Tuesday, September 29, 2015

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ (ጥላዬ ታረቀኝ)



ሰንደቅ አላማ የአንድ ሀገር ህዝቦች ተስማምተውበት ይወክለናል ቢውለበለብ ይገልፀናል ብለው ለቀለማቱ ትርጉም በመስጠት ከምንም በላይ ክብራቸውን የሚገለፀበት የሀገር ውክልና የሚወስድ ወይም የሚገልፅ የሀገር ንብረት ወይም መግለጫ ነው ። ሰንደቅ ሀገራት ከሀገራት የሚለዮበት ትልቅ ምልክት ነው። ሀገራት ወይም ሰንደቅ አላማ ትልቅ ዝምድና አላቸው በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ያለች ድንቅ ሀገር ለሰንደቅ አላማ ያላት ክብር ከፍተኛ ነው ። ሰንደቅንና ኢትዮጵያዊ የተቆራኞት ሀገሪቱ በንግስና መተዳደር ከጀረችበት ግዜ አንስቶ ትውልድ ለትውልድ እያስረከበ ለባንዲራ ያለው ፍቅር ከአያቶች እየተማረ ለልጆች እየተላለፈ የመጣበት ሁኔታ ነው። የነበረበው ሄደቱ ሳይቆራረጥ በዚያ ሰአት የነበረው ትውልድ ሲረከብ ሲያስረክብ ይዘቱን ቀለሙን ሳይቀየር ቢጎዝም በንግስና ግዜ የነበረው መሀል ላይ የሞሀ አንበሳ ምልክት ከሀይማኖት አንፃር ቢነሳም ቀጣይ የነበረ የባንዲራ ፈተናዋች የበዙ ቢሆንም ባንዲራዋ ግን ቀለሞን ሳትቀይር እዚህ ደርሳለች ።
የትውልድ ቅብብሎሽ ባንዲራዋን እዚህ ቢያደርሳትም ያኔ የነበረ ትውልድና አሁን ያለው ትውልድ ለባንዲራ ያለውን ክብር ከማወቃችን በፊት የኢትዮጵያ ህዝብ ለባንዲራ ያለውን ፍቅር መግለፅ ማስቀደሙ ሊገልፀው ይችላል። ብዬ በማሰቤ ይቺን ላስቀምጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ለመከራ ለችግር ለደስታ እንዲሁም ለሀገራዊ ክብር በአላት ላይ ይውለበለባል ሀገራችን ዳር ድንበሮ ተሰብሮ በተወረርንበት ግዜ አባቶች ህዝቡን ሲያነቁ ባንዲራህ ተደፎርል ድንበርህ ተጥሶል ለክብርህና ለባንዲራ ውጣ ብለው ያዙ ነበር። በዚያ ግዜ ለባንዲራ ያላቸውን ነገር ብንገልፅበት ሊገልፀው ይችላል ብዬ ያስብኩትን ይቺን እንመልከት ሸንጎ (.ፍርድ) ሲቀርቡ ሰው ሲበድላቸው እረ በባንዲራ ብሎ ከለመነ ጥፍተኛውም ጥፍቱን ያርማል በዳይም በደሉን ይቅር ይላል ተበዳይም የተጠራው #ባንዲራ በመሆኑ!!!
ለሀገራችንን ኢትዮጵያ ባንዲራ ምንድን ነው የሚለውን ጥያቄ መልስ ሊሆነው የሚችለው ባንዲራ ወይም ሰንደቅ አላማ ማለት ለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር ዘውድ ወይም ደም ማለት ነው። ይሄ ለኢትዮጵያ ህዝብ መገለጫ የሆነው ሰንደቅ አላማ አሁን ላለው ትውልድ ምን ቦታ አለው ብለን መፈተሽ ተገቢ ነው ባይ ነኝ በነገራችንን ላይ የኢትዮጵያ ባንዲራ መንግስታት ሲቀያየሩ በመሳሪያ ስለሆነ ሁሉም ሲመጡ የህዝብን የሚውክለውን ሳይሆን የህዝብን ፍላጎት ሳይሆን እነሱ ይመቸናል ስልጣናችንን ሊያራዝምልን ይችላል ብለው ያመኑትን ከህዝብ ፍላጎት ውጪ ምልክት በመጨመር የስልጣን እድሜን ማርዘሚያ እንጂ ለሀገር ፍቅር ወይም ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ የለም ሁሉም ለራሱ በማሰብ እንጂ የፀና የኢትዮጵያን ባንዲራ የለም መንግስትም ቢወርድ ቀጣይነት ያለው ባንዲራ ባለመኖሩ የአሁን ትውልድ የኔ ነው ብሎ ሳይቀበል ያንተ ነው ተቀበለው ተብሎ ስለተቀበለው ጥቂት የዚህ ትውልድ ወጣቶች የባንዲራ ትምህርት ትርጉም ባይገባቸውም ለባንዲራ ያላቸውን ፍቅር ይሄ ነው ብሎ ለመተንበይ ያስቸግራል የአባቶቻቸው መሰረት ተቀይሮ ስላገኙት ይሄን ደግሞ ለዚህ መሰረት መናጋት ዋናው ተጠያቂ አስተዳዳሪ ሆኖ ራሱን የሾመው የህውሀት ኢህአዲግ መንግስት ነው ።
ከህዝብ ጋ ሆድና ጀርባ ሆኖ በራሱ ፍቃድ ትርጉም ሊሰጥ የማይችል ተጨማሪ ባእድ ከእምነት ከሀገሪቱ ነባራዊ ሆኔታ ጋ የማይገናኝ ለትውልድ መከራ የሚያመጣ እርስ በእርሶ እንዳይተማመን መልካም ያልሆነ የባንዲራውን ፎርም ወይም መልክት ያጠፉ የሰይጣን ምልክት ነው። የተባለወን መሀል ላይ በመሰንቀር ባንዲራውን ከህዝብ በመነጠል የራሱ በማረግ የባንዲራውን ትርጉም በማዛባት በሀገሪቱ የነበረውን የባንዲራ ቁጥር ከአንድ ወደ አስራ ምናምን ያሳደገ የህውሀት መንግስት ለባንዲራ የነበረውን ክብር ዝቅ አድርጎታል ።

በዚህም የተነሳ የአሁን ትውልድ የባንዲራ ትርጉም ጉራማይሌ እንዲሆን አድርጎል ከአስራ ምናምን ውጪ የሀገሪቱ ባንዲራ በሁለት በመክፈል
1 አረንጎዴ ቢጫቀይ (ንፁህ) ቀደም
2 አረንጎዴ ቢጫ ቀይ (መሀል ላይ ኮከብ በማረግ የሀገሪቱን ባንዲራ በሁለት በመክፈል የባንዲራ ፍቅር ይሁን የባንዲራ ትርጉም በማጥፍት ግንባር ቀደም ተወቃሽና ተከሳሽ ይህ ሀገሪቱን እየመራ ያለው መንግስት ነው ።
አሁን በህይወት የሌሉት ጠቅላይ ሚኔስተር አማካኝነት የባንዲራን ክብር ዝቅ በማድረግ ጨርቅ ነው እስከማለት ደረጃ ደርሶ የነበረበት ወቅት ሁሉ ነበር ይሄን የነበረ የሀገር ባንዲራ ትርጉም በማሳጣት ደረጃ ከፍተኛውን ሚና በመጫወት አሁን ሀገሪቱን በመሳሪያ ሀይል እየመራ ያለው ህውሀት ኢህአዲግ አስራ አራት ባንዲራዋችን በአንድ ሀገር ላይ እንዲውለበለቡና በአለም አቀፍ ደረጃ ሁለት ባንዲራዋች በዜጎች ደረጃ እንዲውለበለቡ ከፍተኛ አስተዋፅ አበርክቶል የስርአቱ ደጋፊዋች ባለአርማውን ወይም ሰይጣን የሰይጣን ምልክትን ያካተተውን ሲያውለበልቡ በዚህ አመት የሰይጣን ቤተመቅደሴ ነው በማለት ያስተዋቀውን ማስታወስ በቂ ነው በዋሽንግተን ዲሲ ሰሞኑን ቤተ መቅደሴን ከፍቻለሁ ምልክቴም ይሄ ኮከብ ነው።


በማለት ለቢቢሲ ይፍ በማድረግ በአለም ዜናውን አሰራጭቶል ይህ የሰይጣን ምልክት ደግሞ በኢትዮጵያ ባንዲራ መሀል ላይ ተለጥፎ ይገኛል በመሆኑም ሀገር ውስጥ በሀይል በህግ በህገወጥ መልኩ በማሰፈራራት እንዲውለበለብ ቢያረግም ከሀገር ውጪ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ግን ባንዲራውን አይቀበሉትም በብዛት ህዝብ የሚቀበለው አርማ የሌለወን .#አረንጎዴ #ቢጫ #ቀይ ሲሆን ብዛት ያለውተቀባይነትም አለው ይሄም ህዝቡን ይወክላል ።ይሄ ሆኖ ሳለ እውነቱ ስርአቱ ግን የብሄረሰቦችን እኩልነት እንዴት እንደሚወክል በፍጹም የማያሳየውን አና ታማኝነት የሌለው ከሃገሪቱ ሃይማኖታዊ ባህላዊ አና ማህበራዊ ዘይቤ ጋር የማይገናኘው ይህ ኮከብ ያለበትን ባንዲራ ሰንቅሮ ሃገራችን ላይ በፍቃድ ያውለበልባል በመሆኑም እኛን የሚወክለን መሀል ላይ ምንም የሌለበት አረንጎዴ ቢጫ ቀይ ነው ሰንደቅ ኣላማ መሃልላይ ያለው ባእድ ምስል መነሳት ኣለበት ::
ህዝብ ሀይል ነው በቅርብ ይቺ ንፁህ የኢትዮጵያ ባንዲራ ትውለበለባለች
ድል የህዝብ ነው #ባንዲራየ #አረንጎዴ #ቢጫ #ቀይ ቅን አሳቢው .#ጥላዬ #ታረቀኝ

Thursday, September 24, 2015

በአየር ኃይልና በሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ውስጥ ያሉት በTPLF ብቻ የተያዙ ከፍተኛ የአዛዥነት ቦታዎች...





የአርበኞች ግንቦት 7 ህዝብ ግንኙነት
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ መንግስት
ክፍል 8

• ብ/ጀነራል መዓሾ ሀጎስ የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ እና የኦፕሬሽን ኃላፊ (ህወሓት)
• ኮ/ል ደሳለኝ አበበ የአየር ኃይል የዘመቻ ዕቅድ መምሪያ ኃላፊ (ህወሓት)
• ኮ/ል ሰለሞን ገ/ስላሴ የማዕከላዊ አየር ምድብ ዋና አዛዥ (ህወሓት)
• ኮ/ል ፀጋዬ አርፋይኔ የማዕከላዊ አየር ምድብ ዘመቻ (ህወሓት)
• ሻምበል ገ/እግዚአብሄር ኃ/ስላሴ የምዕራብ አየር ምድብ 3ኛ ሚሳይል ክንፍ አዛዥ (ህወሓት)
• ሻምበል ዝናቡ አብርሃ የምዕራብ አየር ምድብ የ301ኛ አየር መቃወሚያ አዛዥ( ህወሓት)
• ኮ/ል ኪዱ አሰፋ የምዕራብ አየር ምድብ ምክትል አዛዥ እና የኦፕሬሽን ኃላፊ(ህወሓት)
• ሌ/ኮ ክብሮም መሃመድ የምዕራብ አየር ምድብ ምክትል አዛዥ እና የሎጅስቲክ ኃላፊ (ህወሓት)
• ኮ/ል ኃይሌ ለምለም የሰሜን አየር ምድብ ዋና አዛዥ (ህወሓት)
• ኮ/ል ፀጋዬ ካህሳይ የሰሜን አየር ምድብ ምክትል አዛዥ እና የአስተዳድርና ፋይናንስ ኃላፊ (ህወሓት)
• ኮ/ል አበበ ተካ የምስራቅ አየር ምድብ ዋና አዛዥ (ህወሓት)
• ኮ/ል ሙሉ ገብሬ የምስራቅ አየር ምድብ ዘመቻ ኃላፊ (ህወሓት)
• ሻላቃ ፀጋዘዓብ ካሳ የምስራቅ አየር ምድብ ተዋጊ ሄሊኮፕተር ክንፍ አዛዥ(ህወሓት)
• ሻለቃ ሀብቶም ዘነበ የምስራቅ አየር ምድብ ዘመቻ ምክትል ኃላፊ (ህወሓት)
• በደቡብ ሱዳን አብዬ ሰላም ማስከበር የስምንተኛ ታንከኛ ሻምበል አዛዥ ሻላቃ ተክላይ ወ/ገሪማ (ህወሓት)
• በደቡብ ሱዳን አብዬ ሰላም ማስከበር ምክትል የኃይል አዛዥ ብ/ጀነራል ህንፃ ወ/ጊዮርጊስ (ህወሓት)
• በደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር 9ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ አዛዥ ኮ/ል ጥጋቡ ተወልደ (ህወሓት)
• በደቡብ ሱዳን አብዬ ሰላም ማስከበር 10ኛ ሻለቃ አዛዥ ኮ/ል ገ/ህይወት አደራ (ህወሓት)
• በደቡብ ሱዳን አብዬ ሰላም ማስከበር የ17ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ አዛዥ ኮ/ል መለስ ብርሃን (ህወሓት)
• በዳርፉር የኢትዮጵያ ሰላም ማስከበር ድጋፍ ሰጭ ቡድን አስተባባሪ ኮ/ል ዮሴፍ አሮን (ህወሓት)
• በዳርፉር የ13ኛ ሞተራይዝድ ሰላም ማስከበር ሻለቃ አዛዥ ኮ/ል ተክላይ ወ/ጊዮርጊስ (ህወሓት )
• በዳርፉር የ13ኛ ሞተራይዝድ ሰላም ማስከበር ሻለቃ የዘመቻ አዛዥ ሻለቃ ሀጎስ ነጋሽ (ህወሓት )

Tuesday, September 22, 2015

ፕሮፓጋዳ ዓይን ያወጣ ውሸት ማቅረብ አይደለም።የሚሰራ መሆን አለበት። ጎብልስና ወያኔ

                              

ጎብስ_ደብረጽዮን
ፕሮፓጋዳ ዓይን ያወጣ ውሸት ማቅረብ አይደለም።የሚሰራ መሆን አለበት። ጎብልስና ወያኔ

ከቢላል አበጋዝ
ዋሽግቶን ዲ ሲ
ሰኞ ፣ ሴፕቴምበር 21 ቀን 2015
የወያኔ ትልቁን “ኩዴታ” ጥምረት ውህደትን “በሾኬ የጣለበትን” የወሬ ጋጋታ እንግዲህ አለፍነው። ተመስገን። ሰማይ አልተደረመሰም። የወያኔ ቲቪ ሰዓት እላፊ ሰራ። በዳያስፖራ ያሉ የወያኔ አሽከሮች “የፍየል ወጠጤ” ዓይነት መልክት አስተጋቡ። ወያኔን አትንኩብን አሉ። የአንድን ሰው መክዳትን ድል አድርገው ሊያደናቁሩ ተሟሟቱ። አዲስ የተሻሻለች ህወሃትን የሚሹ ምሁራንም የቆሙበት በግልጥ ታየ። ሌሎችም ጥምረት ውህደቱን ተቹ። ህብረት እንፍጠር ያላችሁ ሳይገባችሁ ነው አሉ። የሞላ መክዳትት ወሬ ጥቂቶችን አናዞ እያለፈ ነው።መጭውን የወያኔ “የረቀቀ ስለላ ውጤት” እስክንሰማ እንጠብቃለን።የሞላ አስከዶም ተገቢው ጎራ መዘነቅ ወሬው ቶሎ ከሰመ::ከዚህ የሚያልፍ አይደለም።ግን መጥኔ ለአዲሳባ!
ፕሮፓጋዳ ጥበብ ነው።ተንኮልም አለበት። ወያኔ ደግሞ በተንኮል እንጂ በጥበብ አይታማም። ፕሮፓጋዳ ዓይን ያወጣ ውሸት ማቅረብ አይደለም።የሚሰራ መሆን አለበት።ፕሮፓጋዳን በስልት ከያዙት ጋር ሲተያይ፡ ወያኔ ዛሬ ገና በድንጋይ ዘመን እየኖረ ነው።የወያኔ ፕሮፓጋዳ በመለስ አገዛዝ ይሻል ነበር።የአስራ አንድ ከመቶው “ዓመት ካመት እድገት”፤”አልሸባብ ሊወረን ነው””በቀን ሶስቴ መብላት”ትዝ የሚሉ ናቸው። ዛሬ በሞላ መክዳት የሆነውን የህወሃት ግርግር መለስን መቃብሩ ውስጥ ሆኖ የሚያወራጨው ነው።የሞላ መክዳት ጊዜ አለመግዛቱን መለስ ቶሎ ይረዳው ነበርና።አንድ የትጥቅ እንቅስቃሴ ብርታቱን የሚያገኘው ወይ በተሰዋ፤ በተሰዋች ጓድ ነው፤ወይ በከዳ፤ በከዳች ጓዲት ድርጊት የአባላት መብገን ነው። ከርእዮትና ከዓላማ ጎን ለጎን እኒህ ያሉት ተጨባጭ ክስተቶች ናቸው ትግልን ወደፊት የሚገፉት።የሞላ አስከዶም መክዳት በጊዜ መሆኑ ከፍ ካለ ጥፋት የሚሰውርና ለደምሂት ሰራዊት ጠብቆ መዋቀሪያ እድል ማስገኘቱ ይታመናል። ታች ከምናየው የፕሮፓጋዳ ሊቅ ከነበረው የአዶል ሂትለር ባለሟል አባባል ብዙ ታዝበን የወያኔንና አሽቃባጮቹን ጅል ድርጊት እንታዘባለን።ህዝባዊ ትግል የተራ ፕሮፓጋንዳ ሰለባ የሚሆነው በህወሃቶች ጭቅላት ውስጥ ብቻ ነው።ህዝባዊ ትግል በተራ ፕሮፓጋዳ የሚገታ ቢሆን እንዴት ከየካቲት ስልሳ ስድስት አንስተን ከዚህ ደረስን? ፕሮፓጋዳንና ድንፋታ ለደርግ የእለት ተለት ተግባር አልነበረም ?እስቲ  ወደ ዮሴፍ ጎብልስ እንሂድ። እሱ እንዲህ ይላል፡
“ፕሮፓጋዳ ሰዎችን መሳብ፤ማሳመን እውነት  ነው ብየ ለተቀበልኩት፤ ይህ ነው ፕሮፓጋዳ ማለት ። ሲጀመር መግባባት አለ። ይህ መግባባት ፕሮፓጋዳን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ መግባባትን(ስብከትን) ወደ ፖለቲካ ይቀይረዋል።ማቸነፍ ዋናው ነገር ነው።ፕሮፓጋዳ የተራ ሰዎች ምግባር አይደም።የሙያተኞች ነው።ደስ የሚል ወይም በንድፈ ሃሳብ ትክክል መሆን የለበትም። የሚያስደንቁ፤የተዋቡ ንግግሮችን ባደርግ ሴቶችንም እምባም ባስረጭ ግድ አሰጠኝም።የፖለቲካ ንግግር ዓላማው ማሳመን ነው።እኛ ትክክል ነው የምንለውን።ክፍለ ሃገር ሆኘ የምለው በርሊን ሆኘ ከምለው ይለያል።ቤይሩት ሆኘ የምናገረው ፋረስ አዳራሽ ሆኘ ከምለው አይመሳሰልም።ይህ የንድፈ ሃሳብ ሳይሆን የተግባር ጉዳይ ነው። የጥቂት ገልጃጆች ማህበር ሳይሆን ሰፊውን ህዝብ የሚያንቀሳቅስ ነው የምንሻው።ፕሮፓጋዳን ተቀባይነት ሊኖረው ይገባል። አእምሮን ማራኪ መሆን የለበትም።የፕሮፓጋዳ ተግባር ምሁራዊ እውነቶችን መፈተሽ አይደለም።እዲህ ያለው ፍተሻ የራሱ ጊዜና ቦታ አለው።እኔ እዲህ ያለውን እውነት የምፈትሸው ከቢሮዬ ተቀምጨ  እንጂ ከስብሰባ አዳራሽ ሆኘ አይደለም።”(1)
ወያኔ ህውሃት በሙስና የተዘፈቀና የተጠላ መንግስት ነው። ፕሮፓጋዳ አያሰነብተውም። ከላይ የጠቀስኩት ዮሴፍ ጎብልስ የናዚን ፓርቲ አላዳነም።ጎብልስን የጠቀስኩት ወያኔዎች የምትሰሩት የገልጃጃ ስራ እንጂ ፐሮፓጋንዳ አይደለም ለማለት ነው።ስራችሁ አያተርፍም።ዙሪያው ገደል ሆኖባችኋል። ከጭካኔአችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ በውሸታችሁ ነው የሚለያችሁ።ስለዚህ በጥቅም ከምትደልሉት በተቀር ሌላው ዛሬ በምን ይደግፋችሁ?ይህ የናተው ግዛት ሲያልፍ(በቅርቡ) “የውሸት ዘመን” የሚባል ታሪክ ይነገራል ብንል ስተት አይሆንም።የወያኔ ፕሮፓጋንዳ የቱ ይማርካል? ከህወሃት አበደን ምንም አይወጣም። ሺ ደምስ ቢለጠም ስኒ የምትሞላ አያመርትም።የህወሃት ፕሮፓጋዳ እውር ሌላውን እውር የሚመራበት ድራማ ነው።
ማንም ደካማ መንግስት በፕሮፓጋዳ አልዳነም።ወታደራዊ ደርግንም ፕሮፓጋዳ አልታደገውም።ዋንቻው  ዮሴፍ ጎብልስ እና ጌታውንም አላዳነም። ታአማኒነት ከሌለ ፕሮፓጋዳ ዋጋ የለውም። ተአማኒነት ታገኙበት የነበሩት ሃያ አራት ዓመታት አባክናችኋል።ተቃዋሚው እውነት ከሱ ጎን ስለሆነች ፕሮፓጋዳ አይነዛም።ራቡ እውነት ነው።የኑሮ ውድነቱ የሚታይ ነው።ስደቱ ምስክር አያስጠራም።መፈናቀል፤ሰቆቃ፤ግድያው ያንገሸግሻል።ህዝቡ በምቾት ተንደላቃችሁ በሙስና ተጨማልቃችሁ እንቀጥላለን በሚል ተስፋ የምትወራጩትን ህወሃቶች ይገረምባቸዋል።”እኒህ ጉዶች !” ይላል።እያለ እንደከረመው።
የሰሞኑ ወሬ መሰረት የሆነው ሞላ አስገዶም አሳዛኝ ነው።እንዴት ዓላማውን እንኳን አፍታቶ ማስረዳት የማይችል ሰው የሞቀ ኑሮውን ለዓላማው ሲል ሁሉን ትቶ በረሃ የወረደውን ይዘልፋል?እንደ አንድ ህብረተሰብ ወያኔ(መለስ) ከመጣ ወዲህ የነገሰው ጻረ ምሁርነት ውጤት ነው።ሞላም የዚህ ዝቅጠት ውጤት ነው።ወያኔ ያልተረዳው እንደ ህዝብ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ከጊዜያዊ ወሬ ሸመት ማለፋችንና ውጤት ተኮር መሆናናችንን ነው።ድንበር ቆርሶ ሰጥቶ፤አርሶ አደሩን(ሃረሽታይ!)ከመሬቱ አፈናቅሎ ለውጭ ከበርቴ ቸብችቦ ስለ አገር አለማፈራረስ ማውራት እብደት ነው።እብዶች ስልጣን የያዙባት አገር ዛሬ ኢትዮጵያ ናት። ይህ ደግሞ አስጊ ነው። ለመሳለቅ አይደለም::ህወሃት በስልጣን ከቀጠለ ሊሆን የሚችለው ዘግናኝ ነው።
እስቲ ይህን እንጠይቅ።ደምሂት አስራ አራት ዓመት የፈጀ የንቧይ ካብ ነው የሞላ አስከዶም ባንዴ የሚንደው?ይህ እራሱንስ ሞላን አያስገምተውም ?እሺ ሰባት መቶ አስከትሎ ከዳ የተባለውን ብናምን አብዛኛውን ጦር ይዞ እንዳልወጣ የሚያመላክተው ወዲያው በማግስቱ ስለሌላ ውጊያ ሰማን።ገና ደግሞ ዝርዝሩን እንሰማ ይሆናል።አንድ ቀን ደግሞ አንድ የአውሮፓ ወይም የሌላ አገር ጋዘጠኛ ሁሉን ይዘረዝረው ይሆናል። ልክ ስዊድናውያኑ እነ ሺብዬ የኡጋዴኑን የወያኔ ግፍ እንደዘረዘሩት ማለት ነው።ምናልባት የሞላም ወታደራዊ ወንጀል ይዘከዘክ ይሆናል።
ሞላ ወንጀል ፈጽሟል።ለራሱ ምቾት በማድላት ጔዶቹን ከድቷል።የሞራል ብቃት፡የአስትሳሰብ እርጋታና ማጣቱና  ከቅሌት አለመራቁ በጣም አዋርዶታል።የህወሃት መሪዎች ከተዘቀጡበት ቁልቁለት ይዘውት ተንሸራተዋል።ሞላ ሌላው ቀርቶ እዚያው አስራ አራት ዓመታት አባክኖ ከሄደበት አገር የነበረው ታሪክ ያገናዘበ አልመሰለኝም።በ1980 መጀመሪያ የጀብሃ ወይም የኢልፍ ጦር ተበተነ።ትልቅ ገናና ጦር ነበር።ግን ኤርትራ የነበረውን ሁኔታን አልወሰነም።ጦርነትም አልቆመም።ታሪክ ጉዞውን ቀጠለ።እኔ እስከማውቀው በራሳቸው ድክመት የጠፉ የትጥቅ እንቅስቃሴዎች ጀብሃ፤ኢህአሰ እና የታሚል ነብር ይባሉ የነበሩ የሲሪላንካ ተዋጊዎች ነበሩ።የተቀረው ለታሪክ ምሁራን እተዋለሁ።መልእክቴ ጦር እዲህ በዋዛ አይበተንም።ነገ ጎንደር፤ትግራይ ወሎ ላይ ሲያርበደብዳችሁ የማን አገር ጦር መጣብን ልትሉ ይሆን? ይህን ጎርፍ በዛሬው ውሸት ልትገድቡት?ሰዓት ቆጣሪ ዘግን በእጅ በመያዝ የጊዜን(ታሪክን)ግስጋሴ ማቆም ይቻላልን?
የኤርትራ መንግስት የኢትዮጵያ መበታተን ዓላማው ከሆነ ህብረት ጥምረት ከጓሮው እንዲበቅል ለምን ይፈቅዳል?ማነው የመበታተንን፤የመክፋፈልን እቅድ በመንግስት ደረጃ የሰራበት ወያኔ ወይስ በሙስና ያልታማው የኤርትራ መንግስት? የኤርትራ መንግስት የወያኔ ወዳጅ ነበር።ይህን እናውቃለን። ዛሬ ግን አይደለም።በወያኔና በኤርትራ መንግስት መካከል ያጥፊና ጠፊ ቅራኔ ነው ያለው።የጥምረት ውህደት ሀይሎች ይህን ሳይገነዘቡ የዓመታት ጥረት አላደረጉም።ጋዜጠኛ ነኝ ያለ እንደ ኢሳት መሄድ የሚከለክለው አለ ማለት አይቻልም።አይቶ ነው ማውራት።የተረፈው የሻይ ስኒ ውስጥ ማእበል ነው።
ወያኔ ህወሃት ከኤርትራ በኩል ከሚመጣበት ጥቃት ይልቅ የራሱ ጉድለት ቁልቁለት እያወረደው ነው::የጥንታዊ ገናናው የሮማውያን አገዛዝን ምን ምክንያቶች ጣሉት?ሞላ አስገዶም አንዳንዴ እንኳን እያነበበ፤ እየተማረ ቢሆን ኖሮ በኤርትራ የቆየው የሮማውያን አገዛዝ ከአምስት መቶ የገነነባቸው ዓመታት በኋላ የተንኮታኮተው በሙስና፤በኑሮ ውድነት፤ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና  ወታደራዊ ሽንፈቶች መሆኑን ይረዳ ነበር። የህወሃትም እጣ ይህ እንደሆነ ይረዳ ነበር።ጣሊያን በምን ምክኛት ሊቸነፍ በቃ? በሰራው ግፍ አልነበረም?
ሞላ ሲከዳ በኤርትራ የተመቸ ኑሮውን ነው ያስታወሰው።ጓዶቹ የተጋዳይ ኑሮ እሱ ተንደላቆ እንደነበረ ተናግሯል።ይችኑ ምቾት ፍለጋ ህሊናውን ሸጠ።የትግሉ የታሪክ ጉዞ ግን አይቆምም።የሞላ አስከዶም ተገቢው ጎራ መዘነቅ ወሬው ቶሎ ከሰመ::የወያኔ የጅል ፕሮፓጋ መሪ ተዋናይ በመሆን የአስራ አራት ዓመታትን ትግል በክዳት መደምድም ዝቅ ያለ የአእምሮ እሴት ውጤት ነው።ወያኔ አይለወጥም።አይታረምም።አያቸንፍም።ፕሮፓጋዳው ጅል ነው!
1)     https://en.wikiquote.org/wiki/Joseph_Goebbels

አነድነት ሀይል ነው!
ድል ለመብቱ ለነጻነቱ እየታገለ ላለው የኢትዮጵያ ህዝብ!
ኢትዮጵያ  በህዝቦችዋ አንድነትና ፍቅር ለዘለዓለም በነጻነት ትኑር!

የተናገሩት ከሚጠፋ . . . በኤፍሬም ማዴቦ


ephrem-madebo
የተናገሩት ከሚጠፋ . . .
በኤፍሬም ማዴቦ                                                                      
ባለፈዉ መጣጥፌ “ቃል የእምነት ዕዳ ነዉ” ብዬ ጀምሬ “ቃላችን አይለወጥ” ብዬ ነበር የተለየኋችሁ። አለምክንያት አልነበረም እንዲህ ያልኳችሁ፤ በአንድ በኩለ ቃል መከበርም መከፈልም ያለበት ዕዳ ስለሆነ በሌላ በኩል ደግሞ ቀትር ላይ የገባዉን ቃል ሳይመሽ እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ የሚክድ ብዙ ቃላ አባይ ሰላለ ነዉ። አገሬን ከወያኔ አጸዳለሁ ብሎ ቃል የሚገባ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዕዳ አለበት። ዕዳዉ ደግሞ ገንዘብ ወይም ንብረት አይደለም። ቃሉን መጠበቅ ወይም ቃሉን ማክበር ነዉ። ደግሞም አንድ ሰዉ የተናገርዉን ቃል ሰብሮ የእምነት ባለዕዳ ከሚሆን ዕድሜ ልኩን የገንዘብ ባለዕዳ ቢሆን ይሻለዋል። የገንዘብ ዕዳ ቆይቶም ቢሆን ይከፈላል ወይም አበዳሪዉ ሊምረን ይችላል፤ የዕምነት ዕዳ ግን የማይሽር ጠባሳዉ እየቆረቆረን አብሮን ይኖራል እንጂ አይጠፋም። ማንም ሰዉ ለአገሬ ህይወቴን እሰጣለሁ ብሎ ቃል ሲገባ መሃላዉ ከህዝብና ከአገር ጋር ብቻ አይደለም፤ እንዳዉም የሰዉ ልጅ ቃል የሚገባዉ መጀመሪያ ከራሱ ጋር ነዉ። ለራሱ የገባዉን ቃል የማያከብርና ቃሌ ቃል ነዉ ብሎ የገዛ ራሱን የእምነት ዕዳ ያልከፈለ ሰዉ ለህዝብና ለአገር ቃል መግባት አይችልም። ዛሬ ወያኔን እናጥፋ ብሎ ካራ ጨብጦ አብሮኝ የቆመ ሰዉ ነገ ከወያኔ ጋር ሆኖ ካራዉን እኔዉ ላይ አዙሮ ባየዉ እሱ ቀድሞዉንም ካራ የጨበጠዉ ወያኔን ለማጥፋት ሳይሆን ስጋ ሊቆርጥብት ነዉና ብዙ አይገርመኝም። እንዲህ አይነቱን ለቁም ነገር ሲፈልጉት አልሰማ ብሎ ሆዱ ሲሞላለት ግን ሳይጠሩት አቤት የሚል ስጋ ወዳድ ሆዳም ደግሞ ኢትዮጵያ በየዘመኑ አፍርታለችና ብዙ ሊገርመን አይገባም።  ከሰሞኑ ከምድረ ኤርትራ የነፈሰዉ ነፋስ ያስተማረን አንድ ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር እንዲህ አይነቱን ሞላ ጎደለ የሚባል የካራና የስጋ ጨዋታ ነዉ። አዎ! የካራ ጨወታ – ወዲህ ማዶ ስጋ ሊቆርጡበት ወዲያ ማዶም ስጋ ሊቆርጡበት።
“የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ” . . . ገዢዎቻችን በተለይ የዛሬዎቹ ቃል አባዮች እንደቆሻሻ ዕቃ መሬት ላይ ጣሉት እንጂ ቃል የዕምነት ዕዳ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ዘመን አይሽሬ የአገራችን አባባል ነዉ። አባቶቻችን የተናገሩትን ወይም ቃል ገብተዉ የተማማሉትን ነገር ከሚያጥፉ የወለዱትን ማጣት ይቀላቸዋል። እኛ ልጆቻቸዉ ግን ከዬት የመጣን ጉዶች አንደሆንን አላዉቅም ቃል አባይነታችን እኛን፤ ልጆቻቸንና አገራችንን ሲያጠፋ በአይናችን እያየን ቅር እንኳን አይለንም። “እመጣለሁ ብሎ ሰዉ እንዴት ይዋሻል፤ ማበል እንኳን አንቺን ምድር ያበላሻል” መሬት ላይ ጠብ የማይል ትክክለኛ አባባል ነዉ። አገራችን ኢትዮጵያ ትናንት እንሞትልሻለን ብለዉ ዛሬ በሚገድሏት ቃል አባይ ልጆቿ እየተበላሸች ነዉ። እነዚህ ቃልአባዮች የኢትዮጵያን የምድር ላይና የምድር ዉስጥ ኋብቷን አንጂ የገረጣዉን ፊቷን ማየት አይፈልጉም- አዎ ወያኔ የሚያየዉ ኃብትሽን፤ የሳዑዲዉ ሰዉ ወርቅሽን፤ ባዕድ ከበርቴዉ ለምለም መሬትሽን . . . ወይኔ ኢትዮጵያ ማን ይሆን የሚያየዉ የጠቆረዉ ፊትሽን፤ ማን ይሆን የሚያብሰዉ እምባሽን፤ እኮ ማን ይሆን የሚያቆመዉ መከራሺን . . .  ማን ይሆን?. . . ማን ይሆን?
የዛሬዋ ኢትዮጵያ አንድ ትዉልድ ዉሸት ብቻ እየሰማ ያደገባት የዉሸት መዲና ሆናለች። ጳጳሱ፤ ቄሱና ፓስተሩ “እኔ መንገድ፤ አዉነትና ህይወትና ነኝ” ያለዉን የሰማዩን አምላካቸዉን ረስተዉ ለምድር ዉሸታሞች አደሩ። ሂዱና ዋሹ ሲባሉ ሄደዉ ዋሹ፤ እዉነትን በዉሸት አስተባብሉ ሲባሉ አስተባበሉ፤ በሀሰት መስክሩ ሲባሉ አፋቸዉን ሞልተዉ በሀሰት መሰከሩ።  “ታላቁ መሪ” እየዋሸን ኖሮ እየዋሸን ሞተ። መታወቂያዉ ዉሸት ነዉና ሞቶም አልሞተም ተብሎ ተዋሸለት። ከአህያ ጋር የዋለች ጊደር ምን ለምዳ ትመጣለች እንዲሉ ሌላ ሁሉ ቢቀር ዉሸትን ይፀየፋል ተብሎ የተነገረለት የዛሬዉ ጠ/ሚኒስቴር ጭራሽ “ታላቁን መሪ” እንደዋቢ እየጠቀሰ ስራዉ ሁሉ ዉሸት፤ ዉሸት፤ ዉሸት ብቻ ሆኖ ቀረ። የኢትዮጵያ ሬድዮ ሲከፈት ዉሸት ይናገራል፤ ሲዘጋ ደግሞ ነገ ስለሚዋሸዉ ዉሸት ያስባል። ጋዜጦች በስህተት አንኳን እዉነት አይጻፍባቸዉም። የኢቲቪ ዜና አንባቢ ተመስገን በየነ ግማሽ ሰዐት የዋሸዉን ዉሸት ለማካካስ ዜናዉን አንብቦ ሲጨርስ ለ15 ደቂቃ ጎንበስ ብሎ ይሰግዳል።
ለረጂም ግዜ ተማምነን ጀርባችንን የሰጠነዉ ሰዉ ለጠላት እጁን ሰጥቶ ጦርነት ሲያዉጅብን አንዳንዴ በትግሉ ዉስጥ ማንን አምነን ጀርባችንን እንደምንሰጠዉ ግራ ሊገባን ይችላል። ከሰሞኑ የሰማነዉ ዜና እንዲህ ግራ የሚያጋባ ዜና ነዉ። ሆኖም ሳንተማመን ትግል ብሎ ነገር የለምና የትግል ጓዶቻችንን ማመን ብርታት እንጂ ደካሞች እንደሚሉት ሞኝነት ወይም የዋህነት አይደለም። በጓዶቻችን ላይ ክህደት ፈጽመን ከምናሰቃያቸዉ እኛ ብንሰቃይ ይሻላል፤ ደግሞም ጓዶቻችንን ማመን አቅቶን በጥርጣሬ ተፋጥጠን ባለንበት ከምንረግጥ አንዳንዴ አዉቀንም ቢሆን ብንታለል ብዙ መንገድ መጓዝ እንችላለን። ትግል በተለይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ከሚያስተምረን ትምህርቶች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ሌሎች በኛ ላይ እምነት እንዲኖራቸዉ ከፈለግን እኛ አስቀድመን ልናምናቸዉ አንደሚገባን ነዉ። አለዚያ ሁለታችንም አንተማመንም። አለመተማመን ደግሞ ያጠፋፋናል እንጂ አንድ ቤት ዉስጥ አብሮ አያኖረንም። እንደኔ እንደኔ የወያኔን ስርዐት ደምስሰን ኢትዮጵያን የእኩሎች አገር የምናደርጋት እያንዳንዳችን ለትግል ጓዶቻችን የገባነዉን ቃል ሰብረን ረጂም ህይወት ከመኖር ቃላችንን አክብረን ዛሬዉኑ መሞትን ስንመርጥ ብቻ ነዉ። ወያኔ አንደ እሳት የሚፈራዉና በፍጹም የማያሸንፈዉ አንዲህ አይነቱን ከብረት የጠነከረ ጽኑ አቋማችንን ብቻ ነዉ። ለዚህ ነዉ እንዲህ አይነት ጽናት የሌላቸዉን ደካማ ግለሰቦች ፈልጎ እያማለለ ጽናታችንን የሚፈታተነዉ። ከሰሞኑ ለህዝብ ከመታገል ህዝብን መታገል መርጦ ከለየላቸዉ የህዝብ ጠላቶች ጋር የተቀላቀለዉ ሞላ አስገዶም ለዚህ ዉሳኔ የበቃዉ ህዝባዊዉ ትግል የሚፈልገዉ የአለማ ጽናት የሌለዉ ደካማ ግለሰብ ስለሆነ ብቻ ነዉ። ዉድ ኢትዮጵያዉያን ክህደት ትናንት ነበር፤ ዛሬ አለ፤ ነገም ይኖራል። ስለዚህ ክህደት ሊያስተምረን እንጂ በፍጹም ሊያስበረግገንና አንገታችንን ሊያሰደፋን አይገባም። ክህደትና ከሀዲዎችን እያሰላሰልን የምንኖር ከሆነ የበለጠ እንዲጎዱን ተጨማሪ ዕድል እንሰጣቸዋለን እንጂ ሌላ ምንም የምንፈይደዉ ፋይዳ የለም።
ሞላ አስገዶም እሱን የመሰሉ ደካማ ጓደኞቹን ከተቀላቀለ በኋላ መቀሌ፤ አዲስ አበባና አዳማ ዉስጥ ክህደቱን አስመልክቶ እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ሦስት ጋዜጣዊ መግለጫዎችን ሰጥቷል። እርግጠኛ ነኝ ይህ ቁርስ ላይ የተናገረዉን ምሳ ላይ የማያስታዉስ ግለሰብ በተያዘለት የጉብኝት ሰሌዳ መሠረት ዘጠኙን ክልሎች የሚዞር ከሆነ ዘጠኝ የተለያዩና እርስ በርሳቸዉ የሚጣረሱ ምክንያቶችን መደርደሩ አይቀርም። የወያኔ የመረጃና የደህንነት መ/ቤት ተብዬዉም ቢሆን ምን ያህል የዉሸትና የጉራ ቤት ለመሆኑ መረጃ ብሎ የለቀቃቸዉን ዉሸቶችና ቱልቱላዎች መጥቀሱ ይበቃል። ለምሳሌ የመረጃና ስለላ ድርጅቱ ከአንድ አመት በላይ ከሞላ አስገዶም ጋር በሚስጢር ይሰራ እንደነበር ተናግሯል። ይህ እዉነት ከሆነ የደምህት ታጋዮች በዚህ አንድ አመት ግዜ ዉስጥ በወያኔ ታጣቂዎችና ወታደራዊ ጣቢያዎች ላይ ለወሰዷቸዉ እርምጃዎች በተለይ እግር ኳስ ጨዋታ በመከታተል ላይ እንዳሉ ለወሬ ነጋሪ ሳይቀር እንዳለ ለተደመሰሱት የኢትዮጵያ ወታደሮች ተጠያቂዉ ከሞላ አስገዶም ጋር ይሰራ የነበረዉ የወያኔ የመረጃና የስለላ ድርጅት ነዉ ማለት ነዉ።

ሞላ አስገዶም ትናንት ከኛ ጋር ሆኖ እኛ ሲል ነበር፤ ዛሬ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጠለቶች ጋር ሆኖ እኛ ይላል። ይህ ሰዉ  “እኛ” ሲል የሱ እኛ እነማንን እንደሚያጠቃልል አይታወቅም፤ እሱ እራሱም የሚያዉቀዉ አይመስለኝም። ሞላ አስገዶም ወያኔን እንደተቀላቀለ አፉን ሞልቶ ጥምረቱን የፈጠርነዉ “እኛ” ነን ብሎ ሲናገር በተደጋጋሚ ተደምጧል። ጥምረቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎትና ህዝባዊ ትግሉ የደረሰበት የዕድገት ደረጃ ዉጤት ነዉ እንጂ ሞላ አስገዶም ስለፈለገዉ የሚፈጠር አለዚያ የሚቀር የሞላ አስገዶም የቤት ዉስጥ ዕቃ አይደለም። ደግሞም እንደ ሞላ አስገዶም ፍላጎት ቢሆን ኖሮ የደምህት ጥምረቱ ዉስጥ መግባት ለግዜዉም ቢሆን ሊዘገይ ይችል ነበር። ደምህት ጥምረቱ ዉስጥ ገብቶ አገር አድን የጋራ ንቅናቄዉ የተፈጠረዉ የደምህት ሠራዊትና ከሞላ አስገዶም ዉጭ ሁሉም የደምህት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ከሌሎች ኢትዮጳያዉያን ወገኖቻቸዉ ጋር ሆነዉ በጋራ ለመታገል በመወሰናቸዉ ነዉ። የሞላ አስገዶም ፈርጥጦ ወያኔ ጉያ ዉስጥ የመሸጎጡ ዋነኛዉ ምክንያትም የዚህ ዉሳኔ ዉጤት ነዉ እንጂ የወያኔ መረጃና ስለላ ድርጀት ሚስጥራዊ ግንኙነት ዉጤት አይደለም። ሌላዉ እርስ በርሱ የሚጋጭ የወያኔ ዉሸት –  በአንድ በኩል ሞላ አስገዶምና የደምህት ሠራዊት ሙሉ ትጥቃቸዉን እንደታጠቁ ጠቅልለዉ ወደ አገራቸዉ ተመለሱ የሚለዉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቁጥሩ ወደ 700 የሚጠጋ የደምህት ሠራዊት ወደ አገሩ ተመለሰ የሚለዉ የተምታታ ዘገባ ነዉ። እዚህ ላይ የደምህትን ሠራዊት ብዛት መናገሩ አስፈላጊ ባይሆንም ግንዛቤ ማግኘት የፈለገ ሰዉ ግን ተመድ ያወጣቸዉን ሪፖርቶች መመልከቱ የሚበቃ ይመስለኛል። ደግሞም ሞላ አስገዶም አታልሎ መንገድ ካስጀመረዉ ሠራዊት ዉስጥ ገሚሱ ወደ ትግሉ ሜዳ ተመልሷል፤ የተቀረዉ ደግሞ ወደ ትግሉ ሜዳ ካልተመለስኩ እያለ ከሱዳን ባልስልጣኖች ጋር እየተደራደረ ነዉ። በነገራችን ላይ የዚህ ጽሁፍ ጸሀፊ ሞላ አስገዶም አታልሎ ሀምዳይት ከወሰዳቸዉ በኋላ ትግል ወይም ሞት ብለዉ ተመልሰዉ ከትግል ጓዶቻቸዉ ጋር ከተቀላቀሉ ጀግኖች ኢትዮጵያዉያን ጋር አብሮ ቡና ጠጥቷል።

ጓዜን ጠቅልዬ ትግሎ ሜዳ ከመግባቴ በፊትም ሆነ ከገባሁ በኋላ የደምህት ስም በተነሳ ቁጥር አብረዉ የሚነሱ ሁለት መላምቶች አሉ። አንደኛዉ መላምት ደምህት የኤርትራ መንግስት ሆን ብሎ የፈጠረዉና ጭራሽ ኤርትራ ዉስጥ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎችን ተክቶ በመንግስታዊ ተቋሞች ጥበቃና ደህንነት ስራዎች ላይ የተሰማራ ድርጅት ነዉ የሚል መላምት ሲሆን ሁለተኛዉ መላምት ደግሞ ሞላ አስገዶም በኤርትራ መንግስት ድጋፍ ሁለተኛዉ መለስ ዜናዊ ሆኖ ህወሃትን ተክቶ አትዮጵያን ይመራል የሚለዉ መላምት ነዉ። ደግነቱ የነዚህ መላምቶች የማዕዝን ራስ የሆነዉ ሞላ አስገዶም ኮብልሎ ወያኔን መቀላቀሉና ከተቀላቀለ በኋላ የሰጣቸዉ ጋዜጣዊ መግለጫዎች ሁለቱንም መላምቶች እንዳልነበሩ አድርጓቸዋል። እኔን አልገባ ያለኝና በጣም የሚገርመኝ ግን በአንድ በኩል የኤርትራ መንግስት የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች ትብብር እንዲፈጥሩ አይፈልግም ይባላል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ጥምረቱ የተፈጠረዉ በሻዕቢያ ግፊት ነዉ ይባላል። መቼም ገና በልጅነቴ ካልጃጀሁ በቀር ሻዕቢያና የኤርትራ መንግስት መሃል ልዩነት ያለ አይመስለኝም። ሌላዉ የሰሞኑ አስቂኝ ድራማ ደግሞ ሞላ አስገዶም ጥምረቱን የፈጠርነዉ እኛ ነን ሲል የሱን መኮብለል አስመልክቶ የሚሰጠዉ አስተያያት ደግሞ ሞላ አስገዶም ጨርቁን ጠቅልሎ ወያኔን የተቀላቀለዉ ብርሀኑ ነጋ በኤርትራ መንግስት ግፊት የጥምረቱ ሊ/መንበር መሆኑ አልዋጥ ብሎት ነዉ ይባላል።

ሌላዉ አሁን በቅርቡ ወይም ከሞላ አስገዶም መኮብለል በኋላ የተጠነሰሰዉ መላምት ደግሞ ደምህቶች እራሳቸዉ ኤርትራ ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ድርጅቶች በወያኔ ስርዐት ላይ ወታደራዊ እርምጃ መዉሰድ እንዳይችሉ ሆን ተብለዉ በወያኔ የተፈጠሩ እንቅፋቶች ናቸዉ የሚለዉ መላምት ነዉ። በኔ ግምት ይህኛዉ መላምት ከሁሉም መላምቶች የከፋና እጅግ በጣም አደገኛ የሆነ ጽንፈኛ መላምት ነዉ። እንደዚህ መላምት ፈጣሪዎች አባባል የትግራይ ህዝብ በህወሃት አመራር በደል አይደርስበትም ወይም የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቹና እህቶቹ ጋር ሆኖ የህወሃትን ግፈኛ ስርዐት አይታገልም ማለት ነዉ። እንዲህ አይነቱ ጭፍንነትና ጠባብነት የሚመነጨዉ ደግሞ ሞላ አስገዶምንና ደምህትን ወይም ህወሃትንና የትግራይን ህዝብ ለያይቶ ማየት ካለመቻል አባዜ ነዉ። በደርግ ስርዐት ዉስጥ ጭቆናዉና በደሉ በዛብኝ ብሎ ጠመንጃ ያነሳዉ ጀግናዉ የትግራይ ህዝብ ህወሃት ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹ ተነጥሎ እንዲታይ ለማድርግ የሚሸርብበትን ሤራና የሚያደርስበትን ግፍና መከራ አፉን ዘግቶ የሚቀበልበት ምንም ምክንያት የለም። ስለዚህ ደምህት የትግራይ ህዝብ ብሶትና ምሬት አምጦ የወለደዉ ፀረ ህወሃት ንቅናቄ ነዉ እንጂ ወያኔ የፈጠረዉ ድርጅት አይደለም፤ሊሆንም አይችልም። ሞላ አስገዶምም ቢሆን የራሱ የተጠረቃቀመ ድክመት ከንቅናቄዉ ሊ/መንበርነቱ እንደሚያስነሳዉ ሲያዉቅ የፈረጠጠ ፈርጣጭ እንጂ እሱና ወያኔ እንደሚሉት የአንድ አመት ቀርቶ የአንድ ወርም ተከታታይ ግንኙነት አልነበራቸዉም።

ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረከ ብቅ ብለዉ የጠፉትንም ሆነ ዛሬም ድረስ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች ባህልና ድርጅታዊ አሰራር ስንመለከት የድርጅቶች ህልዉና መመዘኛና የማንነታቸዉ መለኪያ ቆምንለት የሚሉት አላማ ሳይሆን የመሪዎቻቸዉ በተለይ የዋናዉ መሪ ተክለሰዉነት ነበር። የድርጅት ወይም የፓርቲ ሊ/መንበር ከድርጅቱ ባለይ ነዉ፤ እሱ ይሁን ያለዉ ይሆናል፤አይሁን ያለዉ አይሆንም። ብዙ ግዜ የድርጅት/ፓርቲ ሊ/መንበር ድርጅቱን የማፍረስ አቅም ጭምር አለዉ። ይህንን ደግሞ በቅርብ ግዜ ታሪካችን በተደጋጋሚ አይተናል። አንድን ድርጅት ወይም ፓርቲ አባላት ሲቀላቀሉ የሚመለከቱት የፓርቲዉን ሊ/መንበር እንጂ የፓርቲዉን የፖለቲካና የኤኮኖሚ ፕሮግራም አይደለም። የፓርቲ ሊ/መንበርም ቢሆን የኔ የሚላቸዉን ሰዎች ነበር እየመረጠ የሚያሰባስበዉ። እንደዚህ አይነቱ የፓርቲ አደረጃጀትና አሰራር አሁን እየተቀየረ የመጣ ቢሆንም ለረጂም ግዜ የፖለቲካ ትግላችን ችግር ሆኖ ቆይቷል። ሞላ አስገዶም በቅርቡ የደምህትን ሠራዊት ከነሙሉ ትጥቁ ይዤ ኢትዮጵያ ገባሁ ብሎ በድፍረት የተናገረዉ ንግግር ይሄዉ የድርጅት ሊ/መንበር ያሰኘዉን ሁሉ ማድረግ ይችላል የሚለዉ የቆየ የፖለቲካ ባህላችን በሽታ ተጠናዉቶት ነዉ። “ዝንጀሮዉን ከጫካ ያዉጡታል እንጂ ጫካዉን ከዝንጀሮዉ ዉስጥ አያወጡትም” የሚል ብህል አለ፤ ትክክለኛ ብህል ነዉ። ሞላ አስገዶም ህወሃት/ወያኔ የኢትዮጵን ህዝብ በአጥር እየለያየ በትናናንሽ ጎጆዎች ዉስጥ ማኖሩ አልዋጥ ብሎት ሁሉንም የሚያቅፍ ሰፊ ቤት ሰርተን ኢትዮጵያን የዲሞክራሲ አገር እናደርጋለን ብሎ ለብዙ አመታት የታገለ ሰዉ ነዉ። ችግሩ ሞላ አስገዶም ነዉ ከነዚያ ትናንሽ የወያኔ ጎጆዎች የወጣዉ እንጂ ትናንሽ ጎጆዎቹ ከሞላ አስገዶም ዉስጥ ስላልወጡ እንደ ማግኔት እየሳቡት ወደነበረበት ቦታ መልሰዉታል። ለሁሉም የሞላ አስገዶም ታሪክ ሲጻፍ – መጣና ሄደ ከሚሉ አምስት ሆሄያት የዘለለ ምንም ቁም ነገር የለዉም። እየመጡ መሄድና እየሄዱ መምጣት ደግሞ ትናንሽ ቤት የሚናፍቃቸዉ ትናንሽ ሰዎች እስካሉ ድረስ ይቀጥላል።

ሁለት ሺ ሰባት ሊጠናቀቅ ሦስት ቀን ሲቀረዉ አንድ የብዙ ኢትዮጵያዉያንን ጆሮ የሳበ ዜና ቴሌቪዥኑን፤ ሬድዮኑን፤ ጋዜጣዉንና ድረገጹን ተቆጣጠረዉ። ዜናዉ የወያኔ/ህወሃትን ስርዐት በመሳሪያ ኃይል የሚታገሉ አራት ድርጅቶች አገር አድን የጋራ ንቅናቄ ፈጠሩ የሚል የአዲስ አመት የምስራች ነበር። የኢትዮጵያ ህዝብ ለረጂም ዘመን የናፈቀዉ የምስራች ነበር። ግን ምን ያደርጋል – በጥባጭ እያለ ንጹህ ዉኃ አይጠጣምና ይሀንን የአዲስ አመት የምስራች ሰምተን ሳናጣጥም ነበር የሞላ አስገዶምን ዜና ክህደት የሰማነዉ። አስደንጋጭ ዜና ነበር። በእርግጥም የአራት ድርጅቶች ጥምረት ተፈጠረ የሚል ዜና በተሰማ ማግስት የጥምረቱ ምክትል ሊ/መንበር ሠራዊት እየመራ ሄዶ ወያኔን ተቀላቀለ የሚል ዜና መስማት የሚያስደነግጥና በመጀመሪያዉ ዜና ላይ ቀዝቃዛ ዉኃ የቸለሰ ልብ ሰባሪ ዜና ነዉ። ደግነቱ ሁሉም ነገር ለበጎ ነዉ። የሞላ አስገዶም መክዳት ተራ ዜና ነዉ ማለቴ አይደለም። ግን ሞላ አስገዶምና የወያኔ መረጃ ድርጅት በትብብር ሠራነዉ ያሉት አዲስ ድራማ ተዉኔቱ ሳይጻፍ አየር በአየር የተከወነ ምናቡ ያልተባ ድራማ በመሆኑ ድራማዉ ከያኒዉን ሳይሆን የኢትዮጵያን ህዝብና ለአንድነቱና ለነጻነቱ የሚታገሉ ልጆቹን በከፍተኛ ደረጃ የጠቀመ መሆኑን ማሳዉቁ አስፈላጊ ይመስለኛል።

ደምህት በዚህ የወያኔ ድራማ ዉስጥ በእሳት ተፈትኖ ወርቅነቱን አረጋግጧል። ሞላ አስገዶም የደምህትን ሠራዊት ለወያኔ አስረከብኩ ብሎ በተናገረ ማግስት የደምህት መሪዎች የሰጡት አርቆ አስተዋይነት የታየበት አመራርና ያሳዩት ቆራጥነት የፖለቲካ ድርጅቶቻችን የደረሱበትን የዕድገት ደረጃ በግልጽ አሳይቷል። ደምህት እራሱም እንደ አንድ የትግል ድርጅት የተደቀነበትን አደጋና ፈተና በጣጥሶ በመዉጣት በትናንሾችና በደካሞች ሴራ በፍጹም የማይናጋ ጠንካራ ድርጅት መሆኑን በተግባር አሳይቷል። የዛሬዉ ደምህት ዉስጡን ከአድርባዮች ያፀዳ ሁለትና ሦስት እርምጃዎች ወደፊት የተራመደ ጠንካራ ድርጅት ነዉ። እርግጠኛ ነኝ ይህ የደምህት መሪዎች ያሳዩት አስተዋይነት፤ ጽናትና ቆራጥነት እኔ የምፈልገዉ ነገር ካልሆነ ድርጅቱን በአፍጢሙ እደፋዋለሁ ብለዉ ለሚያስቡ ዕብሪተኛ መሪዎች ጥሩ ትምህርት ነዉ። ሌላዉ የሞላ አስገዶም ክህደት በግልጽ ያሳየን ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ፖለቲካ መድረክ የሀዝብ መብትና ነጻነት ይከበር በሚሉ የነጻነት ሀይሎችና ህዝብን ረግጠን እንገዛለን በሚሉ ፀረ ህዘብ ሀይሎች ለሁለት መከፈሉን ነዉ። ወደድንም ጣላን ካሁን በኋላ ያለን አማራጭ ሁለት ብቻ ነዉ፤ ወይ ወያኔ ሆኖ ከህዝብ ጋራ መዋጋት ወይም ከህዘብ ጋር ሆኖ ወያኔንና ስርዐቱን መዋጋት። ሞላ አስገዶም ጎራዉን ለይቷል፤ እኛም ጎራችንን እንለይ። መኃል ቆሞ መመልከት አብቅቷል።

ጠላቴን አግዝፌ መመልከት አልወድም፤ ትንሽ ነዉ ብዬም ጠላቴን በፍጹም አልንቅም። በቅርቡ የወያኔ የመረጃና ደህንነት መ/ቤትና ሞላ አስገዶም ከአንድ አመት በላይ አብረን ሠራን ያሉትን የጀማሪዎች ስራ ስምለከት ግን ወያኔ/ህወሃት “የምትሰሩትን ብቻ ሳይሆን የምታስቡትን ጭምር የሚያይ አይን አለኝ” እያለ የኢትዮጵያን ህዝብ ከማስፈራራት ዉጭ የረቀቀ የመረጃ ስራ መስራት ቀርቶ አረፍተነገሮችን አገጣጥሞ ለጆሮ የሚጥም ንግግር ማድረግ የሚችል አዋቂ የሌለበት የባዶዎች ድርጅት መሆኑን ነዉ የተረዳሁት። ሞላ አስገዶምም በወዶገባነት ሄዶ የተቀላቀለዉ ይህንኑ አዋቂ የሌለበትን እሱን የመሰለ ድርጅት ነዉ። ይህንን ደግሞ እስከዛሬ በሰጣቸዉ ቃለመጠይቆች በግልጽ አይተናል። ህወሃት/ወያኔን እስከዛሬ በሥልጣን ላይ ያቆዩት ሁለት ነገሮች ቢኖሩ አንዱ ጠመንጃ ሁለተኛዉ የኛ የነጻነት ኃይሎች መበታተን ብቻ ነዉ።

ነገ የምንፈልጋት ኢትዮጵያ እንደ መኪና ተገጣጥማ አትጠብቀንም – የዛሬዉ ጥረታችንና ድካማችን ዉጤት ናት። ኢትዮጵያና ህዝቧ ከወያኔ ሲፀዱ የሚነፍሰዉ የነጻነት አየር ሁላችንንም ቢያስደስትም ደስታዉ የሚገለጸዉ በግለሰብ ደረጃ ነዉ። ዛሬ ከጠላት ጋር ተፋልመን የተቀማነዉን ነፃነት ማስመለስና እንደገና እንዳንቀማ ነቅቶ መጠበቅ ግን የሁላችንም የጋራ ሀላፊነት ነዉ። እንግዲህ ወገን ወገባችንን ጠበቅ የምናደርግበት ግዜ አሁን ነዉና ሁላችንም በየተሰለፍንበት መስክ እንበርታ። ጠላታችን ጠንካራ መስሎ የሚታየዉና ያለ የሌለ ጡንቻዉን የሚያሳርፍብን የማይቀረዉን ድል ማሽተት ስንጀምር ነዉ። የድል መአዛችንን የምናሸትበት ግዜ ደግሞ ሩቅ እንዳይመስለን ነገና ከነገ ወዲያ ነዉ። ከወላዋይና እዚህም እዚያም እየዘለለ ከሚያዘናጋን አጉል ጓደኛ አንዱኑ የለየለት ጠላት ይሻላልና የሞላ አስገዶም ክህደት ትግላችንን ሊያጠራዉና መንገዳችንንም ሊያሳጥረዉ ይገባል እንጂ በፍጹም ግራ ሊያጋባን አይገባም። አይዞን. . .  ሞኝ ከዘመዱ ከሚያገኝዉ ጥቅም አዋቂ ከጠላቱ የሚያገኘዉ ጥቅም ይበልጣልና ጠላቶቻችን የፈጠሩልንን አጋጣሚዎች ሁሉ በሚገባ እንጠቀምባቸዉ እንጂ ለጠላት አንመቻች። ጠላታችን እየተሳሳተልን ነዉ፤ ጠላት ሲሳሳት ማቋረጥ ነዉር ነዉ። ቸር ይግጠመን!!!

Friday, September 18, 2015

The sun is shining over Ethiopia

 

by Yilma Bekele
Ethiopia has been in darkness. We had light before most but that is history. We can recite our ancient history; write beautiful poetry extolling our virtues and fill a library with our traditional lore unfortunately it is not something we can take to the bank. It is not all lost. Ethiopia and her wellness has been woven into our soul. Thus today where ever we go we survive and thrive. Don’t take the fact you walk with your head high for granted my friend, that pride in you is cultivated and nurtured.
The Ottoman Turks, the Egyptians, the British, the French, the Italians have all tried to force their ways on us. It just did not work. Outsiders have learnt their lesson and have stopped trying force to make us serve their interest. It is the homegrown variety that has become a challenge. It could be a (seyawkush yinkush ሲያውቁሽ ይንቁሽ) situation where naturally one disarms in the presence of family and friends. Sooner or later one member goes rogue. It never fails. Throughout our history we have encountered such situations where kings, warlords or madmen have fought for power and glory. TPLF is our child gone rogue.
TPLF is the worst internal enemy faced by our county. There isn’t any aspect of our culture and history they have not tried to contaminate with negativity and hate. For over thirty years they have systematically worked on destroying the unity and strength that has taken hundreds of years to build. It is due to the solid foundation that our dear country has been built on that they are unable to even cause a little crack let alone a fissure. We are grateful to all those that sacrificed and painstakingly built this formidable home we call Ethiopia.
The current struggle being waged by TPLF on one side and Democratic forces on the other is about the kind of Ethiopia we want to build on the foundations already laid by our ancestors. Instead of building on that and adding value we have been busy subtracting, dividing and undermining our precious asset.
On this side we have the current Ethiopian government led by Tigrai Peoples Liberation Front (TPLF) that has been in power for the last twenty two years uninterrupted. The TPLF Party with its clueless and unwritten guiding dogma it calls ‘Revolutionary Democracy is based on the following principles:
• The Ethiopian people are not ready for Democracy.
• The vanguard TPLF will oversee the development of Democracy.
Despite what the regime and its international supporters claim this arrangement has not worked well for the average Ethiopian. There is no need to try to convince an Ethiopian how bad the Tigrai People’s party has been to our country. All one has to do is look around one’s own family and ask ‘how are you doing?’ If you do not know of a family member in distress you my friend is an exceptional Ethiopian. We all salute you but that unfortunately is not the norm.
That is why there are many that have decided to sacrifice life and family and stood against the tyranny of the Tigrai Peoples Liberation Front. We Ethiopians are such a lucky people to have been able to produce such dynamic and selfless leaders that would rather suffer than accept injustice.
Kinijit is the grandfather of all independent movements in Woyane era politics. Kinijit beyond a shadow of doubt showed how hollow and wild Woyane’s are. Before Kinijit we used to view Woyane as being benign with no harmful effect. Thanks to Kinijit Woyane was forced to show what a malignant tumor it is.
Ever since then many have tried to work within the system Woyane created. We are finding out even that is not possible. The brave leaders and members of Semayawi Party are a living testimonial that conversation with Woyane is not possible.
That in a nutshell is Ethiopian history the last twenty two years. We produce selfless individuals that have entered the fray knowing full well what savage Woyanes are capable of. Common sense shows that carrot (staying quiet) alone has not worked in Ethiopia. A stick is an absolute requirement to balance the equation. Do you follow me? After twenty three years of abuse we Ethiopians should be the last to be bewildered by this situation.
Patriotic Ginbot7 is our stick. There have been others, what makes this one any different is a good question. That is the reason I raised our recent history earlier. Woyane has held five or more election the last twenty two years, which one is memorable? May 2005 is when we divorced Woyane. The 2005 was led by Kinijit with Berhanu Nega as a central figure. Dr. Berhanu and friends whipped Woyane. Dr. Berhanu is the first popularly elected leader to a high office in our entire history. His election to be Lord Mayor of Addis Abeba was a landslide. The people of Addis Abeba loved him. No need to say more.
The formation of Ginbot7 Movement for Unity and Democracy was the result of lessons learnt from the 2005 attempt to seize power through peaceful and legal means. By all scale of measurement G7 has exceeded all expectations. It has shown what it means to be an organization focused on one thing and one thing alone. To leave no stone unturned to find a way to grow Freedom and Democracy in Ethiopia.
To this end the last five years the Organization has painstakingly built the network necessary to do the work. What is there not to admire more than the fact despite the mighty power of a Nation State’s attempt to kill, undermine, destroy, wreck from inside, jail exile so many times in the name of fighting terrorism but to protect single ethnic rule, G7 has managed to blossom to an organization that in the eyes of many Ethiopians managed to bring that old feeling of pride that has quietly been sitting inside all of us. Elel Belu!
How do you fight one of your own has been our dilemma. Believe me if Woyane was an outsider no matter what; we all would fight back and there would not be discussion like what we are having now. Unfortunately it is not so. At the moment Patriotic G7 is in the forefront of the struggle to get rid of this disease that is infecting our homeland.
It is said ‘leadership is the capacity to translate vision into reality’ that is what we have in Dr. Berhanu Nega. In every turn of our movement he has been there crafting winning strategy to get us closer to our goal of building a better Ethiopia where her children invest time and energy in making it a place we are proud to call home. His simple manners, generous smile and focus His style has been pay any price, walk the extra mile so we Ethiopians can drink from the fountain of freedom.
The TPLF regime has done all it could to discourage our leader. A mere mortal would have thrown his hands in the air and walked away. Dr. Berhanu stayed the course and showed little Woyane there are some Ethiopians that are determined and resolute. Such character is not a trait Woyane understands.
In Arbegnoch G7 we Ethiopians at last have achieved a winning formula to bring national salvation to our homeland. In Berhanu Nega and his team we have found leaders with a record and a winning formula. Kinijit paved the way and Arbegnoch G7 is poised to finish the job. We say it with confidence because the experience the last ten years have shown us that an organization built on democratic principles, staffed by able leaders and carrying the torch of freedom and equality cannot fail. Especially when the enemy is a group led by gangsters and shameless characters that have not achieved much in life using legal and transparent means it does not need much for the house of cards they built to come crashing down.
All patriotic Ethiopians are fighters in this war of salvation. The question we should ask ourselves is what can I contribute to hasten the day of freedom. Today this joke of I am not into politics, I am neutral has no place. It is like standing back and watching while your house is on fire. Ethiopia is burning and her children are dying in droves. This is not the time to be a spectator or a shameless supporter of the ethnic regime. It is past time for verbal condenations. We have done that, we have been there.
The current activity to support and celebrate our Freedom fighters is a breath of fresh air. It is nice to stand up rather than always be a victim. We used to cry for Ethiopia. Today we cry for Woyane that is already feeling the wrath of the people. All over the world Ethiopians are giving what they could without being compelled. Five dollars or a thousand, five minutes or a lifetime, whatever is offered, it is sure to bring satisfaction to the heart, pride to the family and debt paid top our mother. Here in Oakland, California we are preparing to give the mother of all fundraising events since Kinijit. The enthusiasm of the members, the reception of our people and the smile painted on our face is an indication the sun is shining on our motherland. Find out where Arbegnoch G7 activity is held in a location near you and be part of this tsunami of support for our liberators. Tell everybody that the Sun is shining brighter than ever over Ethiopia.
 

Wednesday, September 16, 2015

Tigray Peoples Democratic Movement (TPDM) press release regarding Mola Asgedom’s defection.



ከትህዴን የወጣ አስቸኳይ መግለጫ።
Sept 14, 2015
ድርጅታችን ትህዴን በየካቲት 1993 ዓ/ም ብረት አንስቶ ትግል ሲጀምር አላማው ግልፅና የማያሻማ ነበር።
እሱም በሃገራችን የገነነው አፋኝ ስርዓት ህዝባችንን ከፋፍሎ ሰብኣዊ መብቱን ረግጦ ለመግዛት በሚያመቸው መንገድ ይጓዝ ስለነበር ድርጅታችን ትህዴን ችግሩን ለመፍታት ኩሁሉም በኢትዮጵያ አንድነት ከሚያምኑ ድርጅቶች በመተባበር ህዝባዊ ስርአት ለመትከልና አንድነቷ የተጠበቀ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ መገንባት የሚል አላማ አንግቦ የህወሓት-ኢህ አዴግ ስርዓትን በመቃወም ነፍጥ አንስቶ በትጥቅ ትግል መፋለም ከጀመረ 14 ዓመታት ሆኖታል።
በነዚህ 14 ዓምታት የትግል ጉዞ ድርጅታችን ትህዴን በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ወታደራዊ መስክ ከፍተኛ ድሎችን እያስመዝገበ መጥቷል። ትግል ሲባል ቀላል እንዳልሆነ ካሳለፍነው የትግል ታሪክ እየተማርን መጥተናል። ድርጅታችን ትህዴንም በዚህ አጭር እድሜው ክፍተኛ ድሎችን ሲጎናጸፍ የተለያዩ መስናክሎችን በመሻገር ነው።
በቅርብ ጊዜ የተወሰኑ በትግሉ የቆዩና ግላዊ ጥቅማቸው የተነካባቸው ግለስቦች ትግሉን ባሻቸው መንገድ ሊጠመዝዙት ስላልቻሉና በአብዛኛው ታጋይ በመድረክ ተይዘው መፈናፈኛ ስላጡ ተስፋ ቆርጠው ከትግሉ ጎራ ሸሽተዋል።
የተከበርከው ሰፊው ህዝባችን እነዚህ ጥቂት ግለሰቦች ለግል ጥቅማቸው ያደሩ እንጂ ትህዴንን የሚወክሉ አይደሉም። የእነዚህ ስዎች ከትግሉ መክዳት ደግሞ ድርጅታችን ትህዴን የቆሸሸውን በመጥረግ ጥንካሬውን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያጎለብተዋል እንጂ ትግሉን ለሰክንድም ቢሆን አያደናቅፈውም።
ትህዴን ይዞት የተነሳ ዓላማ የመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት ስለሆነ ሊቅበለውም ውይም ላይቅበለውም የሚችለው ህዝብ እንጂ ግለሰቦች አይደሉም። ትግላችን ደግሞ በሃገራችን ያለውን ፀረህዝብ ስርዓት ከስልጣኑ ተወግዶ ህዝባችን የጀመረውን የትጥቅ ትግል ግቡን ሳይመታ ለአፍታም ቢሆን አይቆምም።
ስለሆነም መላው የኢትዮጵያ ስፊ ህዝብ ይህንን ተረድተህ እንደበፊቱ ሁሉ በልጆችህ እይተካሄደ ባለው ህዝባዊ ትግል ጎን እንድትሰለፍ መላው የትህዴን ታጋይ ጥሪውን ያቀርባል።


Monday, September 14, 2015

የዴሚት ሊቀመንበር ከኤርትራ ወጥተው ለወያኔ እጃቸውን ሰጡ።

 

mola-asgedom
የኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቪዝን(ኢሳት) ዛሬ እንደዘገበው የዴሚት ሊቀመንበር ከኤርትራ ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ተከትሎ የተለያዩ ኣስተያየቶች በህዝቡ ዘንድ እየቀረበ ነው።
ከየድርጅቶች ኣመራርን ለማግኘት ሞክረን ባይሳካልንም የውስጥ ምንጮች እንደገለጹልን የዴሚት ሊቀመንበር ታጋይ ሞላ ኣስግዶም ለ፩፬ ኣመታት በበረሃ በነበረበት ሰኣት ምንም ኣይነት ይሄ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ኣለማድረጉ በኣመራሩ ውስጥ ቅሬታ ሳይኖር እንዳልቀረ ይገመታል። ኣሁን የተጀመረው ትግል በፍጥነት መሄድ ኣለበት፤ ኣንድ ላይ ሁናችሁ ስሩ የሚል ከኤርትራ ባለስልጣናት በኩል በተደጋጋሚ ይጠየቅ እንደነበር ነው። ይህም የዶር ብርሃኑን መግባት ጨምሮ ኣሁን ለተደረሰበት ውሳኔ በጋራ መስራት ኣስተዋጻኦ እንዳደረገ ነገር ግን ኣቶ ሞላ ኣስግዶም ይህን  መቀላቀል መቃዎማቸውን ብሎም  የራሳቸው የደሚት ስራ ኣስፈጻሚ ኣመራር ሁሉም በጋራ ለመወሃድ ኣብሮ ለመስራት ያሳዩት ትብብር ና ፍላጎት መሪውን እንዳላስደሰታቸው ይገመታል። ከደምሂትም ከጥምረቱም በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ እየተጠበቀ ነው።
ላአገር እና ለዓላማ ታማኝነትን የማንም ግለሰብ እርምጃ አያሳንሰውም።ከተነሳበት ዓላማ ርቆ የሄደ ሰው ድርጊት ዓላማውን የተሳሳተ አያደርገውም።ዛሬ የትግሉ መስመር መጥራቱ ጥምረቱ የጠና መሰረት ላይ እንዲቆም ከወዲሁ ያረጋግጣል።የተያዘው አገር አድን ትግል ከግለሰቦችና ቡድፋዊነት እጅግ የገዘፈ ነው።በጠላት ወረራ ኢትዮጵያ ስትያዝ “አንድ ሳር ቢመዘዝ ያፈሳል ወይ ቤት ?” ተብሎ ነበር ወደ ጠላት የወገኑትን ተግባር ለመግለጥ።ወያኔ ወታደራዊ መረጃ አገኘሁ ማለቱና፤ለአንድ ሰሞን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚሆን የወሬ ስንቅ አገኘሁ ማለቱ የማይቀር ነው።ይህ ደግሞ የተፋፋመውን ትግል በምንም አይነት አይጎዳውም።የጠራ መስመር፤የበረታ አመራር የሚወጣው እንዲህ ያለው ክስተት ሁሉ ታልፎ ነው።እንዲህ ያሉ ሁኔታዎች የትግሉን መምረር አመላካቾች ናቸው። በተግባ ለተግባር መነሳሳት ሳይኖር ይህ ሁኔታ አይከሰትም ነበር።የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ጽናት፤ብርታታቸው የሚታይባቸው እድሎች ከፊታቸው ናቸው።የሞላ አስገዶም መሄድ የወያኔን ባህሪ አይለውጥም፤ለወያኔ የሚያክለው ብርታት የለም።ከጥምረቱ የሚወጣውን መግለጫ መጠበቁ ይመረጣል ከዚህ ሌላ ከመናገር።

Sunday, September 13, 2015

የነ ኤፍሬም ማዴቦ ትንቢት ስለ ሞላ አስገዶም ከዳተኝነት – አብርሃም ታየኝ

 

  • 864
     
    Share
Birhanu2qከአንድ ወር በፊት የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር አባል ኤፍሬም ማዴቦ ኤርትራ ሂዶ ከዊሃ እስከ ኦምሃጅር ከአርበኞች ጋር በሚል ርዕስ የጻፈውና በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የናኘው መልዕክት ትዝ ያለኝ የትህዴን   ሊቀመንበር የነበረው ታጋይ ሞላ አስገዶም ድርጅቱን ከድቶ ወደ ወያኔ ህወሃት ተመለሰ እንደተባለ ነው።
በተለያዩ የኤርትራ በረሃዎች ጫካዎች የመሸጉትን አርበኞች በጽሁፉ እያስቃኘን የትህዴን ካምፕ ደርሰው በነዓምን ዘለቀ ዲጄነት የተከፈተው የጥላሁን ገሰሰ ሙዚቃ ሲያዳምጡ በነበረበት ቅጽበት እንዲህ ሲል ሳያውቍም ይሁን አውቆት ተንብዮታል።
“አልማዝን አይቼ እልማዝን ሳያት”፤ “እንጉዳዬ ነሺ” “አመልካች ጣት” “መሳቁን ያስቃል” . . . ብቻ ምን አለፋችሁ የጥላሁን ሙዚቃ ተዥጎደጎደ። ጥላሁን ገሠሠ አስመራ ላይ የሚጠብቀንን ቀጠሮ ብቻ ሳይሆን ጭራሽ እኛነታችንን አስረሳን። ቢበዛ አንድ ሰዐት ብለን የመጣን ሰዎች ከሦስት ሰዐት በላይ ከደምህት ጓዶቻችን ጋር ቆየን። በመጨረሻ የጉዟችን መሪ “አንድ ለመንገድ” ብሎ ከተቀመጠበት ተነሳ። እሱ ሲነሳ “እንክርዳድ እንክርዳድ የተንከረደደ፤ ስንዴ መስሎ ገብቶ ስንቱን አሳበደ” የሚለዉ ዘፈን እያለቀ ነበር። ነአምን. . . ነአምን ብዬ ስጣራ . . . “One for the road” ይቀረናልኮ አለ ነአምን . . . እንሂድ የምለዉ መስሎት። ይህንን ሙዚቃ እንደ እንክርዳድ ተቀላቅሎን ለሚያሳብደን የዳያስፖራ ቱልቱላ መርጫለሁ አልኩት። ሳቅ አለና ከቴፑ ጋር መጫወቱን ቀጠለ። እርግጠኛ ነኝ ተቦርነ በየነ ወይም መሳይ መኮንን አንድ ቀን “እንክርዳድ እንክርዳድን” በኢሳት ያሰሙናል። አይደል ተቦርነ?
በመጨረሻ የኛም መሄጃ የሙዚቃዉም መገባደጃ ደረሰ። “One for the road” የተባለለት ሙዚቃ (ዘፈን) ገና ሲጀምር ሰማሁና ኢችንማ አምላክ ነዉ የመረጠልን አልኩ በልቤ። ያ በቁሙ “አጥንቴም ይከስከስ” ብሎ ያስተባበረን ጥላሁን ገሠሠ አሁንም ከላይ ከሰማይ ቤት “ቃልሽ አይለወጥ እባክሺ….ን” እያለ ቃል እንድንገባባ አደረገን። ተራ በተራ ከአርበኛ ሞላ አስገዶም ጋር እየተቃቀፍን “ቃልሽ- አይለወጥ- አባክሽን” ብለን ተለያየን። ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ ብዬ ነበር የጀመርኳችሁ፤ አሁንም ቃሌ ይሄዉ ነዉ። ቃላችን አይለወጥ! ቸር ይግጠመን።
ኤፍሬም ነኝ ከአርበኞች መንደር
 
አይ ሙዚቃ አመራረጥ ለነዓምን፤ አይ አጻጻፍ ለኤፍሬም !!! ቃልሽ አይለወጥ በሚለው የጥላሁን ገሰሰ ዘፈን ከዛሬው ከዳተኛ ከሞላ አስገዶም ጋር የተሰነባበታችሁት ቃሉን እንደሚያጥፍ ታይቷችሁ ነው ብዬ የነብይነት ማዕረግ ልሰጣችሁ ወደድኩ። “One for the road” የተባለለት ሙዚቃ ለሞላ አስገዶም መሸኛ  ይመስላል። እንክርዳዱ ማን እንደሆነ በውስጠ ወይራ አጻጻፉ ገባን።
የአፋር ሕዝብ ንቅናቄ፣ ትህዴን፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄና አርበኞች ግንቦት 7 የጋራ  አገር አድን ንቅናቄ መመስረታቸውን በተመለከተ  ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋም በኢሳት ራዲዮ  ተጠይቀው  በድርጅቶቹ አባላት መሃል ማፈግፈግ ቢከሰት እንኳ አገር አድን ሰራዊቱ እንደሚታደገው አብራርተዋል። ይቺንም ትንቢት ብያታለው። ለዚህም ካስረኛው የቃለመጠይቁ ደቂቃ በኋላ  እንደተረዳነው ከሁሉም ድርጅቶች ተውጣጥቶ ከተቋቋመው አገር አድን ሰራዊት ተመልሶ ወደ እናት ድርጅቱ ልመለስ ማለት አይቻልም። አራቱ ድርጅቶች  በጋራ ንቅናቄው ሰራዊት ይዋጣሉ እንጂ ለምሳሌ  ትህዴን  ብዙ ሰራዊት ያለኝ እኔ ነኝ እና በኔ ስም ተጠሩ ቢል የሚሰማው የለም።ሞላ አስገዶም ትግሉን የከዳውም ትህዴንን እንደንብረቱ ቆጥሮ  መሪ ካላደረጋችሁኝ ብሎ ከሌሎች ጋር ተጣልቶ ከሆነም ወደፊት የምናየው ነው።
ለማንኛውም የነፕሮፌሰር ብርሃኑ ምሁራዊ አካሄድ የህወሃትን ካባ ለብሰው ኤርትራ ለመሸጉት ቅጥረኞች አልተመቻቸውም። የተደላደለ የ አሜሪካ ኑሯቸውን ትተው እነ ኤፍሬም በረሃ ይወርዳሉ ብለው እነ ወዲ አስገዶም አልጠበቁትም። ህዝቡ ለውጥ እንደሚፈልግ ተረዱት።ነገም ዛሬም የሚወተውቱት ስለ እውነተኛ ዲሞክራሲ ነውና ሆዳሞች ጨነቃቸው።ስለዚህ ሳይነቃባቸው ፈረጠጡ።
በመጨረሻም የ አርበኖች ግንቦት ሰባት አመራሮች ኤርትራ ከገቡ የተሰበሩ ሁለቱን የህወሃት ሴራዎች እንይና  ለዛሬ ይብቃን።ዙሩ ከሯል።   ሃምሌ 10 እነ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ  ኤርትራ  ገብተው ሃምሌ 20 የኤርትሪያውንን መረጃ ሙሉ በሙሉ ለኢትዮጵያ ሲያቀብል ለበርካታ ዓመታት  የኖረ እና በኤርትሪያ የወያኔ ተቃዋሚ የነበሩ ሰዎችን  እያደነ ሲገድልና ሲያስር የነበረ የመላዋ ኤርትሪያ የፀጥታ ኃላፊ በቁጥጥር ስራ ውሏል።  ያኔ  ከአሜሪካ የሄዱት አመራሮች ያለደህንነት ስጋት እንዲንቀሳቀሱ የወያኔ ቀኝ እጅ የነበረው የጸጥታ ሃላፊ መያዝ ፍንጭ ሰጥቶ ነበረ። አሁን ደሞ  የተቃዋሚ ጦር ሰራዊት የት ህ ዴን መሪ በመሆን ለህወሃት ሲሰራ የነበረው ሞላ አስገዶም ተጋልጧል።ይህ እንግዲህ ብስሉ ከጥሬው ገና ከጅምሩ የተለየበት፤ ምርቱ ከ እንክርዳዱ በመጀመሪያው የውህደት ወንፊት የተጣራበት ወቅት ነው። በነዓምን የተጋበዝነውን ቃልሽ አይለወጥ እባክሽን የሚለውን የ ጥላሁን ገሰሰን ዘፈን ለሌሎቻችን እየጋበዝኩ ቃል የዕምነት ዕዳ ስለሆነ እንዳናጎድለው አሳስባለው።ቃል ብናጥፍ ግን የሚጎልብን ራሳችን ላይ መሆኑን ግልጽ ነው። ታጋይ እንጂ ትግል አይሞትም
 
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46640#sthash.35pPnGlh.dpuf

Tuesday, September 8, 2015

የአፋር ሕዝብ ንቅናቄ፣ ትህዴን፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄና አርበኞች ግንቦት 7 የጋራ ንቅናቄ መሰረቱ

 

(photo File)
 ከአርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ እንዳገኘችው መረጃ ከሆነ ብረት አንስተው በበረሃ የመሸጉ አራት ታላላቅ የነፃነት ድርጅቶች አምባገነኑን የህወሓት አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ደምስሰው ግብአተ መሬቱን ለመፈፀም ተጣምረው “የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ” የሚል አዲስ ድርጅት መሰረቱ፡፡

ተጣምረው የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄን የመሰረቱት አራቱ ታላላቅ የነፃነት ድርጅቶች የአፋር ድርጅቶች የጋራ ንቅናቄ፣ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ እና አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ናቸው፡፡
Arbegoch Ginbot 7
የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ /በአጭሩ የአገር አድን ንቅናቄ/ የተቋቋመው ጳጉሜ 3 ቀን 2007 ዓ.ም ሲሆን የንቅናቄው ምክር ቤት፣ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና የተለያዩ መምሪያዎች ተቋቁመው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበር እና ታጋይ ሞላ አስገዶም ም/ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡
የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ ከአራቱ አባል ድርጅቶች የተውጣጣ እጅግ በጣም ግዙፍ አገር አድን ሰራዊት አቋቁሟል፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46520#sthash.lrUziVSj.dpuf

የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄን ምሥረታ በማስመልከት የወጣ ድርጅታዊ መግለጫ


http://ethsat.com/video/2015/09/07/esat-breaking-news-four-ethiopian-forces-formed-a-united-front-sep-07-2015/
September 8, 2015
…በጋራ አብሮ በመታገል የሚገኘው ዘርፈ ብዙ ጥቅም የገባቸውና ካለፈው ተደጋጋሚ የታሪክ ስህተት የተማሩ፣ በአገራችን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲመሰረት በምድር ላይ በመንቀሳቀስ ላይ ያሉ አራት ድርጅቶች በጥምረት ተባብረው በጋራ ለመታገል ወስነዋል። እነዚህ አራት ድርጅቶች ለብዙ ዓመታት የአብሮ መታገል ፍላጎት እንቅፋት የሆነውን የገዢ መደቦች የከፋፍለህ ግዛው ሴራ በጣጥሰዋል። ይህ ዛሬ በጥምረት የተጀመረው ትብብር እያደገ ሄዶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ውህደት እንዲያድግ ይደረጋል። ከዚህም በተጨማሪ ንቅናቄው ከሌሎች ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት መመስረት ከሚታገሉ ኢትዮጵያውያን ድርጅቶች ጋር ተጣምሮ ለመስራት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ አጠናክሮ ይገፋበታል።
በዚህም መሠረት፣
1ኛ) የአፋር ድርጅቶች የጋራ ንቅናቄ
2ኛ) የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ
3ኛ) የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ፣ እና
4ኛ) የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ
የኢትዮጵያ አገር አድን በዲሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ (በአጭሩ “የአገር አድን ንቅናቄ”) የሚባል ድርጅት ዛሬ በአዲስ ዓመት መባቻ ጳጉሜ 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ፈጥረዋል። የንቅናቄውን ምክርቤት፣ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴና የተለያዩ መምሪያዎችን ከማቋቋሙም በላይ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ሊ/መንበር፣ አቶ ሞላ አስግዶምን ም/ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል። [ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
United Movement for the Salvation of Ethiopia through Democracy