Wednesday, September 26, 2018

ከሰሞኑ የከሸፈው የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ሚስጢሮች ( ዳነኤል)


የጠ/ሚ አብይ መንግስትን የመገልበጥ ሙከራ እንቆቅልሽ!

የመንግስት ግልበጣ ውጥን ነበር ከሽፏል! ፥,አሁንም ያልከሸፈው ከግልበጣው ጀርባ ያለው ፓለቲካዊው ቁማር ነው:: ይህም ቀጥሏል::
የመንግስት ግልበጣው መሃንዲስ ህወሃት ሲሆን የሴራው ተባባሪዎቹ አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦነጋውያን(OLF)ና አክቲቪስቶች ናቸው:: 


A). የመንግስት ግልበጣ ጠንሳሾች የጋራ አላማና አንድነት bበአጭሩ:-

1. ህወሃት(TPLF) አፓርታይዳዊ የህዳጣን ሥርዐቱን ለመመለስ፣ ይህ  ደግሞ ካልተሣካ ኢትዮጵያን ለመበታተን

2. የጠ/ሚ አብይና የፕ/ት ለማ መገርሣን  ኢትዮጵያዊ ቀመር በሁለቱም ሃይሎች አለመወደድ

3. አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦነጋውያን(OLF)ና አክቲቪስቶች አንድም ኦሮሚያን የመገንጠል ይህ ካልሆነ የብዝሃን ጎሣ አምባገነን መንግስት (multiethnic government)መመስረት ህልም ለመተግበር

4. የአርበኞች ግንቦት 7 መምጣትና ይህን ተከትሎ በትላልቅ ከተሞች ላይ የታየው የኢትዮጵያዊነት መንፈስ መነቃቃት፣ ማበብና ማንሰራረት ለህወሃትም ይሁን ለአክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞች (OLF, TPLF).ምቾት ስለነሳቸውና በነዚሁ ከተሞች ያለው ሕዝብ እንደማይመርጣቸው ማወቃቸው ዋነኛው ምክንያት ነው::

 የመንግስት ግልበጣው ሴራና ዕቅድ!


ሀ). የመንግስት ግልበጣው ቅድመ ዕቅድ (pre-coup d’etas Contingency plan)

በድሬዳዋ፣ ቡራዩ፣  አዋሣና አሰላ የዘር ጭፍጨፋ በማድረግ ሕዝቡ በቁጣ ገንፍሎ የፕሮፓጋንዳቸው ሠለባ ማድረግና ለአመፅ መገፋፋትና የጠሚ አብይን መንግስት ከቁጥጥሩ በላይ የሆነ ክስተትን መቆጣጠር አልቻለም የሚል ግንዛቤን በሕዝብ ውስጥ በማስረፅ ለቀጣይ ዕቅድ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ነበር::
ለ). የመንግስት ግልበጣ ድህረ ዕቅድ
(post - coup d’etas Contingency plan)

1. አዲስ አበባ አቀፍ ሰልፍ መጥራትና በሰልፈኞቹ መንገድ  በመዝጋትና ማህበራዊና የንግድ አገልግሎትን ማሰናከል

2. ኢቲቪ*ETV(ና ፋና ሬዲዮ ጣቢያን መቆጣጠር

3. ኦሮሚያ ባህል ማዕከልን፣ ባንክ ፣ ኢንሹራንስ መንግስታዊና የግል የንግድ ተቋማትን በመቆጣጠር፣ በመዝረፍና በማቃጠል የአካባቢውን የኦሮሞ ገበሬን በቁጣ በመቀስቀስ ከተማዋን ማስወረር የትግራይ ተዎላጆችን ንብረት የሆኑትን ህንፃን መዝረፍና ማቃጠል

4. የ"ጎሣ ፌደራሊዝምን" (ethnic federalism)እና የተዎሰኑ ብሔረሰቦችን  ነጥሎ በመፈክር በማውገዝና በመዝለፍ  ሰንደቅ          ዓላማ  በመቀየር "ህገ መንግስቱ ተጣሰ" በሚል ሴራ  ሐገራዊ ድጋፍን ማሰባሰብ
5. "ሥራዓት አልበኝነት በሃገሪቱ ነግሷል" በሚል ሽፋን "ሕዝብን ከእርስ በርስ እልቂት ለመከላከል ፣ለመጠበቅና ወንጀልን                 ለመከላከል" ጦሩ ጣልቃ ገብቷል የሚል በድርጊት የታገዘ ፕሮፓጋንዳ በማሰራጨት ከዓለም አቀፋዊ ማህበረሰብ ድጋፍን              ማሰባሰብ
6. ህወሃት በሚስጥር ባሰረጋቸውና በአዲስ አበባ የሚገኙ የደህንነትና የጦር ሃይሉች አማካኝነት የጠሚ አቢይን መንግስት ሁኔታው      ከቁጥጥሩ ውጭ ነው በሚል ዶር አቢይን ከስልጣን ማውረድና የጠቅላይ /ሚኒስተር  የለውጥ ቡድን(team Lemma)ና              አጋሮዎቸን ማፈስና ማሰርና (Replacement of incumbent leaders with another)
7. የገቡ የለውጥ ሃይሎችን ሃገር ጥለው እንዳይወጡ የአየርና የምድር ትራንስፖርት በማገድ በቁጥጥር ስር ማዋል

8. የመንግስት ግልበጣው ውጥን የተነደፈው በግንቦት 7 እንደሆነ በማስመሰል ጦሩም ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ጣልቃ       እንዲገባ ማድረግ የድራማው ክፍል ነበር::

C). የመንግስት ግልበጣው እንዴት ከሸፈ?

የመንግስት ግልበጣው ውጥን ከሰላማዊ ሰልፉ ጥሪ ጋር የተያያዘ ነው:: ሠልፉን የጠራው ይህ የግልበጣ ቡድን ነው:: ውጥኑንም በቅድሚያ የደረሰበት በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የደህንነት አታሼ ሲሆን የግልበጣውን ዝግጅት
ለጠ/ሚ አብይ መንግስት በጊዜው አሣወቋል:: ለግልበጣውም መክሸፍ አይነተኛ ሚና ተጫውቷል:: የግልበጣው ጠንሳሾች ታውቀዋል:: የጠ/ሚ አብይን  መንግስት ቀጥተኛ እርምጃ ለጊዜው በነዚህ ሐይሎች ላይ እንዳይወስድ ኤምባሲው ጫና አሳድሯል:: በግልበጣው ጠንሳሾች ላይ የሚወሰድ እርምጃ የሚያስከትለውን ፓለቲካዊና ወታደራዊ አንደምታና መዘዝ የጠ/ሚ አብይን መንግስት መመከት አሁን የማይችል በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርግና ስልት እንዲነድፍ በተለይም በወታደራዊውና በደህንነት ዘርፉ ላይ የፍፁም የበላይነትን አቅም ፈጥኖ እንዲፈጥር መክሯል:: ይህ ምክንያታዊም ይመስላል::

D).ከግልበጣው ጀርባ ያለው ፓለቲካዊው ቁማርና ሚስጥር!

የመንግስት ግልበጣው ውጥንና ዕቅድ  ከሸፈ እንጂ የፓለቲካው ሴራና አሻጥሩ ቀጥሏል:: የሀገራችን እጣ እጅግ ፈታኝና አደገኛ አዙሪት ውስጥ ገብቷል::

የመንግስት ግልበጣው መክሸፍ በሁዋላ ሁለት ዓይነት መንግስት አንድ ሐገርን እያስተዳደረ ነው:: አንደኛው የጠ/ሚ አብይ እና ቡድናቸው ነው:: ሁለተኛው በጃዋር
(team Jewar)፣ እዝቅኤልና በቀለ ገርባና በፀጋዬ አራርሳ አማካሪነት የሚመራውና በህወሃት የሚታገዘው የለሌውና  ቤተ መንግስት ያለው "የቄሮ መንግስት" ነው:: ተከታዩን ማየት ይበጃል::

ሀ). የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው (de jour)

ይህ ቡድን አጣብቂኝ ውስጥ ያለ ነገር ግን  የኢትዮጵያ 
ብቸኛው ሕልውና ተስፋ ነው:: ይህ ቡድን በህወሃት ሰራሹ ፓርላማ ውስጥ ማህበራዊ መሠረቱን ኦህዴድን (ኦዴፓ) አድርጎ በደህዴንና በብአዴን ድጋፍ የቆመ መንግስት ነው  ነገር ግን ከኢትዮጵያዊያንና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ድጋፍ አለው:: ስለዚህም ይህን መንግስት የሚደግፉት ድርጅቶች አባላት አንዱ የሆነው ህወሃታውያንና የመኖር ህልውናቸው በጎሣ ፌደራሊዝም ታማኝነት ላይ የተገነባ ነው:: ኢትዮጵያውያኑ "የጎሣ ፌደራሊዝም" በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲተካ የሚፈልጉ ናቸው:: የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው በእነዚህ ፍላጎቶች መካከል የሚወዛወዝ ነው:: በመንግስት የስልጣን እርከን ውስጥ እራሱን ለማቆም በአንድ በኩል በህወሃት በሌላ ጎኑ አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ  ኦነጋውያን ድርጅቶች(OLF)ና አክቲቪስቶች ፈተና የሚሰጠውም  በእነዚህ ምክንያት ነው::

ለ). በጃዋር፣ እዝቅኤልና በቀለ ገርባና በተልዕኮ በፀጋዬ አራርሳ አማካሪነት የሚመራ፣ በህወሃት የሚታገዘው የኢሊሊው ሆቴልን ቤተ መንግቱ ያደረገው "የቄሮ መንግስት" (de facto government )

ይህ "የቄሮ መንግስት" መንግስት ያልሆነ ግን እንደ መንግስት የሚሰራና የሚወስን (non-state actor) ነው:: በጠ/ሚ አብይ መንግስት ውስጥ ያሉ ባለስልጣኖችን፣ የፓሊስና ወታደራዊ አዛዦችን በጎሣ ምንነት ሰርጎ ገብቶ የጠ/ሚ አቢይንና ቲም ለማን(team Lemma) ቡድን የሚያዳክም ነው:: ሕዝብ አዋኪ የጥፋት አጀንዳዎችን የሚነድፍም ነው:: በቀጥታም ለነዚህ ሹመኞች ትዕዛዝ እየሰጠ የአዲስ አበባን ወጣቶች በመንግስት ግልበጣ ሰበብ ዴሞክራሲያዊውን ጎራ ለማዳከም እያሣሰረም ነው:: ቡራዮ እንደታየው ግጭቶችን በመፍጠር ጭፍጨፋን የሚተገብርም ነው:: የዚህ ቡድን ድንጋጤ የተከሰተው በአዲስ አበባ በጳጉሜ 4/2010 ዓ.ም ግንቦት 7ን ለመቀበል ናዝሬት፣ አርባምንጭ፣ ጎንደር፣ ጎጃም፣ ወሎ፣ ሸዋና ድሬዳዋ ሕዝቡ በኢትዮጵያዊነት ደምቆና ገዝፎ መውጣት እረፍት ነስቶታል:: በዋነኛ ከተሞች ውስጥ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ አብላጫ ድምፅ እንደማያገኝ ስለተረዳ ቢችል የከተሞቹን ጎሣዊ ስብጥር ለማዛነፍ የጎሣ አባላቱን ለማስፈርና ግጭቶችን በመቆስቆስ ነዋሪዎቹን  ለቀው የሚወጡበትን የማፈናቀልና የጭፍጨፋ ዕቅድ የሚነድፍም ነው:: በዚህ ዕቅዱም ደስተኛ የሆኑ የኦህዴድ ባለስልጣናትና አባላትም ይተባበሩታል:: እየተባበሩም ነው:: የቡራዮ ገዳዮችን ትተው ግድያውን የተቃወሙ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ያፍሳሉ:: ይህ ኢ-ፍትሃዊ ብቻ ሣይሆን መዘዝ ያለው ግፍ ና ወንጀል ነው::

E). የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው ብቸኛ ምርጫ!

የመንግስት ግልበጣው ከሽፏል ማለት እንደገና አይጠነሰስም ማለት አይደለም:: ሀገር በሁለት መንግስት አትመራም:: 

የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው የተኩት የኢህአዴግን መንግስት እንጂ በመንግስት ውስጥ ያለውን የህወሃት መንግስት አልነበረም:: አሁንም የጠ/ሚ አቢይና ቡድናቸው የኢህአዴግ መንግስት ይሁኑ እንጂ በመንግስት ውስጥ የተሠራ የአክራሪዎቹ የእነጃዋር 'በመንግስት ውስጥ ያለ መንግስት (Deep State)' አለ:: ይህ ለጠ/ሚ አቢይና ቡድናቸው ይሁን ለሐገራችን ኢትዮጵያ የህልውና ችግር ነው:: ይህ የነጃዋር ቡድን ባለስልጣኖችን እያዘዘና እየተጠቀመ በራሱ ወንጀል የህዝብን ልጆች እያሣፈሰ መንግድታቸውን ሕዝብ እንዲጠላው እያረገ ነው:: ከመደመሩ ማዕቀፍ ውስጥ በአስቸኳይ ተቀንሰው ለፍርድ መቅረብና በOMN የሚሰጡትን አፍራሽ ቅስቀሳ ማቆም አለባቸው:: ህወሃት ቆሰለ እንጂ አልሞተም:: ህወሃትን እያከሙ ያሉት እነዚሁ አክራሪዎች ናቸው:: ለእራት እያሰቧችሁ ነውና ቀድማችሁ ቁርስ አድርጉዋቸው:: ህወሃት ሲያገግምም እናንተውኑ ይበላል::

F). የኢትዮጵያንውያን ብቸኛ ምርጫ!

በመንታ መንገድ ላይ ያለች ሐገራችንን ከመፈረካከስ ለማዳን ያለን ብቸኛ ምርጫ በኢትዮጵያዊነት ከኢትዮጵያውያን ጋር በሕብረት መቆም ነው:: ከዳር ሆነን ከምንተች መሃል ገብተን ለመለወጥ በተለይም ይደረጋል የተባለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዳይደናቀፍ መስራት አለብን: