱና አዜብ ያሉበት ቡድን ውድቅ እንዳደረገው ታውቋል። አባይና አዜብ የሚመሩት እንዲሁም ትርፉ ኪዳነማሪያም፣ ሃድሽ ዘነበ፣ አለም ገ/ዋህድ፣ በየነ ምክሩ፣ ተክለወይኒ አሰፋና ሳሞራ የኑስ የተካተቱበት ቡድን በጉባኤው አሸናፊ ሆነው እንደማይወጡ ከወዲሁ በማመናቸውና በነስብሃት በኩል ከፍተኛ ሃይል እንደተደራጀባቸው ጠንቅቀው ስለተረዱ ነው ሲሉ የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም ሳሞራ በመከላከያ እጣ ፈንታቸው ተመሳሳይ መሆኑን በማመናቸው ከነአዜብ ጋር ተሰልፈው እንደሚገኙ ገልፀዋል።
የበላይነትን እየያዘ ነው የሚባለውና በስብሃት የተደራጀው እንዲሁም በደብረፂዮን የሚመራው ቡድን አብዛኛውን የማ/ኮሚቴ አመራር በዙሪያው ያሰባሰበ ሲሆን ከነዚህም፥ አዲስአለም ባሌማ፣ አርከበ እቁባይ፣ ቅዱሳን ነጋ፣ ፈትለወርቅ፣ ፀጋዬ በርሄ፣ አባዲ ዘሙ፣ ሃ/ኪሮስ ገሰሰ፣ ተ/ብርሃን…በዋንኛነት እንደሚገኙበት ምንጮቹ አመልክተዋል። የሽማግሌው ቡድን ስብስባ እንደቀጠለ ተጠቁሞዋል።
staff reporter | February 28, 2013 at 1:07 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1u3

Wednesday, February 27, 2013

አንድ አስተያየት፤ ህውሀት ተኮር | አቤ ቶኪቻው

Gudu Kassa
ሞት ይርሳኝ እና የህውሃት ወዳጆቼን እንኳን ለየካቲት 11 አደረሳችሁ ሳልላቸው የካቲት 21 ሊሆን አይደል እንዴ!? በሉ አሁንም የካቲት ራሱ ሳይወጣ “እንኳ አብፃኩም” ልበል። እኔ የምለው ይሄ ስንተኛ አመት ነው ማለት ነው… በዛ ሰሞን ስታትስቲክስ መስሪያ ቤት ስሰራ አንድ አባት ዕድሜያቸውን ስጠይቃቸው…” አይ ልጄ የእኔ እድሜ ሩቅ ነው… ቢጠሩትም አይሰማ!” እንዳሉኝ አይነት ህውሀትም እድሜው በጣም እየራቀ ሄዷል። በዚህ ቢጠሩት በማይሰማ ሩቅ ዕድሜ ምን ያህል ስራ እና ምን ያህል ሴራ እንዳከናወነ ግምገማው ይቁጠረው።

በበኩሌ የህውሃትን እምቢ ባይነት እና ታጋይነት አደንቃለሁ። አንድ ማህበረሰብ ጭቆና አለብኝ ብሎ ካመነ፤ እና ተዉኝ አትጨቁኑኝ ቢል የሚሰማው ካጣ “ዘራፍ” ብሎ ማምረሩ የአባት ነው። ችግሩ አትጨቁኑኝ ብሎ ዘራፍ ያለው መልሶ ጨቋኝ ሲሆን ነው እንጂ!
ይህው ዛሬም የደርግ ስርአት ህውሃትን እንደፈጠረው ሁሉ፤ የኢህአዴግ/ ደርግ ስርአት ደግሞ፤ አርበኞች ግንባርን፣ ኦነግን፣ ኦብነግን፣ ደህሚትን እና የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ሀይልን ፈጥሯል። ሁሉም በየ አቅጣጫው ነፍጥ አንግበው “ና በለው… ና!” እያሉ ከግዙፉ የኢህአዴግ ሰራዊት ጋር እየተፋለሙ እንደሆነ በተለያየ ግዜ እየሰማን ነው።
ባለፈው ጊዜ በአዲስ አበባ የመከላከያ ቀን ተብሎ ሲቀወጥ የመንግስት ባለስልጣኖች የሀገር ውስጡም የውጪውም ነፍጠኛ ለመመከት የሚያስችል አቅም እንዳላቸው ሲያሳዩን ነበር። ይሄንኑ ነገር ደርግ ሲያደርገው ነበር። አምባገነኖች መኮራረጅ በጣም እንደሚያስደስታቸው የሚያውቁት ይሄኔ ነው። ኢህአዴግ ደርግን ስታብጠለጥል ላያት እርሱ የነካውን የምትነካ በሄደበት መንገድ የማትራመድ ትመስላለች ግን ልክ ደርግ የሚያደርገውን ስታደርግ ሲመለከቱ አምባገነኖች ለመኮራረጅ የሚጨክን አንጀት እንደሌላቸው ይረዳሉ።
ታድያ ዛሬም ርስ በርሳችን ልንታኮስ ማዶ ለማዶ ተፋጠናል። ህውሀት አርባ አመት ሊሞላት ሁለት አመት ብቻ ቀርቷታል። በእውነቱ ቢያንስ የእርስ በርስ ጦርነትን ታሪክ ማድረግ ከተሳናት ህውሀት አርባ አመቷን ከምታከብር አርባዋ ቢወጣ ይሻላታል።
ለማንኛውም በዚህ አጋጣሚ አንድ አስተያየት እሰጣለሁ። … ህውሃት ብቻ ሳትሆን በጥቅሉ ኢህአዴግ ራሷ ዝም ብላ ዕድሜዋን እና አበሳችንን ከምታስቆጥረን እርሷ የመጣችብትን መንገድ ዳግም እንዳይኖር ብትተጋ ለሁላችንም ጥሩ ነው!
እኔ የምለው ወዳጆቼ… ሰላም ናችሁ ወይ! የኔ ነገር ሰላምም አላልኳችሁኮ!
ይመቻችሁ!
 
staff reporter | February 27, 2013 at 7:28 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1tJ
 


Comment

Monday, February 25, 2013

የቡዳዎቹ ሠፈር የትኛው ነው? ወልደማርም ዘገዬ

Gudu  Kassa
የቀድሞው ኢትዮጵያዊ የአሁኑ ኤርትራዊ ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን መድኃኔ “ኤርትራ እንደ እናት አገር፤ ችግሮችና ፈተናዎች ትናንትም ዛሬም” በሚል ርዕስ በአውሮጳውያኑ የዘመን አቆጣጠር ጥር ወር 2013 የጻፉትን ጥናታዊ ዘገባ በፍላሼ አሰንብቼ ዛሬ ጧት ቁርሴን  አወራረድኩበት፡፡ ኤርትራ ለእርሳቸው የምታስጨንቀውን ያህል ኢትዮጵያም - ባለቤት ያጣችዋ ከርታታዋ ኢትዮጵያም ለእኔ እንደእናት ሀገር ታስጨንቀኛለችና የተሰማኝን ልናገር ብዕሬን አነሳሁ፡፡

ግን በዚህች የተረገመች ሀገር - በዚህ የዜጎች መብት ክፉኛ በሚረገጥባት ሀገር የመብራት መጥፋት በየደቂቃው ስለሚከሰት በምፈልገው ፍጥነት መጨረሴን እጠራጠራለሁ፡፡ አንዳንዴ በቀን ለቁጥር ለሚያታክት ጊዜ ያህል መብራት ይቆራረጣል፤ አሁን ድርግም ይልና ከደቂቃዎች በኋላ ሊመጣ ይችላል፤ የምትሠራውን ቅጥ ያሳጣብሃል - በልጆቼ አነጋገር ‹ሙድህን ይሠርቅብህ›ና ልትሳነፍ ባስ ሲልም ልትጽፍ ያሰብከውን ከነጭራሹ ልትተወው ትችላለህ፡፡ ለምሳሌ በኛ መንደር በቀደም ዕለት የጠፋ ከ27 ሰዓታት በኋላ ትናንት ማታ ነው መብራት የመጣልን፡፡ ስልኩም ውኃውም እንደዚሁ ነው፡፡ የቤት ስልክ ከሚሠራበት ጊዜ የማይሠራበት ይበልጣል፡፡ የአንዱን ሊጠግኑ ሲመጡ የሌላውን አበላሽተው ሊሄዱ ይችላሉ - ጠርተሃቸው በመቁሽሽ እንድታሠራቸው፡፡ ውኃ ወር እስከወርም ላታገኝ የምትችልባቸው አጋጣሚዎች አሉ፡፡ ማንን ትጠይቃለህ? በየቢሮው አናት ‹የዚህና የዚህ የሥራ ሂደት ባለቤት› የሚል ጽሑፍ ተለጥፎ ብታይም ማንም ጉዳይህን ከቁብ የሚጥፍልህና የሚያነጋግርህ ሰው የለም፡፡ ስቃይ ነው ልጄ፡፡ የዴሞክራሲው ነገር እዬዬም ሲዳላ ነውና አታስበውም፡፡ አሁን በአንጻራዊነት ከሚታዩ መልካም ነገሮች ውስጥ ዋናው የመንገዶች መስፋፋት ነው፡፡ ይህም ቢሆን በየቀኑ በመቶዎችና በሺዎች ከሚጨምረው የተሸከርካሪዎችና የእግረኞች ብዛት ጋር በጭራሽ ሊጣጣም ባለመቻሉ ችግሮች ሲወሳሰቡ እንጂ ሲፈቱ አታይም፤ የሕዝቡን ብዛት በየሥፍራው እንደጉንዳን ሲርመሰመስ ስታይ ሰው ነገር ዓለሙን እርግፍ አድርጎ ትቶ ከመፈላፈል ውጪ ሌላ ሥራ ያለው ላይመስልህ ይችላል፤ የሀገሪቱ ዋና ራስ ምታት የራሴ ነው የምትለው ለሀገርና ለወገን የሚቆረቆር፣ ሁሉንም እኩል በሚያሣትፍ የዕቅድና የበጀት ምደባ ሀገሪቱን በተገቢው የዕድገት ጎዳና የሚያራምድ ተቆርቋሪ መንግሥት ማጣት ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ቁጥር በአደገኛ ሁኔታ መጨመርም ነው - እኔ ራሴ ባለቤቴ ዘጠንኛውን ልጃችንን ልትገላገል ጥቂት ሣምንታት ይቀሯታል፤ ይህን የምናደርገው ተስፋ ከመቁረጥና በነሱ ለመጦር ከማቀድ አንጻር ነው - ሌላ መዝናኛም ከማጣት ጭምር(እንዴ! ምን ማለታችሁ ነው - እስከግማሽዋ በአረፋ የተሞላች አንዲት ብርጭቆ ድራፍት እንኳን ባቅሟ በሰባት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከብር 2.20 ሽቅብ ተወንጭፋ አሥር ብር ስትገባ! - ታዲያ መራባት ይነሰን?)፡፡ ሰው ተስፋ ሲቆርጥ ከ‹መብላት› እና ‹መጠጣት› ውጪ ያሉትን አብዛኞቹን የ‹መ›ሕጎች ያከብራል፡- መናደድ፣መበሳጨት፣መሰደድ፣መጠጣት፣መዋለድ፣መእንትን…፤ “ጠጪነትና የሕዝብ ብዛት በአስደንጋጭ ሁኔታ መጨመር የተስፋ መቁረጥ ምልክቶች ናቸው” የሚባለው አዲስ ምሳሌያዊ አባባል ለካንስ እውነት ነው! ምን ልበልህ ወንድሜ! የሀገርህ ነገር እጅግ አሳሳቢ ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሁለተኛና ሰባተኛ ዜጋ ሆነህ ከመኖር አውሮፓ ውስጥ ውሻና ድመት ሆነህ ብትፈጠር በእጅጉ ይሻልሃል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የወያኔ ተለማማጭ ሀብታም ከምትሆን የጓንታናሞ የፍርድ እሥረኛ ብትሆን ላንተ ሉተሪ ነው፡፡ ብሬቪክ የሚባለው ሰባ ምናምን ሰው የገደለው ስዊድናዊ ታራሚ ከእሥር ስወጣም ገና ብዙ ሕዝብ እፈጃለሁ እያለ መስፈራርቾውን በቀጠለበት ወቅት ‹ክፍሌ በሰዓቱ አልጸዳልኝም› ወይም ‹ክፍሌ በቂ ብርሃን ስለሌለው በአስቸኳይ ይለወጥልኝ!› በሚል የማያዳግም ቃል (‘ultimatum’) የማረሚያ ቤቱን ባለሥልጣናት እያሽቆጠቆጠ መብቱን በሕግ ማስጠበቁን ስትሰማ ከጫካ የመጣ ወሮበላ እንደፈለገው የሚደፈጥጥብህን የአንተን ኢትዮጵያዊነት ያሻው ቀቅሎ እንዲበላው ከአእምሮህ መንትገህ ለመጣል ልትዳዳ ትችላለህ፡፡ ጊዜው የፈተና ነው ወንድሜ፡፡ እናም ይህችን ጊዜ እንደምንም ታገላትና ሳትበለሻሽ ተወጣት፡፡ ታሪክ እንደሆን ይቅርታ ማድረግን አያውቅም፡፡ ጽጌረዳን በቀላል አናገኝም፤ እሾኋ ውድነቷን ሳይጨምርላት አልቀረም፡፡ ኢትዮጵያዊነት ሲሞቅ በማንኪያ ሲቀዘቅዝ በእጅ አይደለም፡፡ ዛሬ በስሟ የነገዱና ሕዝቧን የዶጋ ዐመድ ያደረጉ ዱርዬ ልጆቿ ሁሉ አይቀጡ ቅጣት ሲያገኙ ዳፋው እንዳይደርስህ ተጠንቀቅ! ለአንድ እንጀራ ብለህ እንደዔሣው ብኩርናህን ለሆድህ አትሽጥ፡፡ የሰው ወርቅ አያደምቅምና የጠፋህ ወገኔ በጊዜ ተመለስ!!
አንተ ዴሞክራሲ ዴሞክራሲ እያልክ በየሰው ሀገር አደባባይ ትጮሃለህ፡፡ እዚህ ሰዎች ከሰውነት ተራ እየወጡ ተንቀሳቃሽ በድን እየሆኑልህ ነው፡፡ ያንተን ጩኸት ራሱ አይሰሙም - ብዙዎቹ የሚሰሙበት ፍላጎትና መንገድም የላቸውም፤ደንበኛ ሰሜን ኮሪያውያን ሆነንልሃል፡፡ ‹ወንድሞቼንና እህቶቼን ነጻ አወጣለሁ› ብለህ ብትመጣ እንኳን፣ ነጻነት የሚገባው(የሚያስፈልገው) መሆኑን የሚዳ ዜጋ ለማግኘት ይቸግርሃል፤ የሚመጣውን ቁጣና መቅሰፍት ሁሉ በቀላሉ እየተለማመደ ለሁሉም የግፍ አገዛዝ ተንበርካኪ ትውልድ እየተበራከተ ነው፡፡ ግዴለህም አንዳች የተደገመብን ነገር መኖር አለበት፡፡ ፈዘንና ደንግዘን በመተታዊ የአንደርብ ሥራ ወደ ጋንነትና እንሥራነት የተለወጥን ግዑዛን ነገሮች መስለንልሃል ወንድምዬ፡፡
አንድ ለአንድ አካባቢ እንግዳ የነበረ ሰው መንገድ ይጠፋውና አንዱን መንገደኛ ይጠየቀዋል፡፡ “የኔ ወንድም እንደዚህ የሚባል መንደር ልሄድ ፈልጌ ነበር፡፡ እስኪ እንዴት እንደምደርስ ጠቁመኝ ወዳጄ”  ያም ሰው “ ይሄን መንገድ ቀጥ ብለህ ትሄድና እመስቀልኛው መንገድ እዚያ ወዲያ ስትደርስ ግራህን ይዘህ ትታጠፋለህ፤ ከዚያም ጥቂት እንደሄድክ ግራና ቀኝ የሚገኙ ሠፈሮችን ታገኛለህ፡፡ አንደኛው ግን የቡዳዎች ሠፈር ስለሆነ ሰው ጠይቅና ተጠንቅቀህ እለፍ፡፡” ይለዋል፡፡ እዚያ ጠንቀኛ መስቀልኛ መንገድ ላይ ሲደርስ ቀድሞ የተነገረውን ያስብና በቡዳነት ይታማ ከነበረው ሠፈር የመጣ አንድ ሰው እዚያ አካባቢ ስለነበር በየዋህነት “ አንቱ ጋሼ - የቡዳው ሠፈር የትኛው ነው?” ብሎ ይጠይቃል፡፡ ያም ሰው ምንተፍረቱን “እኛም እነሱን እንላለን፤ እነሱም እኛን ይላሉ” ይለውና ወዶ እንዲገባብት ምርጫውን ለጠያቂው ትቶ ንዴቱ እንዳይታወቅበት ለማድረግ በመጣር ይለየዋል፡፡ “እነሱም እኛን ይላሉ፤ እኛም እነሱን እንላለን!”
‹ኤርትራውያን› የኛ የ‹ኢትዮጵያውያን› ችግሮች መባቀያ እንደሆኑ የምናምን ወገኖች ጥቂቶች አይደንለም፡፡ በተገላቢጦሹም እኛ የነሱ ችግሮች ምንጭ እንደሆንን የሚያምኑ ኤርትራውያን አሉ፡፡ የሁለታችንም ችግሮች አንድ መሆናቸውን ግን እያጤንን መጥተናል - ለዐይን ይበጃል ያሉት ኩልም ዐይንን ሊያጠፋ መቃረቡን እየተረዳን ነው - ‹ናጽነት› ወይ ‹ባርነት›፤ ዕድሜ ደጉ የነጻነትንም የባርነትንም አዲስ ፍቺዎች እየተገነዘብን ነው፡፡ በዕንቆቅልሾች ታጥረናል ማለት ይቻላል፡፡ ለቅጣት በተላኩ ሁለት የአክስትና የአጎት ልጆች ጦስ 100 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ እየታመሰና የቁም ስቅሉን እያዬ ነው፡፡ ‹ዘይገርም ሻሸመኔ ትብስ ኮፈኔ› ይላሉ ወንድሞቼ የሚደንቅ ነገር ሲገጥማቸው፡፡
ከአንድ ምንጭ የሚቀዳ ውኃ ጣዕሙ አንድ ነው፡፡ መለስና ኢሳይያስ - የአንድ ሣጥናኤል ሁለት ገጽታዎች - ከአንድ የጥፋት ወንዝ የተቀዱ በመሆናቸው በሃሊዮ በገቢር ተመሳሳይ ናቸው፡፡  የበሰበሰና የገማ የገለማ ዓላማቸው ኢትዮጵያን ማፈራረስ ሕዝብንም ከሕዝብ ማቃቃርና ማፋጀት በውጤቱም የራሳቸውን ሰይጣናዊ ተልእኮ ማሣካት ስለሆነ እነዚህ ሁለት የሥጋ ዝምድናና የዓላማ ቁርኝት ያላቸው ሰዎች በሁሉም ነገር አንድ ናቸው፡፡ የተረገሙና ከእግዚአብሄር መንገድ የወጡ - ለቅጣት የመጡ እንደመሆናቸው መጨረሻቸው ቀርቶ መነሻቸውና መገባደጃቸው ራሱ የሚያምር አልሆነም፡፡ መለስ በ‹ለጋነት› ዕድሜው ሊቀጭ የቻለው በሕዝብ ፍቅር ምክንያት እንዳልሆነ እንኳን ፈጣሪ ሰይጣን ካቦኣቸውም(Foreman) ያውቃል፡፡ በቀላል ትዝብት መለስ ትዳርና ልጅ ሊወጣለት ያልቻለው በሕዝብ እርግማንና በሕዝብ ዕንባ ምክንያት እንጂ የመልካም ሥራ ተፈጥሮ ኖሮት ያንን ደግነቱን ፈጣሪ ዋጋ አሳጥቶበት እንዳልሆነ አሁንም እንኳንስ እግዚአብሔር ዲያብሎስ ራሱም ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ኢሳይያስ አፈወርቂ እንደጎረምሳ ትዳሩን እያመናቀረና ባለቤቱ በሽማግሌዎች ብርታት እየለዘበች እሱ የመጠጥና የቁማር ሱሰኛ ሆኖ የቀረው፣ የረባ ግለሰብኣዊና ማኅበራዊ ሕይወት ሳይመራ ዕድሜውን በከንቱ እየጨረሰ ያለው፣ የበሽታና የጋንጩሮች ዋሻ ሆኖ እንዳበደ ውሻ እየተቅበዘበዘ የሚኖረው በሕዝብ እርግማን እንጂ በጽድቅ ሥራው ምክንያት አይደለም(ልብ አድርጉ! አማሮችን ለተዋጊዎቹ የዒላማ ማለማመጃ እያደረገ የነበረ የሉሲፈር ቀኝ እጅ ነው! To be honest, I was not there in any form of presence, but I can assume as if I were there; my instinct tells me that he and his protégé, His Crookedness Meles Zenawi, have been doing every crime that men can do against the so called Amharas! And it is my sincere conviction that their karmatic uncleanliness will never let them go without punishment, possibly here or probably there, or maybe in both realms until the time they become as immaculate as a newborn sinless babe!)፡፡ የእንጨት ሽበቶቹ ስብሃት ነጋ፣ ሞራ-ራስ የኑስ፤ ሥዩም መስፍን … በልዩ ልዩ ሱሶችና የበሽታ መርዞች ተለክፈው ባብዛኛው እንደነሱው ሰካራምና ሀሺሻም በስተቀር እዚህ ግባ የሚሉት አንድም ቁም ነገረኛ ልጅ ሳይወጣላቸው ዕድሜያቸውን በመንዘላዘል እንዲሁ በከንቱ  እየጨረሱ የሚገኙት በእርግማን እንጂ በምርቃት በረከት አይደለም - ጎበዝ በደንብ እንደማመጥ! የእርግማን ጦር ሲወጋ እንጂ ሲወረወር አይታይም የሚባለውን ነባር ሥነ ቃል አንርሣ! ከጥንትም ቢሆን ሕዝብ ያለቀሰበት መቅኖ  የለውም - በተለይ በኢትዮጵያ፡፡ ለዚህም ነው አሁን ማንም በማንም ላይ እንትኑን እንትን ይበል በሂደት ግን ‹በሠፈረው ቁና ይሠፈርለታል› በሚለው  ነባር መለኮታዊና ተፈጥሯዊ ሕግ መጽናት የሚገባ መሆኑን በጥብቅ የምሰብከው፡፡ የቻለ እንዲያውም በክፉዎች አይቅና - ብድራታቸውን ያገኛሉና፡፡ ክፉዎች ለጊዜው የተሳካላቸው ቢመስልም የማታ ማታ ተጎጂዎች ናቸው፡፡ ሁለት ስህተቶች አንድን የተበላሸ ነገር ሊያስተካክሉ ወይ ሊያቃኑ እንደማይችሉም መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ስህተት ስህተትን ይወልዳል እንጂ የተዛነፈን አያቃናም፡፡ (Two wrongs don’t make a right.) ለዚህም ነው ወያኔን ሳይወለድ እንደጨነገፈ ሽል መቁጠር የሚገባን፡፡ ግርፋቱ ግን ከባድ ነው!
እውነት መስሎ የታየኝን እናገራለሁ፤ እጽፍማለሁ፡፡ በእንትን የተጥለቀለቀ የንግግር ዘይቤያችንን የምጥሰው ሆን ብዬ ነው፡፡ ጥንቃቄ ማድረግ ያለብን መጥፎ ድርጊት ላለማድረግ እንጂ ቋንቋ በማሳመር እውነትን ለመሸፈን መሆን የለበትም፡፡ ባለፈው ሰሞን የላክሁትን አንድ ጽሑፍ አንብቦ አንድ ወዳጄ በስልክ እንዲህ አለኝ፡፡ “አንተ ወልዴ! ምን ነካህ? አበድክ እንዴ? እንዴት በስሜት ውስጥ ሆነህ ትጽፋለህ? ለምን ቀዝቀዝ ስትል አትጽፍም? ተናደህ ከጻፍክ እኮ ሰው ይቀየምሃል፤ተናደን የምንቀጣው ልጅ ሊጎዳብን እንደሚችል አታውቅምን? የምትለው ነገር እውነትነት ቢኖረው እንኳን በቃላት መረጣ ተጠምዶ አንዱ የሌላኛውን ስሜት ላለማጎፍነን እርስ በርስ ሲሞከሻሽ በኖረ ማኅበረሰብ ውስጥ ይህን ያህል ግልጽነት ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ድረ ገጽ ያን ጽሑፍህን ለጥፎት ሲያበቃ ከሁለት ቀናት በኋላ ከውጪ ዐዋቂ ይሁን ከውስጥ ዐዋቂ አስተያየት  በመነሳት ገንጥሎ ጣለው፤ አንድ ቦታ ደግሞ ስሜታቸውን እንዴት እንደነካህባቸው ባልገባኝ ሁኔታ መርቅነህ እንደጻፍከው አስተያየት የጻፉብህ አሉ፤ ለምን …” ሲለኝ ብልጭ አለብኝና “ኦ!ኦ! የኔ ወንድም ዝም ብለው ካዳመጡህ ብዙ ትቀባጥራለህ፤ አንተ ራስህም የፈለግኸውን ልትለኝ ትችላለህ፡፡ የፈለጋችሁትን በሉ ሃሳቡ አይበላኝም፡፡ እኔ ካልተናደድኩ አልጽፍም፡፡ ስናደድ የምጽፈው ለእኔ እውነትነት አለው፡፡ ያልተበረዘና ያልተከለሰ - እከሌን ላስቀይም ወይም ላስደስት የማልልበት እንደወረደ ዓይነት ሃሳብ የማገኘው ተናድጄ ስጽፍ ነው፡፡ አንባቢም ያሻውን የማለት መብት አለው፡፡ የሚዲያ መድረኮችም ሲፈልጉ ይለጥፉ ሳይፈልጉ ቀድደው ይጣሉት - በኔ የቁጣ ንግግር ሰማይና ምድር አያልፉም፡፡ ሰለጠነ በሚባለው ዓለም የአሜሪካ ሴኔትና ኮንግረስ፣ የእንግሊዝ ፓርላማ፣ የእስራኤል ክነሴት፣ የራሽያ ዱማ… በስብሰባዎቻቸው ‹f**k off, idiot, son of a bitch, …› እየተባባሉ ተሰዳድበው ሲያበቁ ከስብሰባው ሲወጡ ሁሉንም ረስተው አብረው ይጫወቱ፣ ይበሉና ይጠጡስ የለምን? እኔስ ምን አጠፋሁ? ‹የትግሬ ወያኔ እንትን አለብን፤ እነእንትና ከፈለጉ እንትን ይሁኑ፤ እንትኔ መጥቶብኝ ወደ እንትን ቤት ልሄድ ነው፣እንትንህ ተከፍቷልና እንትንህ ሳይታይብህ እንትንህን ዝጋ…› እያልኩ ሁሉን ነገር በግድ በእንትን ጀምሬ በእንትን መጨረስ አለብኝ? ለምን? ከፈለግህ አንተም እንደነእንትና መሆን ትችላለህ፣ የእንትን አቀንቃኝ ሁላ! ለካንስ አፈሩን ገለባ ያድርግለትና ስብሃት ገ/እግዚአብሔር ‹እንትን›ን እንደጠላና ስም አይጠሬዎችን(taboo words) እነእንትንንና እንትንን በቁልምጫ ሳይቀር እንደጠራ የሞተው ማፈንገጥ አምሮት ሳይሆን እውነትን እንዳለች መግለጽ ፈልጎ ኖሯል?” አልኩና በንዴት ፎግልቼ ስልኩን ጆሮው ላይ ጠረቀምሁበት፤ የታባቱንና፡፡ ነገር ግን የራሽያው ዱማ በቦሪስ የልሲን የደረሰበት የመድፍና የታንክ እሩምታ ትዝ አለኝና ከጠቀስኩለት ዝርዝር ውስጥ እንዲያወጣልኝ ሳልነግረው ስልኩን በመዝጋቴ ቆጨኝ፡፡ ራሺያና እኛ ለካንስ በአንዳንድ ነገሮች እንመሳሰላለን፡፡ ፑቲን - መድቬዴቭ፤ መለስ - ደሳለኝ፡፡ አይይይ፣ የኛዎቹ ቲያትር እንኳን የነዚያኞቹን ያህል ወዝ ያለው አይደለም፡፡ በምን ተገናኝቶ ልጄ!
እንትን ስል አንድ እንትን ትዝ አለኝ ይልቁናስ - ፈገግ በሉ እንጂ - ግንባርን አኮሳትሮ እስከመቼ ይዘለቃል፡፡ በአንድ መንደር ውስጥ ኃይለኛ ርሀብ ይገባል አሉ፡፡ ከመንደሩ አባውራዎች አንዱ ውሻውን ይዞ አንዳች የሚታደን ነገር ባገኝ ይልና በቅርብ ወደሚገኝ ጫካ ይሄዳል  - ወደ ደደቢት በረሃ፡፡ ጉድጓድ ይቆፍርና ወጥመዱን አዘጋጅቶ ቢጠብቅ ቢጠብቅ ወደ ወጥመዱ ዝር የሚል ሰስና ሚዳቋ ይጠፋል፡፡ ከዚያ እግሩን አፍታትቶ ለመመለስ ከሄደበት ዘወርወር ብሎ ሲመጣ ያጠመደው ጉድጓድ ውስጥ አንድ አውሬ ገብቶ ያገኛል፡፡ ይሄኔ በመደሰትና ዘመኑ የችግር በመሆኑ ግዳዩን ሌላ ሰው እንዳይካፈለው በመሥጋት በኮድ የታሰረ መልእክቱን ለሚስቱ እንዲህ ሲል ጮክ ብሎ ያስተላልፋል፡-
እንትናችን ውስጥ እንትን ገብቶበት፤
እንትን አምጭልኝ እንትን እልበት፤
አንቺም ነይልኝ እንትን ትይልኝ፡፡
ነገሩ ቢላዎ ይዘሽልኝ ነይ ነው፡፡ ሁሉም አልፎ ፣ የቀኒቱ ርሀብም ለጊዜው ጠፍታ ጧት ላይ ቆዳና ጭንቅላት ሲታይ በጨለማ የተበላችው ለካንስ ቡችዬ ናት፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ነው እንግዲህ ‹ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን› የሚል ሥነ ቃላዊ ብሂል በቋንቋችን የተዘነቀውና አሁን ድረስ እየተጠቀምንበት የምንገኘው ይባላል፡፡
ለማንኛውም አካፋን አካፋ ማለት ጥሩ ነው፡፡ በመሠረቱ ኢትዮጵያ ሳይጠጡ የሚሰክሩባት፣ ሳይቅሙ የሚመረቅኑባት፣ ጠብ ከመነሳቱ አቧራ የሚጨስባት፣ በጠብ ያለሽ በዳቦ የስድብ ውርጅብኝና የአግቦ ውሽንፍር አየሩ የሚሞላባት የለየላቸው አማኑኤሎች ሀገር እየሆነች በመምጣቷ ብዙ ነገሮች ሊያስገሩሙን አይገባም፡፡ አምባጓሮ በሽበሽ ነው፡፡ መነቃቀፍ የሠርክ ልማድ ነው፡፡ ሌብነትና ውሸት፣ ሙስናና ንቅዘት አያስነውሩም፡፡ የሚያሾምና የሚያስሞግስ ተግማምቶ መገኘት እንጂ የኅሊናና የሞራል ንጽኅናን መጠበቅ አይደለም - ንጽሕና እንዲያውም ሊያስቀጣና ሊያደኸይ ቤተሙከራ ውስጥ በተፈለሰፈ ወንጀል አስከስሶም በዕድሜ ይፍታህ ዘብጥያ ሊያወርድ ይችላል - ሁሉን ቢያወሩት ሆድ ባዶ መቅረቱ ከፋ እንጂ በዚህ ረገድ ስንትና ስንት የምነግራችሁ ነበረኝ! እናም ወደተነሳሁበት ስመለስ… የወያኔዎች የከረፋ ተፈጥሮና በሀገርና በሕዝብ ላይ የሚፈጽሙት ሰይጣናዊ ድርጊት እያናደደኝ እውነትን ባለማለሳለስ እንዳለ እጽፋለሁ እንጂ በምንም ዓይነት ሰው ሰራሽም ሆነ የተፈጥሮ ንጥረ ነገር ተመርቼ አልጽፍም፡፡ በሀብት ብዛትና ኅሊናን በሚያዛቡ የአልኮል መጠጦች እየሠከሩ እንደዕንቁላል የገማ አስተሳሰባቸውን በጉልበት በተቆጣጠሩት ሚዲያ አማካኝት ሕዝብ ላይ የሚያስታውኩና የሚቀረሹ ስብሃትን የመሰሉ ዘረኞች ሞልተውናል፡፡ “አሜሪካ ቀርቶ መንግሥተ ሰማይም ብትሆን አታመልጠንም! አምጥተን እናስርሃለን” የሚሉ ልበ ድፍን የወያኔ ሰካራሞችና ቅዠታሞች እያሉ እኔ እውነትን ለመጻፍ ጫትም ሆነ መጠጥ አያስፈልገኝም፡፡ እንደውነቱ ከሆነ ውቅያኖሶች ቀለም፣ ሰማይና ምድር ብራና ሆነው የወያኔን ታሪክ ብንጽፍ አያልቅም፡፡
ከዚህ በላይ  እስካሁን ምን እንዳልኩ አላውቅም - የምርቃና ነገር - ቂ…ቂ…ቂ… ሣቅ አምሮኝ ነበር እንደጉድ ተንከተከትኩላችሁ፡፡ ቢሆንም ትርጉም ሰጠም አልሰጠም ነገሬን መቋጨት አለብኝና ወደዚያው ወደሚወስደኝ ጎዳና ላዝግም፡፡ ኤርትራውያን ችግር ላይ እንደሚገኙ ከፕሮፌሰሩ ጽሑፍ በኛና በነሱ የነገሮች ግጥምጥሞሽና ምስስሎሽ እያዘንኩ ተረድቻለሁ፡፡ የኛም የነሱም ችግር አንድ ነው ማለት ነው፡፡ እኛ፣ ኤርትራውያኑ እነበረከትና ስብሃት ገደሉን እንላለን፤ ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን ደግሞ ‹ትግራውያኑ› እነስብሃትና በረከት እነሱን ኤርትራውኑን ገደሉን እያሉን ነው፡፡ ማን ማንን መግደሉ ለጊዜው ለውጥ አያመጣም - ትኩረት ሊሰጠውና ሊቆምም የሚገባው ግድያው ነው፡፡ ይህን የተቀናበረ ታሪካዊ የሀገርና የሕዝብ ግድያና ጭፍጨፋ ማን ነው የሚያቆመው? እነዚህ ታሪካዊ የጋራ ጠላቶቻችን ቅጥረኞች(mercenaries) ምን እስኪያደርጉን ነው የምንጠብቀው? በኛ ስም እየማሉና እየተገዘቱ እስከመቼ ነው ግድያቸውን የሚቀጥሉት? ዐይጥ በበላ እስከመቼ ነው ዳዋ እየተጨፈጨፈ የሚዘልቀው? እንደኔ እንደኔ ሥጋዊ ሞት ከመንፈሳዊ ሞት በጣም ተመራጭ ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ ታላላቅ ሰዎች የሚፈሩት ሞትን ሳይሆን አሟሟትን ነው፡፡ ነገሩ ‹ከሞቴ አሟሟቴ ያስፈራኛል› እንደሚባለው ነው፡፡ የፕሮፌሰሩ አባባል እውነት ከሆነ የሞተችው ኢትዮጵያና ሕዝቧ ብቻ ሳይሆኑ ሳትወድ በግዷ የተለየቻት ልጇ ኤርትራም ናት ማለት ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡
በእኔ እምነት እናትና ልጅ እንደተለያዩ አይቀሩም - በግሌ ያን ጊዜ ልደርስበት ወይ ላልደርስበት እችል ይሆናል - ግን ላምና ጥጃ በርግጥ ይገናኛሉ! ይህን ስል - ማለትም ‹እደርስበት ወይ አልደርስበት ይሆናል› ብዬ በኩራት ስናገር የስድስተኛውን ስሜቴን ‹ትንቢት› ለመግለጽ ያህል እንጂ የአንድ ትንኝ ወደ አንድ ታሪካዊ ኹነት(An historic event which really is inevitable!) መድረስ ወይ ያለመድረስ ጉዳይ አሳስቦኝ አይደለም፡፡ ስትፈልጉ ቅዠት ወይም ቅብዥር በሉት ኢትዮጵያና ልጇ ኤርትራ በአዲስ መልክ ይዋሃዳሉ፡፡ የተበለሻሹ ነገሮች ተቃንተው ይስተካከላሉ፡፡ ይህ የሚሆነው ግን ቂም በቀልና ጥላቻ፣ ዘረኝነትና ጎጠኝነት ተወግደው ሰው እንደውሻ ደምና አጥንት እያነፈነፈ ሳይሆን በሰውነቱ ብቻ ሲሳሳብና ሁሉም ዜጎች በአንድ የወል ሀገራዊ ስሜት ሲተሳሰሩ ነው - የመለስ-ኢሳይያስ የትግራይ ትግሪኝ ዘፈን ቅኝት ወረቱን በመጨረስ ከስሞ የኢትዮጵያዊነት ሥልት ሲናኝ፡፡ ይህን የተቀደሰ ትውልዳዊ ኃላፊነት በብቃት የሚወጡ ዜጎች በቅርብ ይሾማሉ፡፡ በቤተ ሙከራ ተሠርተው እንደዕርዳታ ስንዴ ለየጎጡ የተከፋፈሉ ባንዲራዎች ይቃጠላሉ፤ የዚህ መሠሪ ተንኮል ጠንሳሾች፣ አስጠንሳሾችና አራማጆችም በገሃድ መሞት እንደጀመሩ አንድ ባንድ ግን ሁሉም ተራቸውን ጠብቀው ያልቃሉ፤ በሰማይም በምድርም ተረግመዋልና - በደም ባህር የሚዋኙ ናቸውና - በሕዝብ የምሬት ዕንባ ዶፍም በስብሰዋልና ዘር አይወጣላቸውም፤ ለነሱ የተፈቀደችዋ ዘመን ይህቺ የአሁኗ ጊዜ ብቻ ናት - ባለቻቸው ጊዜ ይደሰቱ፤ ይጠጡ፤ አንዳቸው በሌላኛቸው ቤት ይሸራሞጡ፤ አንዳቸው የሌላኛቸውን ልጅ ያሳድጉ - ከእርጉማን የሚጠበቅ የልክስክስነት ባሕርይ ነውና፤ ዳንኪራና ጮቤም ይርገጡ (የዐዋጁን በጆሮ ባትሉኝ እነዚህ የታሪክ ጉዶች እኮ አልጋንም የሚጋሩና ‹የተቀደሰውን ለውሾች አውጥተው የሚጥሉ› ጋጠወጦች ናቸው! አንዳችም ማሠሪያና የሚፈሩት ነገር የሌላቸው ከሃይማኖትም ከባህልም ማዕቀፎች የወጡ ስዶች እኮ ናቸው!)፡፡ ታዲያን እነሱ ሰይጣንን ይዘው ይህን ያህል ተዓምር የሠሩ እኛ እግዚአብሔርን ይዘን ከነሱ የበለጠ ልዩ ተዓምር እንዴት አንሠራ!? “እመን እንጂ አትፍራ!” መባሉም ለዚህ ነው፡፡ አይዞን ምዕመናን!!
ነጻነትን እንደቀድሞው የሙሤ ዘመን በኅብስተ መና መልክ ከሰማይ መጠበቅ ግን የዋህነት መሆኑን እንረዳ፡፡ ፈረንጆች “There is no free lunch!” ይላሉ፡፡ ምን ማድረግ እንደሚገባንና እንደሚቻለንም እናስብ፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ግን ከክፋት ሥራ ተጠብቀን ወደፈጣሪ መዞር እንደሚገባን እንወቅ፡፡ ፈጣሪን ግማሽ መንገድ ድረስ ሄድን እንቀበለው፡፡ የሞተን ለመርዳት የሚተጋ ሰማያዊም ሆነ ምድራዊ ኃይል እንደሌለ እንገንዘብ፡፡ እናም ሕይወት እንዳለን፣ እንዳልሞትን፣ ለዲያብሎስ መንጋ እንዳልተንበረከክን የምናሳውቅበት የመነሳሳት ቅጽበት እንዲፈጠር እንትጋ፡፡ ያ ጊዜ ደግሞ አሁንና ዛሬ ነው፡፡ የኛን የቤት ሥራ ከሠራን ቀሪው ቀላል ነው፡፡ ለመሆኑ አሁን ፈጣሪ ምን እየሠራ እንደሆነ እናውቃለን? አዎ፣ ሁሉንም ባናውቅም ይህችን ያህል የምናውቅ ግን አለን፡- ‹ቁናውን እየሰፋ ነው› ወይም ‹ሰፍቶ ጨርሷል›፡፡ መሥፈር ሲጀምርስ? እሱን አያድርስ!ሦርያን ያየ፣ ሊቢያን ያዬ፣ የመንን ያዬ፣ ሩዋንዳን ያዬ፣ማሊን ያዬ፣ቱኒዚያን ያዬ… በእሳት ሊጫወት ማሰብ የለበትም፡፡ ግን ግን ‹የዱባ ጥጋብ ካለስንቅ ያዘምታል› መባሉ ለካንስ እውነት ነው? ውድ ወያኔዎች - መጥፊያችሁ ደርሷል! መጥፋታችሁ እንጂ እንዴት እንደምትጠፉ ግን እኛም እናንተም አናውቅም - ከፈጣሪ በስተቀር፡፡
በመሠረቱ ገዢዎች ይሳሳታሉ፡፡ እንዲያውም የማይሳሳት ገዢ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ በዚህች ምድር ፅድቅን ስለማንጠብቅ ለምሳሌ ባገራችን የመንግሥትን ሥልጣን የሚይይዘው ከበደም ይሁን ሐጎስ ወይም ዘበርጋም ይሁን ሂርጳሳ በአንጻራዊነት እገሌ ከእገሌ በዚህ ወይ በዚያ ጉዳይ ይሻላል ማለት እንችል እንደሆን እንጂ በአስተዳደር ረገድ ፍጹም እንከን የለሽ የመንግሥት አካል አናገኝም፡፡ ከዚህ አንጻር የአሁኑን የወያኔ አገዛዝ ካለፉትም ሆነ ወደፊት ይመጣሉ ብለን ከምንጠብቃቸው ጋር ስናወዳድረው በጥፋት ተልዕኮው ወደር የማይገኝለት መሆኑን መገንዘብ አያዳግተንም፡፡ ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን - የውጭ ሀገር ሰው በመሆናቸው ፕሮፌሰር መድኃኔ ልበልና ባባታቸው ስም ልጥራቸውና - ፕሮፌሰር መድኃኔ በጥናታቸው እንደጠቆሙት የአንድ ሀገር አመራር ትልቁ የሞራል ዝቅጠት በሚያስተዳድረው ሕዝብ መሀል ግርድና አመሳሶ እያወጣ ራሱንም ወደ አንድ ሸጥና ጎጥ እየወተፈ ሌሎችን በወርቅነትና በኩበትነት እየፈረጀ ሲያንጓልል ነው፡፡ ይህ በታሪካችን ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ መቅሰፍት - በምንም መንገድ ሊሽር የማይችል ጠባሳ መሆኑ ሳይረሳ - ምን ያህል መሪዎቻችንን ከስብዕና በታች እያወረደና በመዘዙም እኛን ከመኖር ወዳለመኖር እየለወጠን እንደሚገኝ ከተረዳን ቆይተናል፡፡ ከሞላ ጎደል ሁሉንም የሀገሪቱን የመንግሥት ሥልጣን በቀጥታና በተዛዋሪ ከያዘ የአንድ ሀገር የፖለቲካ አመራር ቡድን ውስጥ 3.6% ብቻ ኢትዮጵያን እንደእናት ሀገር የሚቀበል ሆኖ ሲገኝ ሌላውና 96.4% የሚሆነው በትግራይ እናት-ሀገርነት ሲጸና ከዚህ በላይ ማፈሪያ የታሪክ አንጓ የለም - በጭራሽ! ትግራይ ውስጥ በናሙናነት ከተወሰደ የሕዝብ ክፍል መሀል 82.1% የሚሆነው ‹ቀንደኛ ጠላትህ ማን ነው?› ተብሎ ሲጠየቅ ‹አማራ ነው› ካለ አስታራቂ የሚያስፈልገው ግን ቀን ሊሰጠው የማይገባ ችግር አለ ማለት ነውና ሀገር ሰላም ብለን መተኛት የለብንም፡፡ እነዚህን ዘግናኝ መረጃዎች በዝርዝር ለማንበብና በሃዘን ለመቆራመድ የፈለገ ሰው የተጠቀሰውን የፕሮፌሰሩን ጽሑፍ ማንበብ ነው፡፡ የአጻጻፍ ሥልታችንና የይዘታችን ድምፀት (style and tone) ይለያይ እንጂ እኔን መሰሎች ዘባራቂ የብዕር ‹ጦረኞች›ም የምንለው ይሄንኑ ነው፡፡ ችግር አለ! (‹ነገ እዚህ አካባቢ ቤት ይቃጠላል!› ነበር ያለችው የደሴዋ ዕብድ ሴት በማግሥቱ ራሷ ልታጋየውና ጉድ ልትሠራቸው?) ችግሩ ታዲያ እንደሌሎች ሀገሮች ችግር ሳይወሳሰብና ጥርስ ወደሌለው የተቃቃሩት መንግሥታት(DN/Disunited Nations) መሮጥ ሳይመጣ ከአሁኑ እንፍታው ነው እያልን ያለነው፡፡ ሦርያ ላይ የሚጮህ ጅራፍ ጊዜውን ጠብቆ ኢትዮጵያ ውስጥ አይጮህም ብሎ ማሰብ የለየለት ድንቁርናና ትዕቢት ነው፡፡ ትብታብም ይፈርሳል፤ ፍርሀትም ይጠፋል እያልን ነው የምንገኝ፡፡ አሁን ዓለምን የገዙ የመሰላቸው የትግሬ ወያኔዎች በሕዝብ ላይ መፈንጠዛቸውንና ጥሬ እንትናቸውን በጭቁኑ ወልደማርያም ላይ መጣላቸውን ትተው ወደኅሊናቸው ይመለሱ ማለት ኃጢኣት አይደለም፤ ትርፍ እንጂ ኪሣራም የለውም፡፡ ችግሩስ ቁስልን እየሸፋፈኑ ይብስ እንዲነፈርቅ ማድረግ ነው፡፡ በጭቁን ዜጎች ላይ ፋንድያን ማለትም እንትንን እዬጣሉ ለስንት ዘመን መኖር እንደሚቻል የጋዳፊንና የኢዳሚንን የሙት መንፈስ በጠንቋዮቻቸው አማካይነት ያስጠይቁና ከጥጋብ መንገድ በአፋጣኝ ይውጡ ነው እያልን ያለነው፡፡ በተረቱ ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ መባሉ የጥጋብን መዘዝ ለማጠየቅ ነው፡፡ ሰከርክም ልባል መረቀንህ - አሁንም እደግመዋለሁ፡- እነዚህ ዋልጌ የዲያብሎስ ውላጆች ባስከተሉት መዘዝ ኢትዮጵያ በ‹ጥቂት› ትግሬዎች እጅ ገብታ በወለድ አገድ እየተመጠመጠች ናትና ይህ ታሪክ ይቅር ሊለው የሚከብደው አሰቃቂ ድርጊት ተጨማሪ ጥፋት ሳያስከትል በአስቸኳይ ይቁም፤ ብሔራዊ ዕርቅ ይፈጠር፤ ፖለቲካችን ሰው ሰው ይሽተት፤ በዘረኝነት ከርፍቷል፤ በጎጠኝነት ገምቷል፤ በሙስና ጠንብቷል - የኢትዮጵያ ሃይማኖታዊና ፖለቲካዊ መጥፎ ጠረን የዚህችን ዓለም አድማሳዊ ድንበር አልፎ ጽርሐ አርያምን እያጥነገነገ ነውና በቶሎ መፍትሔ ካልተፈለገለት ጦስ ጥንቡሱ ከኢትዮጵያ ድንበሮችም ይሻገራል እያልን የምንገኝበት ሁኔታ ተፈጥሯል የሚል ግንዛቤ ወስደናል እያልን ነው - በበረከት ስምዖን አማርኛ፡፡ ለዚህ ሁሉ ችግራችን ዋናው መፍትሔ ‹አማራ ገዳይ! ትግሬ ገዳይ!...› የሚለው የጅሎች ፉከራና ሽለላ ሳይሆን መደማመጥና መግባባት ብቻ ነው፡፡ ይሄኛው የሃያና ሠላሳ ዓመት አበቅቴ ለነዚህ ቢሆን ያኛው የሠላሣና ዐርባ ዓመት አበቅቴ ደግሞ ለነዚያኞቹ ይሆናል፤ የዚህች ምድር ነገር የጽዋ ማኅበር ዓይነት ነው - ማንም የማንንም ዝክር ቀፈቱ እስኪያብጥ ሰልቅጦ ሰልቅጦ ሲያበቃ በ‹ጨዋታው ፈረሰ - ዳቦው ተገመሰ› የልጆች ጨዋታ የበላ የጠጣትን ሳይከፍል ከማኅበሩ ልሰናበት ሊል አይችልም - በየትኛው ሒሳብ! ዛሬ ለተቀናጀ መንግሥታዊ የበቀል ጥማት ማርኪያ የሆነ ሕዝብ በቀል አርግዞ በተራው በዳዮቹን ለመቅጣት ምቹ ቀንን የሚጠብቅ እንዳይሆን የክፋት ምንጭን እናድርቅ እያልን ነው - አንዳንድ “የሩቅ ተመልካቾች”፡፡ ማሰብ በተሳናቸው የትግሬ ወያኔዎች፣ ይሉኝታንና ሀፍረትን ሸጠው በበሉ ወንድምና እህቶቻችን እያየነው ያለነው አበሳ የሰቆቃችን የመጨረሻ ምዕራፍ ይሁንና ከዚህ መጥፎ ታሪክ ትምህርት ቀስመን የወደፊቱን ትውልድ ከመርዘኛ ፖለቲካና ፖለቲካው ካበሰበሰው አጠቃላይ ማኅበረሰብኣዊ ቀውስ ነጻ እናውጣው፡፡ በሎሚ ተራ ተራ ዜጎች ለማያባራ ስቃይ መዳረግ የለባቸውም፡፡ መለስ በስብሶ የሞተው፣ ኢሳይያስ ለያዥ ለገራዥ አስቸግሮ ሞትን በሚያስመርጥ የቁም መቅበዝበዝ ላይ የሚገኘው አላንዳች ብልሃት አይደለምና ዜጎች ወደጤናማ ኅሊናቸው ባፋጣኝ ይመለሱ - ቢያንስ ከነዚህ ሁለት የጠፉ ዜጎች እንማር፡፡ በሀገር ዕርቅ ይውረድ፡፡ ቂም በቀል ይወገድ፡፡ የጠገበ ይስከን፤ የተራቡና የተጨቆኑ ወገኖቹንም ያስብ፤ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባም ሆነች አሥመራ(I can imagine,) የሎጥን የሶዶምና ገሞራ የእሳት ዝናብ የሚጠሩ የሲዖል ከተሞች ሆነዋል ብንል አልተሳሳትንም - ብዙኃን በርሀብ አለንጋ እየተገረፉ ጥቂቶች በሚመዘብሩት የሕዝብና የሀገር ሀብት ይሠሩትን አጥተው በነውረኝነት ጎዳና መትመምን መርጠዋል…እኛም እነሱም አናሳዝንም? - በሬ ካራጁ ጋር ይውላል፡፡ ቂም በቀል ቂም በቀልን   ይወልዳል፡፡ አመፅ አመፅን ይወልዳል፡፡ ፍቅርና መተሳሰብ ግን የበቀል ቁርሾን አስወግዶ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመሠረት ያደርጋል፡፡ ዛሬ አንድ የሚፏልል ጥጋበኛ የወያኔ ካድሬ በቢሊዮን የሚገመት ሀብትና ንብረት ቢያከማች - እመኑኝ - አይበላውም፤ መቼምና የትምም አይጠቀምበትም፡፡ ‹እባካችን› ልብ እንግዛ፡፡ እርግጥ ነው ሀብታምና ፖለቲከኛ በአብዛኛው ደናቁርት ስለሆኑ ዛሬን እንጂ ነገን ማሰብ አይቻላቸውም  - ለማሰብ የሚጠቀሙበት ሆዳቸውን እንጂ ጭንቅላታቸውን አይደለም፡፡ አንጎላቸው የተቃኘው በሶስት ነገሮች ብቻ ነው፤ እነሱም ሥልጣን፣ ገንዘብና ወሲብ ናቸው - አንቀሳቃሽ ሞተሮቻቸው እነዚህ ናቸው፤ የእነዚህን ፍላጎቶቻቸውን ጥሪ ለመመለስ ሲሉ ከሰማይ በታች ከምድር በላይ የማይሠሩት ወንጀልና ኃጢያት የለም፡፡ በእነዚህ ሦስት ፈታኝ ነገሮች ያልታወረ ሰው ግን ብፁዕ ነው - አእምሮውንም በአግባቡ ይጠቀማል፤ ከቅሌትና ውርደትም ይድናል፡፡ አቅሉን ስቶ ለነዚህ ነገሮች የሚንበረከክ  ከሰውነት ተራ ይወጣል - በመጨረሻው መጨረሻ ላይ ታዲያ ውድ ዋጋ ይከፍላል፡፡
በተረፈ ትግሬ፣ አማራ ፣ ኦሮሞ የምንለው ነገር የቋንቋ ፈሊጥ እንጂ ተጨባጭ የሆነ አመክንዮኣዊ ልዩነት የላቸውም፡፡ በነዚህ የጎሣና የብሔር ስሞች የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ሌቦች በሏቸው - አጭበርባሪዎች፡፡ ለአብራኩ ክፋይ ለልጁ ግድ የሌለው - ሚስቱን በወጣ በገባ ቁጥር የሚነተርክ - ከጎረቤቱ ጋር ዐይንና ናጫ ሆኖ የሚኖር፣ ለቸገረው ወንድሙ አምስት ሣንቲም የማያቀምስ፣ ለተጨነቀ ጓደኛው አሥር ብር የማያበድር… ስግብግብና ፍቅርን የማያውቅ ዜጋ ለሥልጣን አራራውና ለግል ኢኮኖሚያዊ ጥቅሙ ሲል የዚህን ወይም የዚያኛውን ብሔረሰብ ስም በታፔላነት አንስቶ ቢጮህ እውነት አይምሰላችሁ፡፡ ለማያውቅህ ታጠን በሉት፡፡ በአባቱ ኦሮሞ በእናቱ አማራ የሆነ ለማን ሊታገል ነው  የጎሣ ቡድን ውስጥ የሚገባው? ለምሳሌ ስብሃት ነጋ ኤርትራዊነቱንም ኢትዮጵያዊነቱንም ትቶ ለትግራይ የበላይነትና ለወያኔ ንግሥና ቆሜያለሁ የሚል ሰው ነው ይባልለታል፡፡ ይህ ሰው፣ እውን ለትግራይ ይጨነቃል? ለትግራይ ሕዝብስ እንቅልፍ አጥቶ ያድራል? እንዲያ ከሆነ ስንትና ስንት ትግራውያን በርሀብ ሲሰቃዩ እንደማንኛውም ወገናቸው ሲለምኑና ሲቸገሩ በምዝበራና በሕገወጥ የገንዘብ ክምችት ብዙ ቢሊዮን ብር አለው ከሚባልለት ኤፈርት ትንሽ ገንዘብ ቆንጠር አድርገው ለምን አይረዱም? አዎ፣ ብዙ ነገሮች የታይታ ናቸው፤ ብዙ ነገሮች የብልጭልጭ ናቸው፡፡ የእንትና ብሔረሰብ ይልና በቁስልህ ሊገባ ይፈልጋል - ቁስልህን ተገን አድርጎ ወደልብህ ለመግባት ከሞከረ በኋላ ግን የርሱን ቁስል ባንተ ሀብትና ጥሪት ፈውሶና የድህነት ጭቅቅቱን አራግፎ ያንተን ቅስል ይብስ ያነግልብሃል፤ አንተም ከነድህነትህ እህህ እያልክ ትኖራለህ - ለሌላ ዙር እንግልትም ትጋለጥና የራበው አዲስ ተኩላ ከጫካም ይሁን ከከተማ  መጥቶ በአዲስ መልክ ይግጥሃል፡፡ ሕይወት እንዲህ ናት፡፡ አንዱ መሰላል ነው - ሌላው በመሰላሉ የሚወጣ ነቀዝና ተምች ነው፡፡ ታችኛው ግን ሞኝና እንደነዱሽ እንደሆነ ይቀራል፡፡ እነገሌ መጡብህ ካሉት እየደነበረ ከየሽርንቁላው ይወጣና አሰለጦች ባዘዙት መሠረት በንጹሓን ላይ ጦሩን ሰብቆ መሰል ወገኖቹ ላይ ይዘምታል፤ ብዙኃኑ ታችኛው የጥቂቶች ላይኞች መጠቀሚያ ጎጋ ነው፡፡ ከስቅሎ ስቅሎ በፊትም ሆነ በኋላ የዓለም ታሪክ እንደዚሁ ነው፤ ጥቂት ብልጦች ብዙኃንን ዕቃ’ቃ እንደተጫወቱባቸው ዓለም ‹ፍጻሜዋ ደረሰ›፡፡ አንዳንዱ እንደተሸወደ የሚገባውና ዐይኑን የሚገልጠው ራሱ ችግር ውስጥ ከገባ በኋላ  ነው፡፡ እነመለስ፣ እነኢሳይያስ በዚህ መልክ ሲጫወቱብን ከቆዩ በኋላ ነው እንግዲህ እነሱም በፋንታቸው የማይቀርላቸውን መሪር ጽዋ ሊጎነጩ የመጨረሻው ፊሽካ ብቻ እንደቀረው አምነን ያቺን የፍርድ ቀን በጉጉት እየተጠባበቅን የምንገኘው፡፡ በቃ፡፡
የነስብሃትና መሰሎቹ አገርና ወገን ሆዳቸው ነው፤ ሃይማኖታቸው ከፍ ሲል እንደጠቀስኩት ወሲብና መጠጥ ነው፡፡ የሚሉት ሁሉ ለማደናገሪያነት እንጂ የአንጀታቸውን አይደለም፡፡ ትዳርን የማያከብር ዘልዛላ፣ የክፉ ቀንን የትዳር ጓደኛና የልጆቹን እናት ሲያልፍለት አስወጥቶ የሚጥል ጉደኛ፣ ልጆቹን የማይሰበስብ  የሌሊት አውሬ ዳንኪረኛ፣ በሽምግልና ዕድሜው ከልጅ ልጆቹ ጋር የሚማግጥ ሠካራም ነውረኛ… በምን ሒሳብ ለሀገር ጠቃሚና ለወገን ተቆርቋሪ ሊሆን እንደሚችል አስቡት፡፡ ይቅርታ - ባደጉ ሀገሮች ከሕጻንነት ጀምሮ የሚመዘገብ የግል ሕይወት ይዞታ ለሥልጣን ዕጩነት ታላቁ መለኪያ በመሆኑ ይህን ስለባለሥልጣኖቻችን ዋልጌነትና እንስሳነት የምላችሁን ነገር በምን አገባህ አናንቃችሁ አትመልከቱት - በኛ ሀገር ደግሞ በተገላቢጦሹ ባለጌ ባለጌው እየተመረጠ ይመስላል ለሥልጣን የሚበቃው - አልጋውና ወንበሩ የሚወደው ጥፍራሞችንና መደዴዎችን መሆን አለበት፡፡
ሀገር ወዳድነት ላግጣ አይደለም - ሀገርን የመምራት ጠንካራ ጎን ደግሞ ከቤተሰብና ከራስ ጤናማ ኑሮ ይመነጫል፤ በሽተኛ ሰው እንኳንስ ሀገርን ራሱንም መምራት አይችልም፤ ሠካራምና እንደልቡ ተናጋሪ ሰው ደግሞ ከዕብድ ተለይቶ አይታይም፡፡ አሁንም ከዚህ ከምለው ነጥብ አኳያ እነስብሃትን ‹ለማያውቋችሁ ታጠኑ!› በሉልኝ፡፡ መቆሚያቸውን ለማደላደል የትግራይን ሕዝብ ‹ያንተዎቹ ነን፤ ከኛ ወዲያ ላንተ የተሻለ አማራጭ የለም፤ አማሮች ከመጡ ሥጋህን ዘልዝለው ይበሉሃል…› በማለት ሊያስፈራሩበት እንጂ በውነት የትግራይነት ስሜት ኖሯቸው አይደለም፡፡ ቀደም ካለ የትግላቸው ወቅት ጀምሮ እስካሁን ድረስ በትግራይ ሕዝብ ላይ የሠሯቸው ወንጀሎች ይህን የሚሉትን ነገር አያረጋግጡላቸውም፡፡ ብሎም ቢሆን ለትግራይ ምድርና ሕዝብ የሠሩት የልማትና የዕድገት እመርታ የለም ለማለት እንዳልሆነ በትህትና ላስታውስ እወዳለሁ፡፡ ሀገራችን ለሚሉት ብዙ ሠርተዋል - ይሁን፡፡ ጥጃ ጠባ እሆድ ገባ ነው፡፡ ቦዕ ጊዜ ለኩሉ ፤ ሌሎቹም በጊዜያቸው ይለማሉ፡፡
ነገር ቢበዛ በአህያ አይጫንም፡፡ ቀጥሎ በቅንጭብ ያመጣሁትን የፕሮፌሰርን ንግግር አዳምጡ፡-

ኤርትራ ዛሬ በሁሉም መስፈርት አስጠሊና የተገለለች አገር ሆናለች። ሕዝባችን ባሁኗ ወቅት ደቃቃዋ የፖለቲካ መብት እንኳ የሌለው፡ ሰብኣዊ መብቱ ፈጽሞ ያልተጠበቀ፡ እጅግ ከባድ ድህነት ያጐሳቈለው፡ ማህበራዊ ኑሮው ሰብኣዊነት የራቀው፡ የህላዌው ሁኔታ በፍርሃትና ስጋት ተበክሎ የደህንነትና የዋስትና ጭላንጭል እንኳን የሌለው ነው፡፡ የወጣቶቹ ሁኔታ በተለይ እጅግ የሚያሳዝን የከበደ ትራጀዲ ሆኗል፡፡ ወጣቱ ሊደሰትበት በሚገባ አፍላ ዕድሜው በግድ እየታፈሰ ሳዋ ወይም አገልግሎት ለሚባለው ባርነት እየተዳረገ ነው። ወጣቶቹ ከዚያ ገሃነማዊ ሁኔታ ለማማምለጥ ሙከራ ሲያደርጉ፡ ከስደት ወደ ስደት አገር ለመሸጋገር ሲሞክሩ አንዳንዱ ባሕር ውስጥ እየሰጠሙ ለምህረት-የለሽ ዓሳ ሲሳይ እየሆኑ ነው፣ አንዳንዱ ደግሞ በአረሜኔዎች ተጠልፈው እንደ እንስሳ እየታረዱ ኩላሊታቸውና  ሌላ ውስጣዊ አካላቸው እየተነጠቀ ሬሳቸው በሳሃራና በሲናይ ምድረ-በዳዎች እየበሰበሰ ነው፡፡ ይህ መከራ በጣም የሚዘገነን፡ ስትሰማውም እጅግ የሚያስደነግጥ ነው።
 ለመሆኑ ዜጎች ለዚህ አሰቃቂ መከራ ሲጋለጡ አስመራ ውስጥ ያለው መንግሥት ምን እየሰራ ነው? የሚል የዋህ ጠያቂ አታጣም። አስመራ ውስጥ ያለው አምባገነን ኢሳያስ የሚመራው መንግሥት እውነትም ኤርትራዊ መንግሥት አይደለም፣ በኤርትራውያን ላይ የጥላቻና የቂም በቀል ቁርሾ በያዙ፡ ድብቅ ሴራ ባላቸው አካላት የቆመ ቡድን (ካባል) ነው። እነኚህ ሴረኞች በትውልድ ትግሬዎች ቢሆኑም ኤርትራዊያን ሊሆኑ ይችሉ የነበሩ፡ ሆኖም ግን ምንነቱ ባልተመረመረ ችግር ምክንያት፡ ሕዝባችንን በሚያጠቃ መልኩ የ“ትግራይ-ትግርኚ” ንድፍ አዝማቾች ለመሆን የመረጡ ናቸው።
 ከዚህ ጋር በተዛመደ ሊነሳ የሚገባው አሳዛኝ ነገር አለ። ለብዙ ዓመታት ከበረሃ ትግል ጀምሮ እስከ ህግዲፍ መንግሥትነት ድረስ ኢሳያስን ያገለገሉ፡ እንደ እነ ሃይለ ወልደትንሳኤ፡(ድሩእ)፡ማሕሙድ ሸሪፎ፡ እስጢፋኖስ ስዩም፡ ጴጥሮስ ሰለሞን፡ ጀርማኖ ናቲ፡ ኣስቴር ፍስሓጽዮን፡ በራኺ ገብረስላሴ፡ ዑቕበ ኣብርሃ፡ ብርሃነ ገረዝጊሄር የመሳሰሉ፡ በዛ ገሃነማዊ የዒራዒሮ እስር ቤት ውስጥ ተቆልፎባቸው አንዳንዶቹ ሞተው፤አንዳንዶቹ ደግሞ እየተሰቃዩ ሞታቸውን ይጠባበቃሉ። እነኚህ ታጋዮች የፈጸሙት ወንጀል የለም። ኤርትራ ውስጥ ዲሞክራሲ እንዲጀመር ጥገናዊ የሆነ ለውጥ በመጠየቃቸው ብቻ ነው ለዚሁ አበሳ የተዳረጉት። እነዚህንና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችን የምትመለከት አንዲት አንገብጋቢ ነጥብ አለች፤ እርስዋም እኚህ በኢሳያስ የሚታሰሩና በተለያየ ዘዴ እየተገደሉ ያሉት ዜጎች በሙሉ ንጹሃን “ኤርትራዊያን” መሆናቸው ናት። በተቀረ፡ ብዙ ሰዎች እንደነገሩኝ ከሆነ፡ በትውልዳቸው ትግሬዎች የሆኑ ኤርትራውያን በኢሳያስ መንግስት እንዲገደሉ ወይንም እንዲታሰሩ የተደረጉ የሉም። ይህ አሳሳቢ የሆነ ትዝብት ነው!!
 ***
በጥያቄው የተሳተፉት የዛሬው የትግራይ ፖለቲከኞች (ወይም የፖለቲካ ተዋንያን - ማለት ኤሊት) እናት አገራችሁ ማነች ለሚለው ጥያቄ የሰጡት መልስ በመንፈስም በአስተሳሰብም ኤርትራውያን ፖለቲከኞቹ ከሰጡት መልስ አሳሳቢ በሆነ መጠን ይለያል። ከተሳተፉት የትግራይ ፖለቲከኞች መሃል እናት አገራችን ኢትዮጵያ ነች ብለው የመለሱ 3.6% ብቻ ናቸው። አብዛኛዎቹ በጥያቄው የተሳተፉ የትግራይ ፖለቲከኞች ግን እናት አገራችን ትግራይ ነች ነበር ያሉት። ኢትዮጵያ አላሉም። አቶ ስብሓት ነጋ ይህንን ጥያቄ ሲመልስ፡ ላንዳፍታ “ዝግ ካለና ካመነታ በኋላ”፡ እናት አገር ሲባል በአእምሮው ውስጥ ድቅን የምትልበት “ትግራይ“ መሆኗን ገልጿል። አንደዚሁም አቶ ጸጋይ በርሄ - እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የትግራይ ክልል ፕረዚደንት የነበረና፡ ዛሬ ግን የሕዝባዊ ወያነ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስራ አስፈጻሚ አባል የሆነው - ይህ ጥያቄ ቀርቦለት ሲመልስ ሳያመነታ በቀጥታ “እናት አገሬ ትግራይ ነች“ ነው ያለው። ኢትዮጵያ ነች አላለም። “ብትግሬነቴ በኩል አድርጌ ነው ኢትዮጵያዊ የምሆነው“ በማለት ግን መልሷን ስስ በሆነች ኢትዮጵያዊነት ሸፋፍኗታል።
 ይህ እናት አገራችን ትግራይ እንጂ ኢትዮጵያ አይደለችም የሚል መልስ ከታወቁ የሕዝባዊ ወያኔ አመራር አካሎች ሲደመጥ የሚያሳስብ ክስተት ነው። (ለምሳሌ አንድ በኤርትራዊ የፖለቲካ ድርጅት አመራር ውስጥ ያለ ሰው እናት አገሬ ብሎ ኤርትራን ከመጥቀስ ይልቅ ባርካን ወይም ቢለንን ወይም ኩናማን ቢጠቅስ፡ ወይንም ደግሞ ከደጋማው አውራጃዎቻችን - ማለትም ሓማሴን፡ አከለጉዛይ - ብሎ ቢጠቅስ፡ ለኛ ለኤርትራውያን እጅግ የሚያሳስበን ይመስለኛል!!

staff reporter | February 25, 2013 at 1:33 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1tD
Comment 

Sunday, February 24, 2013

አስሩ የጽልመት ቀናት-በኢትዮጵያ! (ከየካቲት 8/1929 – የካቲት 17/1929 ዓ.ም)በሰሎሞን ተሰማ ጂ.

(http://semnaworeq.blogspot.com )በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንን ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር፡፡Nikola Tesla Tells How He'd Defend Ethiopia Against Italian Invasion(www.tesla.hu/tesla/articles/19350922.doc) በቃለ-ምልልሱም ላይ ጋዜጠኛው ዶ/ር ኒኮላ ቴስላን እንዲህ ብሎ ጠየቀው፤ “ካለፈው የካቲት 1935 (እ.አ.አ) ጀምሮ ኢጣሊያን ኢትዮጵያን በኃይል ወራለች፡፡ አንተ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?” መላሹ ዶ/ር ኒኮላ ቴስላም ትንሽ ጊዜ ትክዝ ካለ በኋላ፤ “እኔ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብሆን ኖሮ፣ በከተሞች አካባቢ ያለውን ሕዝብ በመላ ወደገጠርና ወደዱር ገደሉ እንዲሄዱ አደርገዋለሁ፡፡ ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደገጠራማ ቦታዎች እንዲያፈገፍግ አዘዋለሁ፡፡” ጋዜጠኛው ጣልቃ ገባ፤ “ለምን?” አለው፡፡ ቴስላም ቀጠለ፤ “የአሁኗ ኢጣሊያ መሪዎች ክፉኛ ማስተዋል የጎደላቸው ጣሊያኖች ናቸው፡፡ የፋሺዝም ርዕዮት-ዓለም እውር አድርጓቸዋል፡፡ ስለሆነም ከፍተኛ ጭፍጨፋ በከተሞች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እንደሚፈጽሙ ይታየኛል፡፡ ስለሆነም ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደ ገጠራማ አካባቢዎች ወፍለስ አለበት፡፡” ጋዜጠኛው ግራ ገባው፤ ጥያቄዎቹን አዥጎደጎደ፤ “ኢጣሊያ ትልቅ አገርና በሥልጣኔም ቢሆን ከኢትዮጵያ የተሻለች ሆና ሳለ እንዴት እንደዚህ ያለ የአረመኔዎች ግፍ ልትፈጽም ትችላለች ብለህ ታስባለህ?” ሊቁ ኒኮላ ቴስላ ረጋ ባለ አንደበት መናገሩን ቀጠለ፤ “እንዳልከውና እናንተ ጋዜጠኞቹ እንደምትደሰኩሩት አይደለም፡፡ ኢጣሊያ ከአትዮጵያ የበለጠ ሥልጣኔ የላትም፤ ነገር ግን ቴክኖሎጂውና በዘመናት ውስጥ በጦርነት ምርኮና ዘረፋ ያከማቸችው ሀብት አላት፡፡ ኢትዮጵያ ግን ነፃነቷን ተከላካይ አገር አንጂ ወራሪ ሃይል ሆናም ስለማታውቅ በዝርፊያ የተከማቸ ሀብት የላትም፡፡ በሥልጣኔ በኩል ካየኸው ግን ኢትዮጵያ ጁሊየስ ቄሳር ከመነሳቱና የዛሬዋ ኢጣሊያ ከመፈጠራ በፊት ብዙ ሺህ አመታት በፊት የሰለጠነች አገር ናት፡፡ እናንተ ጋዜጠኞቹና የፋሺስት ፕሮፓጋንዲስቶቹ እንደምታወሩት አይደለም፡፡” ቴስላ ትንሽ ቆም አለ፡፡ ወዲያውም ቀጠል አድርጎ፤ “ይኼንን ስልህ ኢጣሊያ የእነሴኔካ፣ የነጆቫኒ ቦካሺዎ፣ የነፔትራርች፣ የነሊዎናርዶ ዳቬንቺ፣ የነሚካኤል አንጄሎና የነጋሊሊዮ ጋሊሊ አገር መሆኗን እያወቅኩ ነው፡፡ ዛሬ ኢጣሊያ (በ1920ዎቹ ማለቱ ነው) ያ የከያኒነትና የተመራማሪነት መንፈስ ከኢጣሊያ ጠፍቶ፣ በፋሺዝምና በጭፍን ካቶሊካዊነት ልጓም የሚፈረጥጡ ልጆች አገር ሆናለች፡፡” ሲል ለረጅም ደቂቃዎች በትካዜ ነጎደ፡፡ቴስላ የፈራውና የገመተው የአስተዋይነት መጥፋትና የጭፍንነት መንገሥ እውን ሆኖ ለመታየት ስድስት ወራት ብቻ ተቆጠሩ፡፡ ከየካቲት 12-14/1929 ዓ.ም ባሉት ሦስት ቀናት ውስጥ ማመዛዘን የማይችሉት ፋሺስቶች በኢትዮጵያውያን ላይ አለን እያሉ ከሚኮፈሱበትና ከሚመጻደቁበት “ሥልጣኔያቸው” ጋር አብሮ የማይኼድ አረማዊ ሥራ ሠሩ፡፡ ፋሺዝምም ሆነ ኮትኩቶና በሮማ አደባባይ መርቆ ሂዱ ኢትዮጵያን ውረሩ ብሎ የላካቸው ካቶሊክኢዝም ምን ያህል “ሥልጡን” እንደነበሩ በገሀድ አሳዩ፡፡ (አፈር ድሜ ኮትኳችነት-እቴ!) በተጨማሪም፣ የፋሺዝምን ዘረኝነትና ዘላለማዊ ቁስሉን ለዓለም አስመሰከሩ፡፡ ከ76 ዓመታት በኋላ ቁስሉ የጠገገኛ የዳነ ቢመስልም እንኳን፣ ጠባሳውን ስድስት ኪሎ በሚገኘው የየካቲት 12 ሰማዕታት ሃውልት አማካይነት ሕዝብ ዕለት በዕለት ያየዋል፡፡ ምን ያህሉ ምስጢሩ ገብቶት፣ የቁስሉ ሕመምና የጠባሳው ግዝፈት እንደሚያንገበግበው ባላውቅም፤ ገሚሱ በእግር፣ ሌላው በመኪና እግር (ጎማ) ሲያልፍና ሲያገድም ያየዋል፡፡ “ምን ያሕሉስ እነዚያን የጽልመትና የመከራ ቀናት ከአምሳለ-ሃውልቱ ተሻግሮ ያስተውላቸዋል?” የሚለውን መገመቱ ግን ይከብዳል፡፡ (በነገራችን ላይ፣ ቤላ የሚገኘው የኢጣሊያ ኤምባሲ ዲፕሎማቲክ አባላት በዚህ ሃውልት በኩል ለማለፍ ጨርሶ አይዳዱም፡፡ በራሳቸው ወጪ ባሰሩትና ከሕሊናቸው ለመሸሽ ብለው በዘየዱት አቋራጭ መንገዳቸው፣ በጀርመን ኤምባሲ በኩል ይገባሉ-ይወጣሉ እንጂ የቤላ ስድስት ኪሎ መንገድን ለመጠቀም አይሹም፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል!)

የየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም በይፋ ማክበር የተጀመረው በ1934 ዓ.ም ነው፡፡ በዚያን ጊዜ የነረውም ሃውልት፣ ይህ ዛሬ ትከሻውን አሳብጦ፣ ደረቱን ገልብጦ ቆሞ የምናው ሃውልት አልነበረም የተተከለው፡፡ ያኛው ሃውልት እስከ 21ኛው የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን (ማለትም፣ እስከ 1950 ዓ.ም ድረስ ለመታሰቢያነት ሲያገለግል ቆየ በኋላ፣ በ22ተኛው የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን/ዕለት ይኼኛው የመታሰቢያ ሃውልት በዩጎዝላቪያ መንግሥት ርዳታ (“በማሻል ዴኒስ ቲቶ እርዳታ አማካይነት” ማለቱ ሳይሻል አይቀርም) በ1951 ዓ.ም በይፋ ተመረቀ፡፡ ለዚሁ የሃውልት ምረቃና ለተለያዩ የጉብኝትና የወዳጅነት ሥራዎችም ሲሉ የዩጎዝላቪያው ፕ/ት ማርሻል ዴኒስ ቲቶ ከነባለቤታቸው፣ ከጥር 25 ቀን 1951 ዓ.ም እስከ የካቲት 6 ቀን 1951 ዓ.ም ድረስ ይፋ ጉብኝት አድርገው ነበር (አዲስ ዘመን፣ የካቲት 7/1951 ዓ.ም፣ ገጽ 1)፡፡ ይህም ጉብኝታቸው ለሁለተኛ ጊዜ የተደረገ ጉብኝት ነበር፡፡ ቀዳሚው ጉብኝት ከታኅሣሥና በጥር 1948 ዓ.ም የተደረገ ይፋ የ14 ቀናት ጉብኝት ነበር፡፡ ምናልባትም በዚህ ወቅት ሳይሆን አይቀርም ስለየካቲት 12ቱ የሰማዕታት ሃውልት ሥራ/ትብብር የተጠየቁት፡፡ በዚህም መሠረት የሥነ-ሃውልትና የቅርጻ-ቅርጽ ባለሙያዎች ከዩጎዝላቪያ መጥተው ይህ ዛሬ የምናየው ሃውልት በመጀመሪያው ሃውልት ስፍራ ላይ ተተካ፡፡
ከየካቲት 12ቱ የሃውልት አሠራርና ታሪክ ጋር ተያያዥ ከሆኑ ጉዳዮች ወጥተን፣ በቀጥታ ወደ የካቲት 1929 ዓ.ም እንለፍ፡፡ የካቲት 1929 ዓመተ ምህረትን ያህል ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የመከራና የጽልመት ወራት ኖሮ አያውቁም፡፡ በጣም የሚገርመው፣ በዚሁ በወርኃ የካቲት 1888 ዓመተ ምህረትም ከሰባ ሺህ በላይ ወገኖቻችንን መሥዋዕት አድርገናል፡፡ ግፈኛው የንጉሥ ኡምቤርቶ ጦር፣ በጄኔራል ባራቴሪ እየተመራ ሃይማኖት ሊቀለብስ፣ መሬት ሊቆርስ፣ ነፃነታችንን ሊገስ መጥቶ ማጭድና ጎራዴ፣ ጦርና ጋሻ የያዙትን ወኔያም አያቶቻችንንና ቅድመ-አያቶቻችንን በመድፍና በዘመኑ መሳሪያዎች ፈጃቸው፡፡ ከአርባ አንድ ዓመታት በኋላ ተመልሶ ለወረራ የመጣው በማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ የሚመራው የፋሺስትም ጦር፣ ከየካቲት 12 ቀን እስከ የካቲት 14 ድረስ ባሉት ሦስት ቀናት ከሠላሳ ሺህ በላይ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያንን ፈጃቸው፡፡ ጣሊያን ብቻውን አልነበረም፤ የእኛም ሰዎች አጅ አለበት፡፡ ለጣሊያን ጭፍጨፋዎች ተባባሪ ሆነን ጭፍጨፋውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አግዘናል፡፡ (“እኛ” የምለው “እኛ የኢትዮጵያዊነትን ጽድቅና እውነት” ችላ ብለን ለጣሊያን በባንዳነትና በጭፍራነት ወይም በአስካሪነት ተሰልፈው የነበሩትን ኤርትራውያን ምንደኞችም አካትቼ ነው፡፡ “እኛ” ስል “እኛን የባንዳቹንና የአስካሪዎቹንም ልጆችና የልጅ-ልጆች ያካትታል”፡፡ አባቶቻችንን ለመውቀስ አፋችንን-ከማሾላችን በፊት “እኛስ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምን አስተዋጽኦ አበርክተናል? ምንስ ልናበረክት እንችላለን?” የሚሉትን ከታሪክ-ሕሊና የማይጠፉ ጥያቄዎች ደጋግመን ልንጠይቅ ይገባናል፡፡)
ወደዋናው ጉዳያችን እንመለስ፤ ወርሃ የካቲት ከማይዘነጋባቸውና ከሚታወስባቸው ነገሮች መካከል አንዱ በየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም የተከሰቱት አስር መራራ የጽልመት ቀናት ናቸው፡፡ እነዚህም አስር ቀናት ከየካቲት 8 እስከ የካቲት 17/1929 ዓ.ም ድረስ ያሉትን የሚመለከት ነው፡፡ በነዚህ ቀናት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን የተደገሰው የሞት ድግስ እጅግ ዘግናኝና ኢ-ሰብአዊም ነበረ፡፡ መነሻዎቹ ሁለት ናቸው፤ የመጀመሪያው ለአርበኝነት ሙያ ወደደቡብ ዘምቶ የነበረውን የራስ ደስታ ጦር ለመምታት በርካታ ጦር አስከትሎ ሄዶ የነበረው ማርሻል ግራዚያኒ ሞቷል ተብሎ ወሬ ይናፈስበታል፡፡ ይኼንንም ወሬ በስፋት ሲያስወሩበት የነበሩት እነአብራሃ ደቦጭና እነሞገስ አስገዶም እንደነበሩ ይገመታል (መቶ አለቃ መለሰልኝ አንለይ፤ በ1947 ዓ.ም በጻፈው መጽሐፍ ላይ እንደገለጸው)፡፡ ሁለተኛውና ዋናው ዳፋ ደግሞ፤ “በየካቲት 12/1929 ዓ.ም በገነተ ልዑል ቤተ-መንግስት መግቢያ በር/በረንዳ ላይ በማርሻል ግራዚያኒ ላይ በነአብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም አማካይነት የመግደል ሙከራ ስለተደረገበት ነው” ሲል ኢያን ካምፔል ያትታል (Ian Campbell; The Plot to Kill Graziani. 2003 ዓ.ም)፡፡ በተጨማሪም፣ ግራዚያኒን በመግደሉ ሴራ ውስጥ “የንጉሠ ነገሥቱ ዋና ዋና ባለሟሎች እነደጃዝማች ለጥይበሉ ገብሬ፣ እነጄነራል መኮንን ደነቀ፣ እና ሌሎችም በቀጥታ ከንጉሠ ነገሥቱ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት ወይም በተላከላቸው ደብዳቤ መሠረት ተካፍለዋል፤” ሲል ይገልፃል፡፡ ብርሃኑ ደቦጭ ለሙዚክ ሜይዴይ የመጽሐፍት ግምገማ ክበብ ተናጋሪዎች በየካቲት 2004 ዓ.ም እንደተናገረው፣ ይህንን ጥርጣሬ አምኖ ለመቀበል ይከብዳል፡፡ ምክንያቱም፣ የአብዛኞቹን ተጠርጣሪዎች ወይም ኢያን ካምፔል እንደሚለው “ሴረኞች” ቃል በቀጥታ ማግኘት ስላልቻለ ነው፡፡ ብዙዎቹ ለዚህ መጽሐፍ ዋቢ ተደርገው የተገለጹት የአርበኞች ማኅበር አባላትም ሆኑ የሴረኞቹ ልጆች ስለሴራው የቀጥታ ዕውቀትም ሆነ ተሳትፎ የሌላቸው በስማ በለው የሚናገሩ ሰዎች ናቸው፡፡ (በዚህ መጽሐፍ ላይ ሰፊ ውይይትና ክርክር ሊደረግበት እንደሚገባ እምነቴ የፀና ነው፡፡ ኢያን ካምፔል በዋነኝነት የመረጃ ምንጭ አድርጎ የተጠቀማቸውን ሰዎችና ሰነዶች እንደገና መመርመሩ የሚገባ ነው፡፡ ጉዳዩን ጉዳዬ ብሎ ስላጠናውና ስለለፋበት ምስጋና ይገባዋል፡፡)
መቶ አለቃም መለሰልኝም ሆነ ኢያን ካምፔል የፈለጉትን መነሻና መድረሻ ሊያቀርቡ ቢሞክሩ፣ ከየካቲት 12 እስከ የካቲት 14 ቀን 1929 ዓ.ም የተፈጸመው ጭፍጨፋ በንጹኃን ላይ የተፈጸመ ግድያ ነው፡፡ ሰላማዊያኑ ኢትዮጵያዊያን በግፍ ዕልቂት የተፈጁበት ይህ ዕለት የተፈጸማ በዕለተ ዐርብ 1929 ዓ.ም ነበር፡፡ ከዚህ ቀን ሁለት ቀናት ቀደም ብሎ (ረቡዕ የካቲት 10/1929 ዓ.ም) ግራዚያኒ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ፡፡ ለሕዝቡም ሞተ ተብሎ የተወራው ስሕተት እንደነበረና ምንም ያለ መሆኑን ለማሳየት/ለማረጋገጥ ስለፈለገ በማግሥቱ የካቲት 11 ቀን 1929 ዓ.ም በዛሬው የየካቲት 12 አደባባይ ላይ እንዲሰበሰቡ አስለፈፈ፡፡ ሆኖም የተሰብሳቢው ቁጥር ስላነሰበትና ያሰበውን ያህል ትኩረት እንዳለገኘ ስለተሰማው፣ በማግሥቱ ዐርብ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም ከቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ መልስ (ልክ ከጥዋቱ በ4፡00 ሰዓት ሕዝቡ በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ፊት ለፊት እንዲሰበሰብ አዘዘ፡፡ ለነዲያንና ለችግረኞችም ብዙ ሊሬ እንደሚሰጥ ጭምር አስለፈፈ፡፡
የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም ልክ በአራት ሰዓት ይጀመራል የተባለው ፕሮግራም ግብጻዊው አቡን፣ አቡነ ቄርሎስ ታምሜያለሁ ብሎ ስለቀረ/ስለዘገየ እስከሚመጣ ድረስ ለአንድ ሰዓት ያህል ዘገየ፡፡ ወታደር ተልኮ አበኑ ልክ 4፡55 ሰዓት ቤተ መንግሥት ደረሰ፡፡ ወንበር መጥቶለት ከግራዚያኒ በስተቀኝ በኩል ከከፍተኛ የፋሺስት ባለስልጣናት ጎን ተቀመጠ፡፡ ከግራዚያኒም በስተግራ በኩል ጄኔራል ጋሪባልዲ፣ ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ (የአፄ ዮሐንስ የልጅ-ልጅ)፣ ራስ ኃይሉ ተክለ ሃይማኖት (የጎጃሙ ንጉስ ልጅ) ከሌሎች የኤርትራ ባንዶች ጋር ተጎልተው ነበር፡፡ ልክ 5፡00 ሲል ግራዚያኒ ሻኛው እንዳበጠ ኮርማ ቁና ቁና እየተነፈሰ ኢትዮጵያውያንን ያበሻቅጥ ጀመር፡፡ “ይኼው አለሁ!... መቷል እያላችሁ የምታወሩትና የምታስወሩት ሁሉ ከንቱ ሟርት ነው፡፡” እያለ የኢትዮጵያን ሕዝብ በገዛ አገሩና በገዛ መሬቱ ላይ ያዋርደው ጀመር፡፡ (ግራዚያኒና ተባባሪዎቹ ቆመው የነበረው የቤተ መንግሥቱ በረንዳ ላይ ነበር፡፡)
ልክ 5፡15 ሰዓት ገደማ ሲሆን አብራሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ከበረንዳው በላይ ባለው ፎቅ ላይ/ግራዚያኒ ከቆመበት ሥፍራ ላይ ጥቁር ሸሚዝ ለብሰው፣ ኩታቸውን ተከናንበው ታዩ፡፡ ዓይኖቻቸው በንቃት ይንተገተጋሉ፡፡ ሰዓቱ ፍጥነቱን ጠብቆ ተጓዘ፡፡ ልክ 5፡30 ሲሆን ለነዲያን ምጽዋት መሥጠት ተጀመረ፡፡ በሥፍራው ከሦስት ሺህ ሁለት መቶ (3,200) በላይ ነዲያን ነበሩ፡፡ እንዲሁም ግብር ሊበሉ የመጡ በርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም ግራዚያኒና ግብረ አበሮቹ ከቆሙበት ስፍራ በአሥር ወይም አሥራ ሁለት ሜትር ርቀት ላይ ከበው ቆመው ነበር፡፡ ከሰዎቹም ፈንጠር ብለው ከዘጠና የማያንሱ መትረየሳቸውን የደገኑ ሶላቶዎችና አስካሪዎች በተጠንቀቅ ቆመዋል፡፡ ነዲያኑን ራቅ እንዲሉ ይገፋቸው ጀመር፡፡ ጫጫታና ውካታው ከፍ ብሎም ይሰማ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ለአሥር ደቂቃዎች ያህል ትርምስምሱ የወጣ ትዕይንት ይታይ ጀመር፡፡
ነገር ግን፣ በግምት ከ5፡40 እስከ 5፡45 ድረስ ባሉት አምስት ደቂቃዎች ውስጥ ተከታትለው ቦንቦች እነአብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ካሉበት ደርብ ላይ ቁልቀል ተወረወሩ፡፡ የመጀመሪያው እንደተመረወረ ብዙዎቹ የመሰላቸው ለስብሰባው ማድመቂያ መድፍ የተተኮሰ ነበር፡፡ ሁለተኛው ሲወረወር ግን፣ አቡነ ቄርሎስና ግራዚያኒ መሬት ያዙ፡፡ በስተ ግራ በኩል ያሉትም ሁለት ጥበቃዎች ወዲያውኑ ሞቱ፡፡ ሦስተኛው ሲወረመርም፣ ግራዚያኒ ወደ ቤተ መንግሥቱ ሊገባ ፊቱን አዙሮ መሸምጠጥ ጀምሮ ነበር፡፡ ሆኖም፣ የሦስተኛው ቦንብ ፍንጣሪዎች በርካታ ቦታ አቆሠሉት፡፡ ዳኒሎ ብቢሪንዴሊ የተባው የካሜራ ባለሙያም እየደማና እያቃሰተ የነበረውን ግራዚያኒን አንስቶ ከ5፡50 እስከ 6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ መኪናው ከተተው፡፡ በፍጥነት ወደ ኦስፒዳሌ ኢታሊያኖ (የጣሊያን ሆስፒታል ለማለት ነው፤ የዛሬው “ራስ ደስታ ሆስፒታል” መሆኑን ልብ ይሏል፤) ወሰዱት፡፡
ከየካቲት 12 ቀን 1929ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓትም ጀምሮ እስከ የካቲት 14 ቀን 1929 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ድረስ ከሰላሳ ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን በግፍ ተፈጁ፡፡ ብዙ ጊዜ የሚነገረው ቁጥር በአዲስ አበባ ብቻ የተፈፀመውን ግድያ የሚያሳይ ነው፡፡ በፋሺስቱ ግራዚያኒና በግበረ አበሮቹ በኢትዮጵያዊያኑም ትብብር አመላው ኢትዮጵያ አውራጃችና ቀበሌዎች ባልቴት፣ ሽማግሌ፣ ሕፃን፣ ወጣት፣ ካሕን፣ ሴት፣ እስላም፣ ክርስቲያን፣ አረማዊ፣ ማንም ከማንም ሳይለይ ተፈጀ፡፡ ፕ/ር መስፍን “አገቱኒ፣ ተምረን ወጣን” ባሉት መጽሐፋቸው እንደገለጹት የአምስት አመት ልጅ ሳይቀር አልጋ ስር ተደብቆ ነበር ያንን የጽልመት ቀን ለጥቂት የተረፈው፡፡
አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበሩትና በወቅቱ በስፍራው የነበሩት አሃዱ ሳቡሬ በየካቲት 12 ቀን 1947 ዓ.ም እንደገለጹት፣ “ኢትዮጵያን መሬቷን እንጂ ሕዝቧን አንፈልግም በሚል ዘረኛነት” የፈጀውና ያስፈጀው ግራዚያኒ፣ በከተማ ነዋሪ የነበሩትን ኢትዮጵያውያን እርጉዝና ሽባዎችን ሳይቀር ነበር ያስፈጃቸው፡፡ ግድያው በመትረየስና በጠብ ምንጃ ብቻ አልነበረም፡፡ በአካፋ ተጨፍጭፈው፣ በዶማም ተፈልጠው፣ በፋስና በመጥረቢያም ተቆራርጠው የሞቱትን ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ ከቤታቸው ለመውጣትና ለማምለጥ ያልቻሉትን ባልቴቶችና ሽማግላችም ቤቱን የኋሊት እየዘጉባቸው ነበር እሳት ጎጇቸው ላይ የለኮሱባቸው፡፡ ልብ ማለት ያለብን ቁም ነገር አለ፤ ፋሺሽት ብቻውን አይፈደለም ይኼንን ግፍ የፈጸመው፡፡ የኛው ሰዎች ተባባሪ (ባንዳና አስቃሪ) ሆነው ነው እልቂቱን ያባባሱት፡፡
በዚህ ለሦስት መዓልትና ለሦስት ሌሊት ሢፈጸም በነበረው ግፍ ወቅት፣ የኢትዮጵያውያኑ ሰማዕታት አስክሬን በገዛ አገሩ ጥርኝ አፈር ተነፍጎ በየጎዳናው ተዘርሮ፣ ደሙም እንደሐምሌ ጎርፍ ሲጥለቀለቅ፣ በገዛ ቤታቸው የተቃጠሉትና የቤቱ ቃጠሎ ነበልባል ደግሞ ጢስ እስከ ሰማይ ሲያርግ ያዩ የዐይን ምስክሮች ዛሬም አሉ፡፡ በዚያን ጊዜ፣ የኢትዮጵያውያኑ ዕንባ እስከ ሰማየ-ሰማያት ደርሶ “እስከ ማዕዜኑ ትረስአኒ ለግሙራ” እያለ ሲጮህ ይሰማ ነበር፡፡ በአራተኛው ቀን (የካቲት 15/1929 ዓ.ም) ግን ነገሮች ጋብ ያሉ መሰሉ፡፡ የግራዚያኒም ቁጣ የበረደ መሰለ፡፡ ለከተማዎቹም ጽዳት ሲባል የሰማዕታቱ አስክሬን አፈር እንዲቀምስ ተደረገ፡፡ ብዙዎቹ በቡልዶዘር አማካይነት በጅምላ ተቀበሩ፡፡ እነዚህ የጅምላ መቃብሮች (ብዙዎቹ) ዛሬም በቅጡ አይታወቁም፡፡ የተወሰኑት ግን ለአጽማቸው ማረፊያና መታሰቢያ ተብሎ በቅድስት ሥላሴ ሃውልት ቆሞላቸዋል፡፡
የዚህ ግፍና ፋሺስታዊ ስራ ግንባር ቀደም ተዋናይ የነበረው ሩዶልፍ ግራዚያኒ ሃውልት ቆሞለት፣ መናፈሻም ተሰርቶለታል፡፡ በቅርቡ ደግሞ፣ ቤርሎስኮኒ የሚባለው የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር ሞሶሎኒን የሚያመሰግን ቃል ሲናገር ተደምጧል፡፡ ጣሊያን ተመልሳ ወደ ኢትዮጵያውያንና ወደ አፍሪካውያን ጠላቶች አስተሳሰብ እየገባች ነው፡፡ ክብር ለማይገባቸው ግፈኞች፣ ክብርንና ሞገስን የሚሰጡትን ሁሉ በያለንበት ሆነን ልንቃወማቸው ይገባል፡፡ (ክብር ለማይገባቸው ክብርን የሚሰጡ ክብረ-ቢሶች ብቻ ናቸው፡፡) ዛሬውኑ ፋሺዝምን ማንሰራራት በሚደግፈው የኢጣሊያን መንግሥትና አንዳንድ ደናቁርት ላይ እንረባረብ፡፡ የኢጣሊያን ኤምባሲዎች በሚገኙበት ቦታ ሁሉ ተሰባስበን ድምጻችንን እናሰማ፡፡ በማኅበራዊ ድረ-ገፆችም ላይ ተቃውሟችንን እናሰማ፡፡ በተጨማሪም፣ የተለያዩ የግፍ ድርጊቶቻቸውን በመጽሐፍም ሆነ በፊልም አቀናብረን ለእውነቱ ከሰማዕታቱ ጋር እንቁም፡፡ በግፍ ለፈሰሰው ሰላማዊ ኢትዮጵያውያን ደም የተከፈለው 30 ሚሊዮን ዶላር በቂ አይደለምና የጦር ካሳ ኢጣሊያ እንድትከፍል የተደራጀ ዓለም አቀፋዊ ዘመቻ እንቀላቀል፡፡ አጠገባችን ያለውን ለኢትዮጵያውያን ክብርና ሞገስ የማይቆም ግድግዳ በጋራ እናስወግድ፡፡ (የሳምንት ሰዎች ይበለን!)

በሳምንታዊው የአዲስጉዳይ መጽሔት ቅጽ 7፣ ቁ. 152 ላይ፤ በየካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም የወጣ ነው::

staff reporter | February 23, 2013 at 8:41 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1sW

Comment   See all comments

«ለዚህ ሕዝብ ብትወድቅ ክብር ነው»

 


በትግል ዘመንም ውስጥ ሆነ ከትግል ውጭ በስልጣን ዘመን አቶ መለስ ዜናዊ በተንኮል አሳሪነታቸው በጣም ከመታወቃቸውም በላይ ይፈሩም ነበር ለምን ሲባል የሚጠነሡት ሃሳብ ብዙዎችን በጭምብል እንዲጠፉ ማድረጋቸው ይታወቃል እና ነው እርግጥም ነው አንድ ነገር ተጀምሮ ለገሰ ዜናዊ አለበት ከተባለ ወደ ኋላ የማይሸሽ ማንም የለም ፣ለዚያም ይመስላል መስራቾቹ ትግላቸውን ከምእራፉ ሳይደርሱ ገና በእንጭጩ ለመለየት የተገደዱት ።ዛሬም ሆነ ትላንት ስለ መልካምነታቸው ከሚወራው ይልቅ ስለ ክፋታቸው የሚወራው ይበልጥ ይገን ነበር በተለይም ስልጣን ይዘው ለ14 አመታት እስከመሩበት ጊዜ ድረስ ማለትም 1997 ምንም ነገር በሃገሪቱ ላይ ሳይሰሩ ገንዘብ ከአለም አቀፍ አገራት በመቀበል እና በመሸኘት የተካኑት እና ለቅርብ ወገኖቻቸው እንዲሁም አባሎቻቸው በማደል ጥቅማቸው እንዳይነካ በማስከበር ትልቁን ሚና ሲጫወቱ መቆየታቸው ይታወሳል ።ሆኖም በምርጫ 97 አመተ ምህረት የህብረተሰቡን የፖለቲካ ንቃተ ህሊና የጠነሰሰ ጉዳይ ተፈጠረ ።በቅንጅት የተሰኘው የሰማይ ላይ ጉም ታይቶ ብን ያለ ለህዙ ተስፋ እንደ መና መግቦ ረሃብ የለቀቀ የጨለማ ተስፈኞች የተሰባሰበበት ድርጅት ፣በመሰረታዊ እድገቶች እና የሃገር ጉዳይ ጥቅም ላይ ሲያሽከረክራቸው በነበራቸው ቁም ነገሮች ላይ ወያኔን አይኑን ገልጦ እንዲመለከት እረዳው ዛሬም ድረስ አድገናል ብለው የሚደነፉበትን መንገድ እንዲጠርግላቸው እረድቶአቸዋል ።ይህም ሆኖ ሳለ በመለስ አስተዳደር የሚመራው ድርጅት ካፒታሉን በሃገሪቱ ላይ መሰረት ጥሎ ዘረፋውን ማከናወኑን ቀጥሎ ከበስተጀርባ በደሃው ህብረተሰብ ገንዘብ ደግሞ አባይን እንገድብ በማለት ጥንሥስ ሃሳብ ይዞ በመምጣት የህብረተሰብን ቀልብ ለመግዛት ቢሞክርም ከድጡ ወደ ማቱ መግባቱን አለማወቁን የተረዱት ወያኔዎች የትምኒትን እና እንደዚሁም የኢፈርትን ካፒታል ወደ ኋላ በመሸሸግ የህዝቡን ገንዘብ እና ደመወዝ በማራቆት ቁፋሮ በመጀመሩ የህዳሴው አባት እያሉ ማቆላመጣቸውን ተያያዙት ፣አዎ መለስ እውነትም የህዳሴው የለውጥ አርአያ ነው ተብሎ ሊወደስ የሚገባው አጡራ ሰው ነው ማለት የማይቻል ለመሆኑ የሃገሪቱ ህዝብ ብቻ ምስክር ሊሆን እንደሚችል ይታወቃል ፣ ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ ተፈጥሮ ያደለችንን ነሳነታችንን የነፈገን፣ብዙ ንጹሃኖችን ያስገደለ ፣ወዳጆቹን በመርዝ ያስጨረሰ ፣ብሎም ነጻ ፕሬሱን እና የሃገሪቱን ህግጋት በማገላበጥ ከብሄር ብሄረሰቦች አንድነት የቂም በቀልነት እና ጥላቻን የዘራብን የ እፉኝት እባብ መርዝ እንደነበር ሁላችንም ልንረዳው እና ልናውቀው የምንችለው ሃሳብ ነው ።ሆኖም ዛሬ ይህንን እንዲህ ለመናገር ያስቻለኝ የተለያዩ ህትመቶችን ሳገላብጥ የሃገሪቱ ከምታሳትማቸው እና በወያኔ መንግስት ስር ብቻ የሚተዳደሩት መገናኛ ብዙሃናት ያሉ የህትመት ድርጅቶች ፈቃድ አግኝተው ከሚያሳትሙት ዘመን መጽሄት ላይ ስለ አቶ መለስ ዜናዊ ስዩም መስፍን የተናገረውን ሃሳብ እኔም ለወዳጆቼ ላካፍላችሁ በማለት ከስር ሙሉ ቃለመጠይቁን አቀረብኩት ።አጠቃላይ ከርእሱ ጀምሮ ሙሉ ቃለመጠይቁ ከዘመን መጽሄት መወሰዱን ከመግለጽ አላልፍም ይህንንም ስናደርግ አሁን መንግስት በዚህ መገናኛ ብዙሃን ላይ ማስፈር የሚፈልገውን ሃሳብ ከመፍቀድ ወደ ኋላ አንልም ፣መማር ብቻም ሳይሆን ማስተማር እንደምንችል የምናሳይበት ትልቁ አብነታችን ነው ።
ላለፉት 40 ዓመታት አብረው ቆይተዋል፡፡ ከሰኔ 1964 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እንደ ወንድምም፣ እንደ ስራ ባልደረባም፣ እንደ ትግል ጓድም ሆነው ብዙ ውጣ ውረዶችን አብረው አሳልፈዋል፤ አቶ መለስና አምባሳደር ስዩም መስፍን፡፡ መለስ እንደ ማለዳ ጀንበር ለአፍታ ቀና ብሎ ሕዝቡ ለእርሱ ያሳየውን ክብርና ፍቅር ባየ እንዴት መልካም ነበር? የሚሉት አምባሳደር ስዩም በትግሉ ዘመን ከአቶ መለስ ጋር ስላሳለፉት መከራና ችግር፤ ስለ አቶ መለስ ባህሪም አጫውተውናል፡፡ አምባሳደር ስዩም በጓዳቸው ህልፈት ክፉኛ ማዘናቸው ያስታውቃል፡፡ ባነጋገርናቸው ጊዜም እንባቸው ለመውረድ ይታገላቸው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ‹እንበርታ እግዚአብሄሔር ያፅናን› ብለዋል፡፡
 
ዘመን፦ እንደሚታወቀው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት የኢትዮጵያ ሕዝብ በጣም አዝኗል። ይህን ኀዘን እርስዎ እንዴት ይገልፁታል?
አምባሳደር ስዩም፦ ሕዝቡ ከሚገልፀው የተሻለ አንደበት የለኝም። ጥልቅ ኀዘን ውስጥ ነው ያለነው። አገሪቱ በሙሉ፤ በውስጥም በውጭም ያለው ሕዝባችን፣ የኢትዮጵያ ወዳጅ፣ጠቅላይ ሚኒስትሩን ያውቁዋቸው የነበሩና ጓደኞቻቸው በሙሉ ያልተጠበቀና ድንገተኛ ህልፈት ስለሆነባቸው ሁሉም ጥልቅ ሐዘን ውስጥ ነው ያሉት። እንግዲህ ይሄ የተፈጥሮ ሕግ ነው። የሰው ልጅ በህይወት እንደሚኖር ሁሉ ማለፉ ደግሞ የማይቀር ነው። በእርግጥ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን ህልፈት በብዙ መንገድ መቀበል አቅቶናል፡፡ ምክንያቱም ብዙ ውጥን ነበረው።
እንደሚታወቀው ድርጅቱ(ኢህአዴግ) የአመራር ሽግግር ላይ ነው ያለው። ከኔ የተሻለ ወጣቱ ትውልድ ቦታውን ይረከብ የሚል አቋም ነበረው፡፡ እናም ስልጣኔን እለቃለሁ ማረፍም እፈልጋለሁ ሲል ቆይቷል።የድርጅቱ ውሳኔ ስለሆነበትና እስከ መጪው ምርጫ ድረስ አምስት ዓመታቱን በግድ መቆየት አለብህ ተብሎ ነው በስልጣን ላይ እስካሁን የቆየው፡፡ ይህን ግን እርሱ ባያምንበትም ለድርጅቱ ዴሞክራሲያዊ ውሳኔ ተገዢ ሆኖ ነው የቀጠለው። በዚህ አምስት አመታት ውስጥም የወጣቱንና የአዲሱን ትውልድ የአገር ተረካቢነት ሚና የማጠናከርና በድርጅቱም፣ በመንግሥትም ውስጥ ተተኪና ጠንካራ አመራርን የመፍጠር እቅድ ነበረው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱንና የመንግሥትን አመራር ሳያጠናክሩ የልማቱን ጉዞ በተያዘው አቅጣጫና በተፈለገው ፍጥነት ለማስኬድ ስለማይቻል ነው፡፡ ይህን እንደ አይነተኛ ጉዳይ አድርጎ ነው ሲንቀሳቀስ የነበረው፡፡ ይህ ውጥን ነበረው። ራዕዩ እውን እንዲሆንና የሕዝቡም ልማት በሚያስተማምን ፅኑ መሰረት ላይ እንዲቆም ፍላጎት ነበረው፡፡ እድል አግኝቶ እንደጠለቀችና ተመልሳ በነጋታው የብርሃኗን ድምቀት እንደምትሰጥ ፀሀይ ለአፍታም ቢሆን ቀና ብሎ ቢያየው እንዴት ጥሩ ነበር? እርሱ የቀየሰው ራዕዩ፣ መስመሩ፤ የኢህአዴግ አባልና ደጋፊው ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በተለይ ደግሞ ጭቁኗ ሴት፣ አፍላው ወጣት፣አርሶአደሩ፣ ሰራተኛው፣ ምሁሩ፣ ባለሀብቱ፣ ነጋዴው፣ ሁሉም መፍትሄያችን ነው፣ የሀገራችን ህዳሴ ነው፣ ድህነት ከፈጠረብን ውርደት የምንወጣበት መንገድ ነው እያለ ነው፡፡ ይሄ የሁሉም አስተሳሰብ ሆኖ ሁሉም በአንድ ድምጽ በድህነት ላይ የዘመተበት መሆኑንና በዚህ ደረጃ ለእርሱ እየገለፀ ባለው ፍቅርና ሀዘን ልቡ እየነደደ መሆኑን ለማየት ቢችል ኖሮ ‹የቀረብኝ ነገር የለም፣ መስራት ያለብኝን ሥራ ሰርቻለሁ› በማለት ረክቶ በተመለሰ ነበር። ግና ሳይረካ እሰራለሁ ሲል ነው ያለፈው። ይህ ነው ለሁላችንም እንደእሳትና እንደረመጥ እያቃጠለን ያለው። ለማንኛውም ይህን ሕዝቡም፣ ወጣቱም እየገለፀው ነው፡፡ ኢህአዴግም የመንግሥት አመራሩም ኀዘን ከዚህ የተለየ አይደለም። ይህንን ሕዝብ ይዞ የመለስን ራዕይ ከዳር ለማድረስ ይቻላል። እናም በቁርጠኝነት ታጥቀን መነሳት አለብን፤ ሕዝባችንን አሰልፈን። መለስን የሚተካ አንድም ሰው ባይኖርም ቢያንስ እንደ ድርጅትና እንደመንግሥት ኃይላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ ኢህአዴግ ብዙ ፈተናዎች ደርሰውበት አዝኖ ኀዘኑንም ተቋቁሟል። እንደዚህ አይነት ከባድ ነገር ገጥሞት ባያውቅም የተለያዩ የህልውና የመኖርና ያለመኖር ፈተናዎች ገጥመውታል፡፡ ይህንንም ችግር ከሕዝቡ ጋር ሆነን እንወጣዋለን የሚል እምነት አለን። የእኔም እምነት ይሄ ነው።
ዘመን፦ አቶ መለስ የትግል አጋርዎ ናቸው፡፡ ለእርሳቸው የበለጠ ቀረቤታ ይኖርዎታል ብዬም አስባለሁ። በትግሉ ጊዜ ከነበራችሁ አንዳንድ ትውስታዎች ሊነግሩኝ ይችላሉ?
አምባሳደር ስዩም፦ የመለስ ራዕይ የሕዝብ ፍቅር ነው፡፡ይህም በቁርጠኝነት ተግባር ላይ እንዲውል ድርጅቱንና ሕዝቡን መርቶ ወደ ተግባር የመግባቱን ጉዳይ በስፋት የሚያውቅ ነው። እንዳልከው ቢያንስ ለአርባ አመታት አብረን ነበርን። ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ጋር በወጣትነት እድሜዬ በ 1964 ዓ.ም ክረምት ላይ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኘነው። ያኔ እርሱ የዊንጌት ትምህርቱን ጨርሶ በ1965 ዓ.ም ዩኒቨርስቲ ለመግባት ይጠባበቅ ነበር፡፡ በወቅቱ በነበረው የተማሪ ንቅናቄ ምክንያት ከመጀመሪያው ሴሚስተር በኋላ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተዘግቶ ስለነበር የዩኒቨርሲቲ ተማሪው ሁሉም በተደራጀ መልክ በወቅቱ በየጠቅላይ ግዛቱ ሄዶ ሕዝቡን እንዲያነሳሳና ከሕዝቡ ጋር የሚያገናኙት አንዳንድ ነገሮችን ይዞ ተንቀሳቅሷል፡፡ በእንቅስቃሴው ውስጥም አመራር ነበር፡፡
አድዋ ላይ እንደዚሁ ከትግራይ የተውጣጣ ቡድን በየጠቅላይ ግዛቱ አውራጃዎች ርዕሰ ከተሞች ይንቀሳቀስ ስለነበር የቅርጫትና የእጅ ኳስ ጨዋታ አለን በሚል ከአዲግራትና ከመቀሌ ተወጣጥተን አድዋ ንግሥት ሳባ ድረስ በሄድንበት ጊዜ አቶ መለስም እዛው ከነበሩት የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር አብሮ ስለነበር እዚያ ተገናኝተናል፡፡እና ከእዚያ ጊዜ ጀምሮ ነው የምንተዋወቀው። በ65 ዓ.ም ነው አቶ መለስ ዩኒቨርሲቲ የገባው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የተማሪውን እንቅስቃሴ መሰረት ያደረገ የትግራይ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበር ነበር። ይህ የተቋቋመው ማህበር የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማህበር ጋር በተጓዳኝ ይንቀሳቀስ ነበር፡፡ አቶ መለስ ያኔ ከሁላችንም ያነሰ ወጣት ነበር፡፡ ነገር ግን ጥናታዊ ጽሁፎችን በማቅረብና ውይይቶችን በመምራት በኩል የጎላ ሚና ነበረው። በተለይ በ1966 ዓ.ም የአገሪቱ አጠቃላይና አብዮታዊ እንቅስቃሴ ከዳር እስከ ዳር እየተቀጣጠለ የመጣበት ሁኔታ ነበር። ያኔም አቶ መለስ ከሳይንስ ፋኩልቲ ተመርጦ የተማሪዎች መማክርት አመራር ውስጥ ተካቶ ነበር። በእንዲህ ያለ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው እንግዲህ በቅርብ ልንተዋወቅ የቻልነው፡፡ አቶ መለስ ያን ጊዜ ወጣትና ከሁላችንም ያነሰ ቢሆንም ብልህና አስተዋይ ነበር።በሳልና ብዙ አስተዋፅኦ ያበረከተ ሰው ነው፡፡ እንግዲህ በኋላም ደርግ የሕዝቡን አመፅ አኮላሽቶ ወታደራዊ አገዛዙን አውጆ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የትግራይ ተራማጆች ብሔራዊ ንቅናቄ ህቡዕ ድርጅት ትግሉን አጠናክሮ ቀጠለ፡፡እርሱም በአመራሩ ውስጥ ባይኖርም ያኔም በንቅናቄው ውስጥ ከታቀፉትና ከፍተኛ ሚና ከነበራቸው ታጋዮች አንዱ ነበር።የደርግ አካሄድ እጅግ አስከፊና ሁለትና ሶስት ሆኖ በጋራ መምከር የማይቻልበት ሁኔታ ነበር፡፡ በወቅቱም ፋሽስታዊው ደርግ የጭካኔ አዋጅ በማወጁ ሠላማዊ ትግል የሚባል ነገር የሚቻል አልነበረም። በእዚህም የትጥቅ ትግሉን መጀመር አለብን ብሎ የትግራይ ተራማጆች ብሔራዊ ንቅናቄ ውሳኔ ሲያስተላልፍ አቶ መለስም ከዩኒቨርሲቲ ወጥቶ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ከሚዘጋጁት አንዱ ነበር። እርሱ መጀመሪያ በጥር ወር 1967 ዓ.ም ወደ ኤርትራ ለስልጠና ከተላኩት ጥቂት የዩኒቨርስቲ ተማሪ ታጋዮች ውስጥ አንዱ ነበር።ወታደራዊ ስልጠናውን ሳይጨርስ እርሱና አቶ አባይ ተመልሰው ወደ ፖለቲካ ስራ እንዲገቡና የትግሉን አቅጣጫ በሰነድና በማኒፌስቶ መልክ እንዲያዘጋጁ የቤት ስራ ስለተሰጣቸው በትግራይ ከተሞች በአክሱምና በአድዋ ተደብቀው ይህንን እንዲያዘጋጁ መመሪያ ተሰጥቷቸው ሲያዘጋጁ ቆይተዋል።
በመጨረሻም በ1967 ዓ.ም ደደቢት ወደነበረውና እዚያ ወደተሰማራው ኃይል ተቀላቅሏል።ስለዚህ በእዚህ ሁሉ የአቶ መለስ ሚና የጎላ ነበር። በተለይ ትግሉን የሚፈታተኑ ሁኔታዎች በሚያጋጥሙ ጊዜ የችግሩን ባህሪ፣ መውጪያና መፍትሄውን አሳማኝ በሆኑ መንገዶች ጥናቶችን አጥንቶ በማቅረብ ድርጅቱንና የድርጅቱን ህልውና በማስጠበቅ ድርጅቱ ሕዝባዊ እንዲሆን አድርጓል፡፡ የትግራይ ሕዝብን ብሔራዊ ትግል ከኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦች መደባዊ ትግል ጋር እንዴት ይቀናጃል? የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች እንዴት ይሰባሰቡ? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳትና የጠራ መስመር በማቅረብ የጎላና ተኪ የሌለው ሚና ሲጫወት ቆይቷል።እነዚህን ጉዳዮች ሁሉም የሚያውቃቸው ናቸው፡፡ ምናልባት ጠቃሚ መስሎ የሚታየኝ ባህሪያቸው ምን አይነት ነበር የሚለው ነው፡፡
ዘመን፦ አዎ! ስብዕናቸው ምን ይመስል ነበር?
አምባሳደር ስዩም፦ ከመጠን በላይ ሩህሩህ ነው። ወገን፣ደም አይለይም፡፡ የተጨነቀ፣ የተቸገረ ሲያይ እንባው ነው የሚቀድመው፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ አይደለም፣ የሁሉንም ህዝብ ታሪክ ያነባል፡፡ የታጋይና የጭቁን ሕዝቦችን ታሪክ ያነባል። ችግራቸውን እንዴት እንዳለፉት ያጤናል።ሁሉም ሕዝብ ፍጡር ነው፣ ሰው ነው ብሎ ያምናል።ሰውን በጣም ያከብራል። ሰው ሁሉ እኩል ነው የሚል የፀና አቋም አለው። እያንዳንዱ ሰው ሚና አለው ብሎም ያምናል። ሁሉም የራሱ ሚና አለውና ያን ሚና ይዞ ሲመጣ ውጤት ይመጣል ይላል። ያበረታታል። ሚናውን ይበልጥ የሚያጎለብትበትን መንገድ ያሳያል፡፡
መለስ የጎላ የሰው ፍቅር አለው። መለስን ቀርቦ ለሚያየው ከእርሱ ብዙ እንደሚማር ያውቃል። ሰብአዊ ርህራሄ የነበረው ሰው ነው። ሲያዝንም ያለቅሳል፣ ሲደሰትም፣ ሲቀልድም እንባውን ያፈሳል፤ ከልቡ። ለይምሰል ብሎ ሳቅ አይስቅም። የመለስ ንግግሮች ከሕዝቡ ኑሮና ከሕዝቡ ትግል የተለዩ አይደሉም። መለስ ሲስቅ ጥርሱን ገልጦና ከልቡ ነው፡፡ ሰው ምን ይለኛል አይልም፡፡ይቀልዳል፣ ይጫወታል፣ ሰውን ይቀርባል፡፡ይህ የአቶ መለስ ባህሪ ነው። መለስ ከትምህርት፣ ከጥናት፣ ከንባብ ተለይቶ አያውቅም።
በአጠቃላይ ለእውቀት ብቻ ብሎ አያነብም፡፡ ጥያቄ ይጠይቃል፡፡ ለጥያቄዎች መፍትሄ ፍለጋም ነው የሚያነበው። የሕዝብ ጥያቄዎች ሲሆኑ አንብቤ መልስ አገኝበታለሁ ይላል። ጽሑፎቹ ወታደራዊ ጥበብና ሳይንስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በሁሉም ዘርፎች ፈጣን ጥያቄዎች ሲነሱ መልስ አገኝበታለሁ ብሎ ይንቀሳቀሳል። ከተግባር ይማራል፣ ከመጽሐፍት ይማራል።ይህን ከማድረግ ወደ ኋላ ብሎ አያውቅም፡፡ ሌሎችንም ያስተምራል።ያወቀውን ሁሉ ያካፍላል፤ያጋራል።ይሄ የእኔ ነውና አንብቡ ብሎ አያውቅም፡፡ የሰራውን ስራ እዩልኝ፣ ይሄ የእኔ ውጤት ነው፣ይህን ሰርቻለሁ ብሎ አይኩራራም፡፡መታወቅን አይፈልግም። ይሄ ጎድሎኛ፤ ይህን ስጡኝ፣ ይሄ ያስፈልገኛልና ይሄን አድርጉልኝም ብሎ አያውቅም።
አባቱ አቶ ዜናዊ የነገሩኝን ታሪክ ልንገርህ፡፡ ጀነራል ዊንጌት ፈተና አልፈሃል ተብሎ አባቱ ከአድዋ በአውቶቡስ ይዘውት ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ወልዲያ ያድራሉ። ምሽት ወልድያ እራት እየበሉ« ምን ትጠጣለህ?» ይሉታል፡፡ «ውሃ» ይላል። ልብ በል ያኔ ገና ወጣት ነው። ስምንተኛ ክፍልን ጨርሶ ወደ ዘጠነኛ ክፍል አልፎ ነው ጀነራል ዊንጌት ይሄድ የነበረው። ያን ዕለት ታዲያ አባቱ አቶ ዜናዊ«ኮካኮላ ጠጣ» ይሉታል፡፡ «የለም ውሃ ነው የምጠጣው» ይላል፡፡ አባትየውም «ለምን? ገንዘብ የለውም ብለህ ነው? ችግርኮ የለም መጠጣት ትችላለህ» ይሉታል፡፡ በኋላ «አይ ከሆነስ እሺ» ብሎ ጠጣ ብለውኛል፡፡ አየህ አባቱንም፣ ቤተሰቡንም ማስቸገር አይፈልግም። ርቦኛል፣ ያስፈልገኛል፣ ይህን አድርጉልኝ፣ ይህን ግዙልኝ አይልም። ኮካኮላ በወቅቱ 25 ሳንቲም ነበር ግን ሊያስቸግር አልፈለገም።
ሌላ ከማስታውሰው ምን ያህል ለሰው ያስባል? ለቆመለት ዓላማስ ምን ያህል የፀና ነው? የሚለውን አንድ ነገር ላንሳልህ። የትጥቅ ትግሉ በ1967 ዓ.ም በተጀመረበት ወቅት ክረምት ሐምሌና ነሐሴ ላይ ዝናቡ ከፍተኛ ነበር፡፡ያኔ እንግዲህ ቤት ወይም መንደር ገብተህ አታድርም፡፡ ራስህን ደብቀህ በረሃ ነው የምትንቀሳቀሰው፡፡ ድርጅቱም ጥቂት የነበሩት ታጋዮችም ራሳቸውን ደብቀውና ሰው ካለበት ርቀው ራሳቸውን በማደራጀት ላይ ነበሩ፡፡ እና ጠላት ታጋዮቹም ገና ሳይበራከቱና ወደሌላ ሳይሻገሩ፣ትግሉን በእንጭጩ መቅጨት አለብን በሚል ነጭለባሾችንና ሰላዮቹን ያሰማራበት ጊዜ ስለነበር በጣም ፈታኝ ወቅት ነበር፡፡ ይሄ የመጀመሪያው የትግሉ ዓመት ነበር። በዚህ ፈታኝ ወቅት አቶ መለስ የታይፎይድ በሽታ ይታመማል። ታይፎይድ መሆኑን ያወቅነው በኋላ ላይ ነው። በጣም ከፍተኛ አደጋ ላይ ደርሶ ነበር። ሕይወቱንም እስከ ማጣት የደረሰበት ሁኔታ ነበር የተፈጠረው፡፡ያኔ እንግዲህ በዋልክበት አታድርም፣ እራት በበላህበት አታመሽም፣አታድርም፡፡ ቀንም ሌሊትም ጉዞ ላይ ነህ። በጊዜው እንደ መለስ ሁሉ በወባም፣ በተስቦም የታመሙ ሌሎች ታጋዮች ነበሩና እንቅስቃሴያችን ተገድቦ ነበር፡፡ የማስታውሰው አንድ በቅሎ ነበረን፤ ስንቅ ምናምን የሚያመላልስ፡፡ ከሁሉም በጠና ታሞ የነበረው አቶ መለስ ስለነበረ በዛ በቅሎ ላይ ብቻውን ተቀምጦ መጓዝ ስለማይችል ሰው ደግፎት ጉዞ ጀመርን፡፡ ጉዞው ደግሞ በጨለማ ነው፡፡ በወቅቱ እንቅስቃሴያችን ድብቅና የተገደበ ነው፡፡ ምክንያቱም ታጋዮች ገና የሚረባ ትጥቅ እንኳ ያልታጠቁበትና ያልተጠናከሩበት ጊዜ ነውና ‹እኔን ሲጎትቱ እዚህ አካባቢ ነው ያሉት የሚል ወሬ ለጠላት ከደረሰ አደጋ ላይ እጥላቸዋለሁ፤ የእነርሱንም ሕይወት ለአደጋ እዳርጋለሁ። እነርሱ ደግሞ አደጋ ላይ ከወደቁ ትግሉ በእንጭጩ ይቆማል› የሚል ስጋት አድሮበት ታጋዮቹ ባረፉበት ምዕራብ ትግራይ ቆላማ፣ተራራማና ገደላማ አካባቢ ነበር ‹ሕይወቴን ባጠፋ የእነርሱን ሕይወት አድናለሁ› ብሎ ያሰበው። ‹የእኔ ሕይወት ቶሎ ቢያልፍ ይሻላል፣ እኔን ሲጎትቱና እኔን ሲሉ አደጋ ላይ ይወድቃሉ፣ ለእኔ ሲሉ ያልሆነ ቦታ እያደሩና እየዋሉ ነው፣ እኔ ከሞትኩ ግን እንደልባቸው መንቀሳቀስ ይችላሉ› ብሎ አስቦ ኖሮ ታጋዮቹ ካረፉበት ቦታ ተንፏቆ ገደል አፋፍ ሊደርስ ሲል አዩት። ገደል ገብቶ ራሱን ሊያጠፋ ነበር ግን ያዙት። በእዚህ ጊዜ እርሱም ያለቅሳል፣ ታጋዮቹም ተላቅሰው ደግፈውት ጉዞው ቀጠለ፡፡ በኋላ ግን ነገሩ ጥሩ ሆነ፡፡ ከከተማና ከድርጅት መድሃኒት ተላኩልንና ከተወሰኑ ሳምንታት በኋላ ዳነ። መጨረሻ ላይ የነበረውን ሁኔታ ሲያጫውተን ተስፋ መቁረጥ ሳይሆን ለሌሎች ታጋዮች ሕይወት ሳስቶ የራሱን ሕይወት ለማጥፋት ወስኖ እንደነበር ነገረን፡፡ የእነርሱ ህይወት ከጠፋ የትግሉ ጉዞ ይሰናከላል፣ በእንጭጩ ይቀጫል ብሎ ስላሰበ ነው። እንዲህ አይነት ሰው ነው መለስ። እና እነዚህ ባህሪዎቹ ብዙም የሚታወቁ አይደሉም። አቶ መለስ ሰው አይለይም፡፡ በጣም በጣም አሳቢ ነው፡፡ አዛኝ ነው። ስስ ነው፤ ለሰው። ለሕዝቡና ለአገሩ የላቀ ስሜት አለው፡፡ አገር ሲባል ሕዝብ ነው፡፡ ከሕዝብ ውጪ የሚታይ ነገር የለም ብሎ የሚያስብ ሰው ነው መለስ።
ዘመን፦ ከእርስዎ ጋር በነበራችሁ ቀረቤታ ሌላሰ የሚያስታውሱት የተለየ ነገር ይኖራል?
አምባሳደር ስዩም፦ በሥራ፣ በትግል፣ በመንግሥት ኃላፊነትም አብረን ቆይተናል። ሳንገናኝ የቀረንበትን ቀን መቁጠሩ ይሻላል። አብረን ሰርተናል። የሚያየውን ጉድለት አይደብቅም።ጉድለትህን እንድትማርበት ነው የሚያነሳው፡፡ እርሱንም ጉድለት አለብህ ካልከውና በትክክል ጉድለቱን ከጠቆምከው ከመቀበል ወደኋላ አይልም። ጉድለቱን አይቶ ይቀበላል፣ ይማራል፣ ሰውንም ያስተምራል። ጉድለትህን ይነግርሃል፣ ያስተምርሃል። ይህን የሚያደርገው እንድትታነፅበት ነው። ኢህአዴግ መለስን አንጿል፣ መለስም ኢህአዴግን አንጿል። ገንብቷል። እኛ የምናየው በመለስ እይታና በመለስ ራዕይ፣ በመለስ መስመር፣ በመለስ ፖሊሲ የታነፁ ግድቦችን፣ መንገዶችን፣ የመሰረተ ልማት አውታሮችን፣ የኢኮኖሚ ልማትንና እነዚህን ነው፡፡ ጎልተው በተጨባጭ የሚታዩት እነዚህ ናቸው።መለስ ያነፀውና የማይጠፋው ነገር ካለ የሕዝቡ አስተሳሰብ ነው፡፡ ሀብትም የሚፈጥረው፣ ትራንስፎርሜሽን የሚያመጣውና የመጪውንም ትውልድ የሚወስነው ይሄ ነው። በሕዝቡ ውስጥ ያለው አስተሳሰብ ምን አንጿል? የሚለውን ነው መለስ የሚያየው፡፡ ድህነትን እናሸንፋለን። ሥራ ክቡር ነው። ሳይሰሩ መብላት ሀጢያት ነው። ሙስናን፣ ኪራይ ሰብሳቢነትን የሚያወግዝና ይህም የልማት፣ የትውልድ፣ የትንሳኤያችንና የሕዳሴያችን ነቀርሳ መሆኑን በወጣቱም ሆነ በሁሉም ዘንድ እንዲሰርጽ አድርጓል። በድርጅቱ ቁርጠኝነትን፣ የሕዝብ አገልጋይ መሆንን፣ የራስን ጥቅም ከሕዝብ ጥቅም፣ ልማትና እድገት ጋር የማስተሳሰርን አስተሳሰብ በታጋዩ፣ በደጋፊው፣በሕዝቡ ውስጥ ሰርጾ እንዲገባ ማድረግ ችሏል፡፡ ዋስትናችን ይሄ ነው በእዚህ አስተሳሰብ እንቀጥላለን ብሎ ሕዝቡ ይሄንን ስላመነበት ነው የተቀበለው። ለምንድን ነው ሕዝቡ በመለስ ህልፈት እንደዚህ አንጀቱ ያረረውና የተቃጠለው?
ዘመን፦ አዎ እርሱን ላነሳልዎት ነበር፡፡ አሁን ሕዝቡ በጣም በሚያስደንቅ ሁኔታ ነው ኀዘኑን እየገለፀ ያለው፡፡ ይሄ ከምን የመነጨ ነው ይላሉ?
አምባሳደር ስዩም፦ ይሄ ምንን ያሳያል? ይሄን ሀሳብና ራዕይ ያመነጨ፣ወደ ተግባር ያሸጋገረው መሪ ጠፋብኝ፤ ይሄን ያስታጠቀኝን መሪዬን አጣሁት፡፡ አከብርሃለሁ፡፡ ምክንያቱም አንተ የሰጠኸኝን ይዤ ተጠቃሚ ሆኛለሁ ነው ሕዝቡ የሚለው።ወጣቱም ሥራ አልባ ነበርኩ፣ ጨልሞብኝ ነበር፣ የብርሃን መንገድ አግኝቼ መንቀሳቀስ ጀምሬያለሁ። ዳር ላይ ሳታደርሰኝ ሄድክብኝ እያለ ነው። ይሄን መገንባቱ ነው ዋስትናችን የሚሆነው። ትልቁ ያገኘነው ሀብትም ይሄ ነው። የተገነቡት ተገንብተዋል፡፡ የሚገነቡትን እንገነባለን፡፡ የመሰረተ ልማት አውታሮችን እንቀጥልባቸዋለን፣ ወደ ኋላ የሚመለሱ አይደሉም፡፡ ግን ከእዚህም በላይ አማትረው የሚሄዱና ብዙ ራዕይን መሰረት ያደረጉ የሰነቅናቸው አመለካከቶች አሉ። መለስ ሁል ጊዜ እነዚህ አመለካከቶች፣እነዚህ የልማት፣ የዴሞክራሲ፣ የሰብአዊና የእኩልነት መብቶች በሕዝቡ አስተሳሰብ ውስጥ ከነገሱ ኢህአዴግ ቢኖርም ባይኖርም ችግር የለውም ይል ነበር፡፡ አሁን ሕዝቡ እነዚህን አስተሳሰቦች የእኔ ናቸው ብሎ አቅፎ ይዟቸዋል። ይህንን ነው መለስ ያነፀው፡፡ይሄም አይመክንም፡፡
ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሸጋገራል። መለስ ሁል ጊዜ የእኛ ትግል የማራቶን እሩጫ አይደለም ይል ነበር። አንድ ሰው ብቻውን ሮጦ የሚጨርሰው የማራቶን ሩጫ አይደለም። የዱላ ቅብብሎሽ ነው፡፡ ትውልዶች የሚቀባበሉት ነው። አንድ ትውልድ አንድ ቦታ ላይ ያደርሳል። በአንድ ወቅት የተጀመረ የሕዝብ ትግል ስለማያቋርጥ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ነው የሚሄደው፡፡ እንደ ዱላ ቅብብሎሽ ነው ይዘነው የምንጓዘው ይል ነበር።መለስ ይህን ዱላ ተቀባይ ወጣት ፈጥሯል። ሴቱን፣ ወንዱን፣ ወጣቱን፣ አዛውንቱን፣ሁሉንም በእዚህ አስተሳሰብ አንፀነዋልና ዋስትናችን ይሄ ነው። ይሄ ደግሞ የመለስ ራዕይ ነው።ይሄ የመለስ አስተዋጽኦ ነው።ተኪ የሌለው አስተዋፅኦ ነው።ውጤት ነው። ለዚህ ነው መለስ በስጋ ቢለየንም በስራውና በያዝነው አመለካከት ሁልጊዜም አብሮን ይኖራል፡፡ መጪው ትውልድም አብሮት ይኖራል የምንለው። ሕዝቡም ይህን ጥልቅ ግንዛቤ በሚገባ ተረድቶታል ብዬ አምናለሁ።
ዘመን፦ቀጣዩ የኢትዮጵያ አመራር፣ ሕዝቡም ኀዘኑን ረስቶ ጠንክሮ ወደ ሥራ በመግባቱ ረገድ ምንድን ነው የሚጠበቅበት፤ በተለይ አመራሩ?
አምባሳደር ስዩም፦ በታሪክ አንዳንዴ የሚወሳ ነገር አለ። አዲሲቷ የቻይና ሕዝባዊት ሪፐብሊክ በፈረንጆች አቆጣጠር በ1949 ዓ.ም ነው የተመሰረተችው። በቻይና አብዮት የሕዝብ ትግል ከሚታወቁት መሪዎች አንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቹ ዬን ላ ናቸው። በ1976 ዓ.ም በፈረንጆች አቆጣጠር ነው ድንገት ያረፉት።በድንገተኛ አደጋ ነው የሞቱት። የእዚች አገር ታሪክ አሁን ያለውን የኢትዮጵያን ሁኔታ የሚያሳይ ነገር ነው ተፅፎ የምታገኘው። አሁን በሕይወት ያሉ ታሪኩን የሚያውቁት ሲናገሩ በወቅቱ አገሪቷን በሙሉ ሽባ ያደረገ ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር ነው የሚሉት፤ በእርሳቸው ሞት። ከእርሳቸው ሞት በኋላ ሕዝቡ በጣም ደንግጧል። አሁን የምታየው የኢትዮጵያ አይነት ሕዝቡ መንገድ ወጥቶ በማልቀስና በማዘን ወደ ሥራ መንቀሳቀስ የተሳነው ጊዜ እንደነበረ ነው የሚነገረው፡፡ ከሐዘኑ ለማገገም የወራት ያህል ጊዜ ወስዶባቸዋል። በሐዘን ምክንያት ሁኔታው የጨለመበት ነበር። በኋላም የማኦ ዘይቱንግ ሞት ተከተለ፡፡ እና በወቅቱ በአገሪቱ ያልተረጋጋ ሁኔታ ነበር ተፈጥሮ የነበረው።እኛ ዛሬ ከእዚህ መማር አለብን እላለሁ። እያዘንን ወደ ሥራ መግባት ነው ያለብን። ሀዘናችንን በሥራ ነው መግለፅ ያለብን። እየሰራን ነው መለስን ህያው አድርገን እርሱነቱ እንዲቀጥል የምናደርገው። እያዘንን ወደ ሥራ በመግባት ሀዘናችንን በሥራ ነው መግለጽ የሚገባን፡፡በእዚህ አይነት ሁኔታ ነው መለስን ህያው የምናደርገው፡፡ እርሱ የፈጠረልንን ሥራ፣ እርሱ የሰጠንን ራዕይ ይዘን የእርሱ ፍላጎት የነበረውንና የእኛንም ጥቅም የምናረጋግጥበትን ይህን ራዕይ አጠናክረን መቀጠል አለብን። ኀዘናችን ከልባችን እስኪወጣ ድረስ ጊዜ ሊወስድብን ይችላል። ሀዘናችን ጥልቅ ነው፡፡ ግን ይህን ተሸክመን በሥራ ነው መግለፅ ያለብን፡፡ መለስን በሥራ ህያው እናድርገው የሚለው ነገር አሁን የወጣቱና የአዛውንቱ ቋንቋና አስተሳሰብ ሆኗል። ቀና ደፋ እያሉና አካፋና ዶማ ይዘው እየቆፈሩ ግድቡን እየገደቡ ነው ሐዘናቸውን እየገለፁ ያሉት፡፡ ሥራ አቁመን አይደለም ማዘን ያለብን፡፡የእኛ ትልቁ መልዕክት ይህን አገሪቱ የጀመረቻቸውን ጅምሮች በዚሁ አጠናክሮ መቀጠል ነው የሚያስፈልገው፡፡ እኛ የሞት ሞት የምንሞተው ሀዘናችን ከስራ ውጪ ካደረገን ነው። በቃ መለስ አልፏል።ሁልጊዜ እናከብረዋለን፣ እንወደዋለን፡፡ ግን የእኛ ክብርና ፍቅር የሚገለፀው በስራ መሆን አለበት የሚለውን በትክክል መረዳት ያስፈልጋል፡፡
ዘመን፦አመራሩ በቀጣይ የእርሳቸውን ፈለግ ተከትሎ እንዴት ነው በጥንካሬና በብስለት መጓዝ ያለበት?
አምባሳደር ሰዩም፦ እንግዲህ ከዚህ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም፡፡ ሌሎች አማራጮች፣ አማራጮች አይደሉም፡፡ ህዝቡን በበሳል መስመር መምራት የተቀመጠለት መስመር ነው፡፡ አዲስ መስመር ፍለጋ ላይ አይገባም፡፡ ይህን መስመር እንዴት ተግባራዊ ላድርግ ብሎና በቁርጠኝነት ለእዚህ የሚያበቃውን አደረጃጀት አጠናክሮ እንዲሁም የተፈጠረውን የህዝብ ማዕበል ይዞ መቀጠል አለበት። ህገ መንግስታችንን በመጠበቅ የድርጅቱን መመሪያዎችና ህጎች መሰረት ያደረጉ ተቋማትን ነው መገንባት ያለብን።መለስን አንድም ሰው ባይተካውም የመንግስትና የድርጅቱ አመራርና የህዝቡ እንቅስቃሴ እንዴት ተቀጣጥሎ ይሂድ የሚለውን ማየት አለበት፡፡
ከዚህ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም፡፡ ወደ ኋላ፣ ወደ ግራ፣ ወደ ቀኝ የሚባልበት መንገድ የለም። የአገራችንና የህዝባችን መፃኢ እድል ብሩህ ነው። በጣም ብሩህ ነው።እንዲህ አይነት ለለውጥ፣ ለትራንስፎርሜሽን፣ ለስራ የተነሳሳ የህዝብ ማዕበል ከሁሉም የሚበልጥ ሀብትና ፀጋ ነው። በዴሞክራሲ፣ በልማት፣ በመልካም አስተዳደር ዙሪያ የህዝቡን ይሁንታ ያገኘ አገር በታሪክ አጋጣሚ ጥቂት ነው። ይህን እድል አግኝተናል።ሁሉንም ሀብትና ጥበብ የሚያስጨብጠንና የሚፈጥርልን ይሄው ነው፡፡ በዚህ ይሁንታ እንዴት አድርገን ነው ህዝቡም አመራሩም በጋራ ተሳስሮ የሚሄደው የሚለውን ያያል ብዬ አምናለሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም።
ዘመን፦ በዚህ ሁኔታ በቀጣይ የአቶ መለስ ራዕይ ይሳካል፣ ኢትዮጵያም ታላቅ አገርና ህዝብ ትሆናለች ብለው ያምናሉ?
አምባሳደር ስዩም፦ አልጠራጠርም። ወደ ኋላ የምንመለስበት ምንም ምክንያት የለም። ሁሉም ዕድል አለን፡፡ እንኳን አሁን ይሔን የፈነጠቀውን ብርሀንና ውጤት እያየ ይቅርና ህዝቡ በተስፋ ድርጅቱንና አመራሩን አምኖ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል።አሁን የራሱም አድርጎ ይዞታል፡፡ ወደኋላ የሚመለስበት ምክንያት የለም።
ዘመን፦ ይህን ያነሳሁብዎት አንዳንድ ወገኖች ከአቶ መለስ ህልፈት በኋላ የፖሊሲ ለውጥ ሊመጣ ይችላል፤ለውጦች ሊኖሩ ይችላሉ የሚሉ ሃሳቦችን እያነሱ ስለሚገኙ ነው፤
አምባሳደር ስዩም፦ የጥፋት መንገድ ዕድል የለውም። ህዝባችን ተገቢ ጥርጣሬዎች ሊኖሩት ይችላሉ። መነሳት ያለባቸውን ጥያቄዎች ቢያነሳ ተገቢ ነው። መለስን የሚተካ ሰው ይገኛል? አይገኝም። የዘመናችን ትውልድ የሚያፈራቸው በጣም ጥቂት በጣት የሚቆጠሩ በዓለም ነበሩ የሚባሉ ካሉ አንዱ መለስ ነው። እንደዚህ ያሉ ሰዎች ደግሞ በታሪክ አጋጣሚ ጥቂቶች ናቸው፤ ባለንበት ዘመን፡፡ እነዚህ ሁሉም መሬት ላይ ያሉ ትውልዶች ያፈሩት የዘመናችን ብልህና አዋቂ፣ ለህዝብ አመራር የሰጠ ታላቅ መሪ ነው መለስ። እርሱ የአፍሪካም መሪ ነው፡፡ በዓለም አመራር ሲሰጡ ከነበሩት ጥቂት ከሚከበሩና አንቱ ከሚባሉ መሪዎች መካከል አንዱ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የዚህ ባለቤት በመሆኗ ትኮራበታለች፤ ከህይወት ህልፈቱም በኋላ። እንደነዚህ አይነት ሰዎች በፈለግህበት ደረጃ የሚገኙ አይደሉም። አቶ መለስ ግን እንዲህ አይነት ሰው ቢሆንም ከድርጅቱ ውጪ ማናቸውንም ሚና መጫወት የቻለበት ሁኔታ የለም፡፡ በእርግጥ እርሱ ድርጅቱን፣ መንግስትንና ህዝቡን አንጿል። ህዝቡ፣ መንግስትና ድርጅቱም አቶ መለስን አንፀዋል። ይሔ ተሳስሮ ነው የሚሄደው።እና አመራሩና ህዝቡ አንድ ላይ በዚህ በተፈጠረው ሁኔታ አብሮ በሚሄድበት ጊዜ የሚጎድለውን እየተካ መጓዝ አለበት።ብዙ መለሶች ወደ ፊት ይወጣሉ ብለን በዚህ አስተሳሰብ ነው መሄድ ያለብን ብዬ አምናለሁ።
ዘመን፦ እንዳው በእርሶዎ ዕይታ አቶ መለስን ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ይኖራል?
አምባሳደር ስዩም፦ እኔ ይሄንን በአንድ ቋንቋ ብገልፀው ይሻላል። አቶ መለስን መለስ ያደረገው ባለራዕይና ራዕዩን ተግባራዊ ለማድረግ በቁርጠኝነት የሚንቀሳቀስ መሆኑ ነው።ይህን ራዕይ ደግሞ ራዕይ ብሎ የሚያየው ህዝቡን እስከጠቀመና የህዝብ ነው ብሎ እስካመነ ድረስ ብቻ ነው። አንዳንድ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ህዝባዊ ፍቅር ይዞ ራዕዩን በፈለገው መንገድ ለመተግበር የሚያቅተው ሰው አለ። አቶ መለስ ብቻ ነው ጥልቅ የህዝብ ፍቅር ያለው ማለትም አይደለም፡፡ ግን ጥልቅ የህዝብ ፍቅር ኖሮት፣ የአመራር ብቃትንና የህዝብን ፍቅር መሰረት አድርጎ ህዝቡን በልማት፣ በዴሞክራሲ፣ በፍትህና በመልካም አስተዳደር መርቶ መሄድ ላይ አቅሙ የማይኖረው ብዙ ሰው ነው ያለው፡፡ ጥልቅ የህዝብ ፍቅርን መነሻ በማድረግ ግን መለስ ባለ ራዕይ ነው፡፡ ራዕዩንም ወደ ተግባር የማሸጋገርና ሌሎችንም አደራጅቶ የመምራት ብቃት ነበረው፡፡ ይሔ የመለስ ባህሪ ነው፡፡
ዘመን፦ በህይወት ዘመናቸው ይመኙትና ይፈልጉት የነበረው ምን ነበር?
አምባሳደር ስዩም፦ አስታውሳለሁ በመጀመሪያ ጊዜ የሽግግር መንግሥት ፕሬዝደንት በነበረበት ወቅት አብረን ዋሽንግተንን ጐብኝተን ነበር። በዚያን ወቅት አንዲት ኢትዮጵያዊት በሚቀጥለው አስር አመት ለኢትዮጵያ ያልዎት ራዕይ ምንድን ነው? ብላ ጠየቀችው፡፡ የምመኘው በሚቀጥሉት አስር አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በቀን ሦስት ጊዜ እንዲበላ ነው ብሏል፡፡ የመለስ ራዕይ ድህነትን ማሸነፍ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከገባበት ውርደትና አንገቱን ካሰበረው ችግር እንዲላቀቅ ማድረግ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ ብሔሮችና ብሔረሰቦች እፁብ ድንቅ የሚባል ባህልና ስልጣኔ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በሃይማኖትም ተባብሮና ተቻችሎ፣ አገር ገንብቶ የኖረ ሕዝብ ነው፤ ለብዙ ትውልዶችና ዘመናት፡፡ ነገር ግን የእነዚህ እሴት ባለቤት ሆኖም ግን አንገቱን ሰብሮና ሀፍረት ተከናንቦ የድህነት፣ የጦርነት፣ የልመናና የረሀብ ተምሳሌት ሆኖ ነው የኖረው፡፡ አገር ለቆ ወይንም ለቃ ስደት ሄዶ ወይንም ሄዳ አሜሪካ የገባ ልጅ ወይንም የገባች ልጅ ያለው ቤተሰብ እንደ ትልቅ ፀጋ የሚያይበት፡፡ልጄ ተለየኝ ወይንም ተለየችኝ ብሎ ሳይሆን ልጄ አሜሪካ ገባ ወይንም ገባች የሚል፡፡የክረምት ጐርፍና ወንዝ ሞልቶ ለያይቶት ሲከርም መቼ ነው የሚያባራልኝ ብሎ ናፍቆቱን መወጣት አቅቶት የሚጨነቅ ሕዝብ፡፡ ባህር ማዶ ተለይተውት የሄዱ ልጆቹን የሀብትና የኑሮ ምንጭ አድርጎ የሚያይበት ሁኔታ ነበር የተፈጠረው። ህፃናት ተወልደው ምን ትፈልጋለህ ? ሲባሉ አሜሪካ መሔድ እፈልጋለሁ ነው የሚሉት፡፡ አገሬን አስከብሬ እኖራለሁ አይደለም መልሳቸው። ከእዚህ የባሰ ውርደት የለም፡፡ ስደትን እንደክብር የሚያይ ሕዝብ ነበር፡፡ መለስ ታዲያ ለዚህ ውርደት የዳረገን ድህነት ነው። የሰላም፣ የመልካም አስተዳደር፣ የዲሞክራሲ እጦት ነው። ድህነትን አሸንፈን ልማትን እውን ካደረግን የመልካም አስተዳደሩንም ሥራ ከአጠናከርንና የሕዝቡን መብት ካረጋገጥን ሕዝባችን ብድግ ይላል፡፡ ለዚህ ማብቃት አለብን ይል ነበር፡፡ የመለስ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ራዕይ ይሔ ነው።
ዘመን፦ እርስዎ ከትግሉ መስራቾች አንዱ እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ ያኔ ለዚህ ለአሁኑ ጊዜ እንበቃለን ብላችሁ ታስቡ ነበር?
አምባሳደር ስዩም፦ መለስ ያለው ነው፡፡ የቅብብሎሹ ታሪክ ነው።ሰው መቼ እንደሚሞት አይታወቅም፡፡ እንኳን ለዚህ እድል ልንበቃ ቀርቶ ነገን እንውላለን፣ አንውልም ማንም የሚያውቅ የለም፡፡ እንጀምረውና ወጣቱ ትውልድ ይቀጥልበታል። ሕዝቡ ትግሉን የእኔ ነው ብሎ ይሂድበት፡፡ ሕዝቡን ባለቤት እናድርገው ነው ምኞታችን። ህወሀትም ኢህአዴግም ልዩ የሚያደርጋቸውና የትግል ሂደታቸውም ሆነ ራዕያቸው የነበረው የዚህ ትግል ባለቤት ህዝቡ ነው የሚለው ነው፡፡ የኢህአዴግና የደርግ ወታደር ተብሎ በሁለት ወታደሮች መካከል የሚካሄድ ጦርነት የህዝብ ጦርነት ነው፡፡ ጦርነቱ የሕዝቡን መብትና ክብር የአገሪቱንም ህዳሴ እውን ለማድረግ የተካሄደ ነው እና ትግሉ የህዝቡ የራሱ ስለሆነ ህዝቡ ባለቤት ሆኖ ይህን ትግል መምራት አለበት። የሚፈለገውን መስዋዕትነትም በሁሉም መስክ መክፈል አለበት። እኛ ይህችን ለማስጨበጥ እድል ካገኘን ከዛ በኋላ ሚናችንን ተወጥተናል የሚል ነበር፡፡ እና ለዚህም ነው እነመለስ ለእኔ ፣ ለራሴ ክብር ሳይሆን ዛሬ ይህቺን ሰርቼና መስዋዕትነት ከፍዬ ልለፍ ይሉ የነበረው፡፡ የእዚህ ትግል ታሪክ ብዙ ነው፡፡ ተነግሮለት የሚያልቅ አይደለም፡፡ ገና አልተፃፈም። ጀግኖች ጠላት ምሽግ ገብተው ያፈራረሱበትና እንደ ቢራቢሮ የእሳት እራት የሆኑበት፡፡ ፈንጂውን በህይወት እየጠረጉና እየረገፉ የሕዝቡን ትግል ለድል ያበቁበት፡፡መስዕዋትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆነ ፍጡር የታየበት ትግል ነበር፡፡ ይህን ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይኮራበታል።
ዘመን፦ አምባሳደር ዛሬ ላይ ሆነው የእርስዎ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩና የመሰል ጓዶቻችሁ የትግልና የመከራ ጊዜ አልፎ ሲያዩት ምን ይሰማዎታል?
አምባሳደር ስዩም፦ እኛና መለስ ያየነውን፣ መለስ የፈጠረውን ሳያዩ ያለፉት የትግል ጓዶች ይታዩኛል። እኛ በጣም እድለኞች ነን እንላለን፡፡ ይህን አይተናል፡፡ መለስ ሁልጊዜ የሰጣችሁኝን አደራ ዳር ሳላደርስ አልቆምም ይል ነበር። ህይወቴ ከመሬት በላይ እስካለች ድረስ ከዚህ ድርጅት አልለይም፤ የሰጣችሁኝን አደራ ተግባራዊ አደርጋለሁ ሲል ነበር።የእርሱን ቃል፣ ራዕይና አመራር እውን ለማድረግ ሲታገሉ አልፈው ለቀበራቸውና መስዕዋትነት ለከፈሉ ብዙ ሺዎች ሲገባላቸው የነበረውን ቃል አክብሮና ፍላጐቱን አድርሶ ሔዷል። የቀረነው እንግዲህ መለስ ያላየው እኛ ያየነው አለ። የመለስና የኢህአዴግን መስመር፣ የሕዝቡንም ፍላጐትና ራዕይ አይተናል፡፡
እኔ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡ ከታደሉት ውስጥ ነኝ፡፡ እንኳን አርባ አመት በዚህ ሁኔታ እቆያለሁ ቀርቶ በትግሉ ወቅት አርባ ቀንም እንኳ እኖራለሁ የሚለውን ሀሳብ አልሜውም አላውቅም፡፡ ለማንኛውም ከዚህ ሕዝብ አብራክ መውጣት ሁል ጊዜ እየኮራህበት የምትሔደው ጉዳይ ነው፡፡ የሚያስተምርህና የምትኮራበት ሕዝብ ነው፡፡ለእዚህ ሕዝብ ደግሞ ብትወድቅ የክብር ክብር ነው፡፡
ዘመን፦ እግዚአብሔር ይስጥልኝ አምባሳደር በዘመን መጽሔታችን ስም እግዚአብሔር ያፅናዎት እላለሁ፣ ሁላችንንም እግዚአብሔር ያፅናን፡፡
አምባሳደር ስዩም፦ አሜን ሁላችንንም ያፅናን፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቶሎ ከዚህ ሐዘን ወጥቶና ፀንቶ የያዘውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥልበት አደራ እላለሁ። እየሰጠን ያለውን ኃላፊነትና አደራም እንሸከማለን ብዬ ላረጋግጥለት እፈልጋለሁ። አመሰግናለሁ።
staff reporter | February 23, 2013 at 10:27 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1tx

Comment

 

Saturday, February 23, 2013

EOTC in Exile issues Statement of Declaration EOTC in Exile



 
Statement of Declaration from the Legal Holy Synod of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Exile on the Upholding of the Church's Cannon Law and the Return of His Holiness Patriarch Abune Merkorios to the Throne from which He was lllegallv Ousted
"Be subject therefore unto God; but resist the devil, and he will flee from you." (James 4:71)
 IntroductionAt its 34th biannual conference held in November of 2012 in Columbus, Ohio, the Legal Holy Synod-in-Exile passed a resolution affirming that a special session---a follow-up to the latest peace ond reconciliation efforts within the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church -- would be held in Los Angeles. Accordingly, the Synod held the meeting on January 7-9, 2013. Following is the Synod's statement of declaratian based on deliberations made at that meeting.
Mindful of this regrettable blemish on the Church, as well as driven by a genuine concern to save it from continuing turbulence, a few true sons of the Church founded the Council of Peace and Unity of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. The Council resolved to bring the Church back to its normalcy by embarking on a mission that would beget peace and reconciliation between the Holy Synod in Ethiopia and the Legal Holy Synod led by His Holiness Abune Merkorios in North America. Nevertheless, a small group of Archbishops within the Addis Ababa Synod, squashing the voices of the majority membership of that Synod, thwarted the peace and unity mission by announcing a statement that in effect wrecked the chances of bringing about the desired unity of the Church. ln its content, not only was the announcement one unexpected of Orthodox Fathers, but also lacked truth, clarity, and integrity of intent; given these facts, therefore, the Exiled Synod has no choice but to issue this statement of declaration to the adherents of the faith in the interest of disclosing the true circumstances that led to the division of our Church and the ramifications thereof.
ln fact, the above referenced Article was put into full effect in the case of our first patriarch, His Holiness Abune Basliose, who was under ailment for about seven years and unable to discharge the duties of the Patriarchate fully. At the time, the great leaders of our Church, strictly adhering to the canon law, elected an Acting Patriarch to lead the Church while the reigning Patriarch was still ill. Eventually, following his death, the Synod elected His Holiness Abune Tewofilos as the second Patriarch of the EOTC in accord with the tradition and practices of the Church.
Furthermore, it should be clearly evident to everyone concerned that neither a letter nor a recorded voice exists that conforms tc the purported statement of the exiled Patriarch with regard to his alleged illness, and the voluntary abdication of his throne thereof. Therefore, in the absence of any credible evidence, other than the unsubstantiated allegation, it should be obvious that the Patriarch was indeed forced out of his position under the orders of the regime's security forces.
It is also ironic that the esteemed Fathers in Addis Ababa also claim that "The Holy Synod is a righteous body guided by the Holy Spirit, and, therefore, Patriarch Abune Merkorios's voluntary abdication of his position should be seen as a way of divine intervention, or a secret means to an end of his reign." Although the true believers of the Church are already privy to the fact of this matter, we still want to expound further on this issue by listing these authenticated details:
 

  1. Mr. Tamerat Layne, the then-Prime Minister of the new government that came to power in 1991 (1983 E.C.), declared at the time that the regime would not wish to work with the Patriarch. lt was subsequently resolved that, until such time that the new rulers stabilized the political uncertainty engulfing the country, the "Holy Synod should operate as is but with the Patriarch's role being limited only to providing prayers and blessings," which in effect meant stripping him of his normal duties as the Head of the EOTC;

  2. ln a letter dated Meskerem 28, 1984 E.C. (Oct, 1992) and numbered 69/298184, the regime illegally issued an order to the Patriarch to vacate his office at the Patriarchate;

  3. Subsequent to that order, His Holiness was forced out of his official residence by security forces on Meskerem 30, 1984 E.C. (Oct, 1992) and practically remained under house arrest in an undisclosed area of Addis Ababa for one year;

  4. Still, in a letter dated Tir 15, 1984 E.C. (January 24, 1992), the Patriarch informed the then-President of the Transitional Government of Ethiopia, Melese Zenawi, PM Tamerat Layne, all members of the Holy Synod, and the Executive Director of the EOTC Patriarchate, affirming that there was no illness nor any other impediments that would prevent him from discharging fully and ably his Holy duties, adding that the esteemed Fathers of the Holy Synod knew perfectly about his ability to do so;

  5. Despite His Holiness's plea against his forced removal, the regime-orchestrated appointment of Abune Paulos as the fifth Patriarch was executed in violation of the canon law of the Church. ln the aftermath, the group that forcefully took over the Church's chain of command placed the legal Patriarch in a life-threatening predicament, forcing him to stay in the underground basement of a burial site at an Entoto church, not too far from the capital city. Gravely concerned about the personal safety and security of the Patriarch, some faithful put together a plan that would escort him clandestinely on Tekimit 1, 1985 E.C. (October 12,1993) to neighboring Kenya through Moyale, a border town between Ethiopia and that country;

  6. ln Tikimt 1985 E.C. (October 1993), His Holiness announced to all followers of the Orthodox faith around the world via radio and through a press release from his exile in Kenya that he is still the legal Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church; and

  7. The events that we have outlined above were finally validated in recent times, thanks to both the current President of Ethiopia, His Excellency Girma Wolde Giorgis, and former Prime Minister Tamerat Leyane, who publicly corroborated the forced removal of the Patriarch in no uncertain terms. Even more importantly, we do have in our possession original documents that further offer evidence substantiating the facts enumerated above. ln fact, we are ready any time to show these authentic, historic documents to anyone seeking them. Despite these undeniable facts, however, the Holy Synod in Addis Ababa continues to deny the truth and still insists on alleging that His Holiness "voluntarily abdicated his throne," a claim that was made in the most recent statement issued from Addis Ababa. Meanwhile, we wish to reiterate that the faithful should not by any means be fooled by an assertion that is devoid of truth, as well as an outright falsification of facts and events.
ln the same statement of declaration, the minority within the Addis Ababa Synod has accused us of "establishing a Synod in exile coiitrary to any historical precedence known to Orthodox religion," Yet we found this to be disingenuous in the sense that it was not intended to address the issues associated with the forced removal of the Patriarch. The esteemed Fathers even went as far as declaring that "Without the permission of the Holy Synod, even the celebration of Fasika (Fthiopian Easter) outside of the Archdiocese of the Church is prohibited based on the canonical law of the Church." To confuse the faithful, they further cited the most venerated religious figures of Orthodox Christianity, such as Pope.Saint Athanasius, 5t. Yohanes Afework and Pope Saint Dioscorus, to validate their point, contending that these past saintly Fathers did not establish a Synod in exile, even though they were banished from their church in which they held the highest position of a Pope or a Patriarch. However, the reference to such Sreat Orthodox saints disguises the truth, since it can only be relevant to a church in which its stability and sanctity, as well as its basic principles of faith, have not been compromised; as such, the cases of the saintly Fathers thus cannot be reasonably used to describe the crisis in our Church, which has fallen under the control of a seemingly "foreign" force that is not only hostile to the Orthodox faith but also has consciously breached the canon law of the Church. Let us now look at the cases of the three great Orthodox Fathers as they relate to the establishment of a synod in exile:
  1. Saint Athanasisus, Saint Yohanes Afework, and Saint Dioscorus were all exiled as individuals, not as part of a group of high clergymen. As everyone who is familiar with Orthodox hierarchy knows, no one individual or a Patriarch alone is authorized to establish a Synod, run a Patriarchate, and consecrate new bishops. ln this connection, both Saint Yohanes Afework and Saint Dioscorus were placed under house arrest in exile, and this meant that they did not even have the freedom to act on simple religious matters, let alone establishing a Synod or appointing bishops. ln fact, their saintly biographies reveal that they lived the rest of their lives in prison and passed away without ever gaining their freedom.
  2. His Holiness Abune Merkorios, by contrast, was forced into exile along with his fellow Archbishops, including His Eminence Abune Yisehaq, Archbishop of the Western Hemisphere; Abune Elias, Archbishop of Europe, Africa and Australia; Abune Zena Markos, Deputy Patriarch; Abune Gorgorios, Archbishop and Special Secretary to the Patriarch; and Abune Mekesedek, who at the time was Dean of the Theological College of the Holy Trinity and current General Secretary of the Holy Synod in exile. The exiled Fathers together established the Synod in exile, and have since expanded their missionary work, and will continue to do so as the legal Ethiopian Orthodox ecclesiastical body in North America. Given these facts, the futile attempt by the Synod in Ethiopia to liken our situation to the cases of the cited saintly Orthodox Fathers is masked in distortion of facts. Moreover, their pronouncement lacks the integrity that the Almighty God has bestowed on them as disciples of his teachings, while at the same time exposing the faithful to utter confusion and falsehood.
Another historical fact begs further explanation to counter the argument that the Addis Ababa Synod has made. When Saintly Father Athanasisus, Patriarch of Alexandria, was exiled five times, at no time did his followers attempt to fill the leadership void created by replocing him with onother person. In fact, when the rulers of Constantinople tried to force upon them someone on their "religious Father," they vehemently rebuffed that order, thereby remaining true to their belief rather than acquiescing to the regime's demands. During the fourth century, our religious forefathers in Axum took a similar action by reecting the accusations made against Saint Athanusius by Constantinople.
Likewise, when Saint Yohanes Afework was falsely accused and forced into exile, his follawers cried out for his return and never accepted his replacement with an open arm. Upon his death, even his accusers felt so remorseful about what they did to him that they cried and pleaded in these words, "Forgive us our Father," but never mocked at him as their ex-Patriarch.
Similarly, Saint Dioscorus, who accepted his exile with grace and saw his suffering os a source of religious atonement, sent his followers a message of exaltation reminding them that "the fruits of the true religian are vested in you," a message that resonated with them for as lang as he was alive; it was a reminder that they believed in him until eternity, as they never wavered from what he taught them, and still recognized him as their leader even when the rulers of Constantinople named a replacement for him without their consent. As their loyalty to Saint Dioscorus was unflinching, it was passed from generations to generations in the annals of Orthodox history. Yet those who followed the orders of Constantinople accepted the replacement af Pope Dioscorus and took a different route that made the religious division bona fide.
ln keeping with the traditions established by our great Orthodox Fathers - Saint Athanasius, Saint Yohanes Afework, and Saint Dioscorus - His Holiness Abune Merkorios has continued in exile his godly work more resolutely than ever. The Almighty God has blessed him to be of great service to the followers of the faith, as he leads a group of devout Archbishops,12 of whom he appointed personally, who perform faithfully God's work throughout the Diaspora Orthodox community, The Legal Synod he leads has helped establish a growing number of churches that are now under the umbrella of the Patriarchate, while at the same time making it possible for the faithful to have their spiritual needs served well. The affiliated churches are growing in number; the missionary work of the Synod is more expanding than ever; the faithful are attending church services in greater numbers more than any other time; and a strong base for communities of Ethiopian Orthodox faith throughout the Diaspora is being established with great fervor. Above all, our community is more prepared than before to build a strong Orthodox foundation; to leave a legacy that gives vibrancy to Ethiopia's Orthodox faith; to revitalize its unique history; and to pass these vital societal hallmarks to the generations to follow.
C. Concerning the Peace and Unity Mission
The Council of Peace and Unity of the Ethiopion Orthodox Tewahedo Church embarked on a mission of peace and unity, mediating between the Holy Synod in Ethiopia and our Synod so as to unite the divided church though reconciliation. With the blessings of His Holiness Abune Merkorios and the Synod's full endorsement of this effort, a team of representatives was named to present our case. Three conferences took place over the last three years involving our team and representatives from the Addis Ababa Synod. Throughout the course of time, the peace and unity mission was greeted overwhelmingly by almost all Orthodox Tewahedo believers both at home and abroad and was awaited with a great sense of hope and optimism.
ln Ethiopia, the majority of the Synod's membership, the clergy, Sunday School pupils and many others concerned individuals and organizations all saw the reconciliation efforts with great fanfare and exaltation. However, the statement issued by the Holy Synod in Addis Ababa, following the talks in Dallas, was such that it not only undermined the process of the reconciliation mission but also presented facts that were deceiving and distorted. ln essence, that statement characterized our position in terms that were outright false. ln it, the Addis Ababa Synod misrepresented the Legal Synod's position describing it in these terms: "There is no such thing as peace and unity within the Church unless we control the Patriarchate," an outright lie that had no credible support, Given this backdrop then, what actually took place during the peace talks? What was the agenda considered for the negotiation? To answer these and other related questions, the following points must be clearly understood:
  1. At the outset, we found out that the team representing the Holy Synod in Addis Ababa had neither the will nor the authority to propose or accept ideas during the course of the negotiation. They presented the same old and debunked argument that "Abune Merkorios abdicated his throne voluntarily and that the Church must now move to selecting the sixth Patriarch," a position that gave no room for further discussian because they had no authorization from Addis Ababa to do anything otherwise;
  2. Since the Addis Ababa Synod has come under the direct control of the regime in power, the peace and unity mediation was doomed from the start, as was evident in the provocative statement released by the Synod that was detrimental to the negotiation even before the team had a chance to report to the entire Synod on the progress of the talks. On one hand, a team was sent to Dallas purportedly to negotiate with us, but at the same time the Acting Patriarch in Addis Ababa was making a statement in an interview over the media that was counterproductive to the negotiation, which in effect gave a clue about the malicious hand of the regime in the affairs of the Church, and therefore was really an effort in futility even to begin with; and
  3. The team representing the Legal Synod in North America, by contrast, was charged with a full authority to negotiate with its counterpart and thus made every effort toward the settlement of the outstanding issues that created the divide within our Church. During the negotiation, we adopted a good measure of flexibility in our bargaining posture, proposing what we thought was a workable solution that would both address the breach of the canon law and yet offer due recognition to the reigns of both the legal Patriarch and the one that was placed on the throne in violation of Orthodox practices. To this end, our team proposed the reinstatement of the legal Patriarch to his former position, so that he will finish up his reign without any lasting damage to the canon law, and then to be followed with the selection of the six Patriarch when the vacancy becomes legally available. However, the latest announcement issued by the Synod in Addis Ababa made it clear that tirey never had the true intentions of finding solutions to the problem. ln fact, they appeared to play "the number game," arguing that reinstating the legal Patriarch now, the fourth in the order of appointment, after the fifth Patriarch (the late Abuse Paulo's) is going "backwards in the numbering order" and thus unworkable, which we found it to be a disingenuous way of looking at the issue at hand aswellas a clear indication of notwantingtofind a realsolution to a realproblem.
After probing the retrogressing behavior of the Synod in Addis Ababa subsequent to the Dallas meeting, it became apparent to us that five of that Synod's Archbishops have taken full charge of making the decision, thereby overshadowing the voices of the entire Synod; they are active members of the ruling party and thus charged with stymieing the peace and unity mission. We also discovered that each had an ambition to become a Patriarch, and therefore it would not have been in their personal interest to support the peace and unity effort even from the start. Any possible return of the Patriarch to his throne would have apparently gone contrary to their plot, as well as to the wishes of the regime to which they report.
From the facts stated in the foregoing, it becomes crystal clear that a small but powerful clique of the Woyane regime, which orchestrated illegally the removal of His Holiness Abune Merkorios from his throne 21. years ago, is still in charge and continues to disgrace our Church.
ln fact, this ruling clique is more determined than ever to subject our Church to relentless infamy; destroy the sanctity of the Church itself as we know it; and weaken the spiritual resiliency of the devout believers of the Orthodox Tewahedo faith.
Taking into account the events described above, the Legal Holy Synod in North America examined thoroughly the state of the EOTC in both Ethiopia and the Didspora and has passed the following resolutions:
  1. Since His Holiness Abune Merkorios is stillthe legal Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the Holy Synod in exile condemns any illegal enthronement of a Patriarch for the EOTC in Ethiopia, because it would be a serious contravention of the Church's canon law;
  2. For more than 21 years, our Church has undergone a crisis of historic proportions, as a government-led coup d'etat against the legal Patriarch was put into effect, leading to the illegitimate ascension of the late Abune Paulos to the throne and the division of the church thereafter. That regrettable action was being repeated again, as five members of the Holy Synod in Addis Ababa, using the power of the regime, were mobilizing forces to install a "Patriarch" of the regime's choice. Thus, based on the orders enshrined in the decrees of the Holy Book, the Synod directs that the true believers of the Orthodox faith, forever and in unison, oppose to, not recognize, or refuse to comply with the appointment of a "false Patriarch" in Ethiopia. The Synod further implores that the true Fathers of the Church in Ethiopia, especially those who stood their grounds for the peace and unity of the Church, refrain from participating in these questionable and ungodly exercises, which are indefensible in the court of both history and the Almighty God;
  3. The Legal Holy Synod is deeply saddened by the fact that all those who stand for the peace and unity of our Church, including our religious Fathers, the clergy, organized Orthodox groups, and the faithful at large in Ethiopia, are being subjected to threats, intimidation or warnings, often coming from government operatives that oppose the return of the legal Patriarch to Ethiopia. These criminal practices against the Orthodox community are part and parcel of the sufferings that all other citizens in Ethiopia are being subjected to under the current regime in Addis Ababa. We are cognizant that our country is at a crossroads of political and social crises and that we pray to the Lord, so the suffering of our people will come to an end. Meanwhile, we are hopeful that Ethiopia will resurrect itself, and our Church will soon regain its freedom from the shackles of bondage. Meanwhile, the Synod wishes to counsel that the faithful engage at all times in activities that not only advance unity and peace for our Church but also foster a sense of fellowship and harmony between and among both the clergy and the laity. We hope you do so with greater care, wisdom, and stronger religious convictions;
  4. The Synod was dismayed to learn that the political gang that had been waging a war of attrition on our Church for more than two decades has made recently the most ungodly claim of having "uprooted the Ethiopian Orthodox Tewhaedo Church from its foundation while annihilating the Amhara benefactors." Besides allowing alien religious forces to undermine our faith, distorting EOTC's positive contributions to Ethiopia's history, encouraging Orthodox believers to turn against their own faith, this seemingly godless clique is running a government bent on destroying our heritage as proud Ethiopians. The statement quoted above offers clear evidence that Ethiopia and particularly our historic Church is under grave danger and that the regime has neither good intensions nor goodwill for people of the Orthodox faith, as would have been expected under a government of national unity. With this being the case, the Synod urges all the faithful to join forces to engage in prayers and vigils so as to publicize this danger while pleading to our Creator to give us solace and strength to save our Church from further destruction;
  5. We believe that the Holy Synod is the messenger of hope and goodwill, and stands for what is right and what is always acceptable unto God. As an ecclesiastical body advancing the work of God, the Holy Synod abominates any practice that begets racism, ethnicism, or any other discriminatory treatment of human beings. ln Ethiopia today, the pitfalls of ethnic-based rule are causing havoc on our society. Even the most celebrated monastery, Waldiba, has not been immune from the misfortune befalling Ethiopia today, Dozens of monks and celibates are being persecuted for resisting the government's desecration of the holiest of the holy site in that country. "The shrine and sanctity of our grand monastery must not be trampled with," cry out the monks of Waldiba, but the response from the regime was a swift and merciless action of intimidation, physical abuse and imprisonment of those God-fearing Orthodox celibates.This meant that the monks in Waldeba have joined the ranks of journalists, human rights advocates, and political prisoners who are all languishing in prison for voicing their ideas, and, in the case of the monks, for objecting peacefully to the demolition of their sacred and holy sanctuary; consequently, they all have become victims of government abuse and official oppression. Given that the regime has caused untold atrocities on every segment of our population, the Synod has resolved to take a stand and become an advocate for those whose freedom and liberties are being crushed in Ethiopia. Ironically, this has come at a time when the federal holiday commerating the birthday of the most celebrated African American civil rights leader, The Rev. Dr. Martin Luther King, was before us. The issue of civil rights and liberties in Ethiopia is one that we intend to publicize to the rest of the world using every available means at our disposal, as Dr. King had done decades ago. ln keeping with the tradition of our own great Orthodox Fathers of the past, who sacrificed their lives for their religious beliefs, including the martyred Abune Pateros, Abune Michael, and the great Patriarch Abune Tewoflos, we in the Exiled Synod, guided by His holiness Patriarch Abune Merkorios, have resolved that we will stand for the freedom of our people in Ethiopia and work toward peace and unity of our Church, relying on the power of God and His blessings. There should not be any doubt that the survival our country is directly tied to the survival of our Church, and thus any weakening in our faith will undoubtedly have a direct bearing on the survival our beloved country, as well. Therefore, we call on all Ethiopians, especially those with strong ties to their country of birth, to rise up in unison and join us in solidarity and unity to voice our cries for freedom and liberty in the country that we all cherish so dearly and collectively;
  6. To effectively carry out the objectives outlined above, the Holy Synod-in-Exile has restructured the Patriarchate and made some readjustment to its priorities. Accordingly, our plan to expand the number of Archdioceses and consecrate additional Bishops, which was on hold due to the now defunct peace and unity bid, will now go forward with new force and vigor. To this end, the Synod has strengthened the Office of the Patriarchate by appointing a three-member executive body charged with coordinating and monitoring the day-to-day operations of member churches throughout the globe; it consists of a General Manger, an Executive Secretary, as well as a Public Relations Officer. Yet this new direction will require the full participation of the faithful particularly in the Diaspora. Your ideas, prayers, and generous financial support are all critical to make a difference in executing the plan that has been put forward, and so the Synod is hoping that your will respond positively to our call for action;
  7. During the last several years, the Exiled Synod has made a sincere effort to bring together the divided Church and the faithful in the Diaspora with some success, but still much remained to be accomplished, During the same period, many of the faithful and several churches had hoped that the divide within the Ethiopian Orthodox Tewhaedo Church would come to an end through reconciliation and thus chose to remain neutral until that happened. However, that hope was dashed when the Synod in Addis Ababa aborted the peace and unity mediation efforts. Given this backdrop, the Holy Synod has now resolved that it has the moral obligation to bring all the Orthodox faithful and neutral churches under a reinvigorated Holy Synod that caters to the spiritual needs of the Orthodox community at large. By so doing, the Synod's guiding principles will be "one country, one people and one church." With this in mind, we pray that the faithful and those churches that are not affiliated with the Synod will join us to make this a reality. To those who are true helievers of the Orthodox faith, are genuinely concerned with crisis facing our Church, and have great ideasto rescue the Church from its current predicamen! we call upon you once again to stand up for freedom and liberty of the Orthodox faithful as well as the sanctity of our Church. Since the Synod has established a special taskforce to find ways that will bring all the divided churches in the Diaspora into unity, the group assigned for this purpose is ready to meet and discuss with representatives of neutral churches and others to build the groundwork that will be necessary to nurture unity, solidarity, and fellowship amongst our people;
  8. The Synod believes that it has the responsibility of educating and informing international organizations, religious communities, human rights organizations, and governments around the work about the brutalities to which our clergy and our people at home are subjected. With this in mind, we have established a taskforce, consisting of members from among the Archbishops, the clergy, and the laity, the charge of which will be to give testimonials at international forums, as well disseminate information as necessary to publicize the danger that our Church is facing;
  9. The recently announced statemont by the Holy Synod in Addis Ababa came from a small group of Archbishops who are in cahoots with the regime, and was made by suppressing the voices of reason expressed by others within the Synod. The statement sent shockwaves throughout the Diaspora Orthodox community that was awaiting for good news, with unprecedented fervor, to see the divide within the EOTC coming to an end.Flowever, the crisis facing the Church will only come to pass once we receive some redemption from our Lord. Our Church, throughout its history, has gone through many tribulations and historical adversities, one of which was the destruction inflicted on it and its treasures by Gran Mohamed. Many Orthodox scholars and believers have lost their lives in defense of our Church duringthis period of sheer destruction that lasted L5 years. After the passage of that tumultuous period, the Church is still a symbol of "light in the midst of darkness." Even with the current crisis, the Synod asks you---the faithful --not to lose hope but to pray and plead too our Almighty God for salvation. Having accepted the commandment of the Holy Spirit, the Holy Synod has taken up the moral obligation to propagate the words of the Gospel through a rejuvenated missionary program and reach out to the Orthodox faithful throughout the diaspora. As commended in the verses of the Holy Bible "Comfort ye, comfort ye my people, saith your God" (lsaiah 4Ai7," the Holy Synod is ready with new energy and zeal to comfort those that need to be comforted; those designated to do the missionary work of the Synod will be at your service from hereon;
  10. Despite a three-year effort to bring peace and unity to our Church, which was finally thwarted by a small cadre of Archbishops who act as regime operatives within the Addis Ababa Synod, the Synod-in-Exile extends a heartfelt appreciation to the Council of Peace and Unity of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church for being so benevolent in their mediation and sacrificing their precious time, energy and resources for a noble cause that has both national and international implications;
  11. At the same time, the Synod has resolved that the selection of the 6th Patriarch that was underway should be halted immediately because the silent majority within the Addis Ababa Synod was not in favor of it, nor the mediators and the faithful at large. We think that the peace and unity effort should take precedence over the selection of a Patriarch, who would be just as illegitimate as the one before him. Therefore, we are still acquiescent to the peace and unity mission, so that the divide within our Church can be overcome once and for all, and we are ready to do our part to bring a historic end to that divide; and
  12. The Los Angeles meeting concluded with the final blessings of His Holiness Abune Merkorios, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Church. Hosted by the clergy, the board, and members of the Dingil Mariam Orthodox Tewaheda Church in Los Angeles, the meeting was received with great enthusiasm and patronage. For this, the Synod gives special thanks to all the members of that Church; we are deeply indebted to the hospitality and graciousness that they exhibited during the course of the meeting.
 

staff reporter | February 23, 2013 at 8:38 pm | Categories: Africa, AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1ts
CommentSee all comments