Monday, September 14, 2015

የዴሚት ሊቀመንበር ከኤርትራ ወጥተው ለወያኔ እጃቸውን ሰጡ።

 

mola-asgedom
የኢትዮጵያ ሳቴላይት ቴሌቪዝን(ኢሳት) ዛሬ እንደዘገበው የዴሚት ሊቀመንበር ከኤርትራ ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ተከትሎ የተለያዩ ኣስተያየቶች በህዝቡ ዘንድ እየቀረበ ነው።
ከየድርጅቶች ኣመራርን ለማግኘት ሞክረን ባይሳካልንም የውስጥ ምንጮች እንደገለጹልን የዴሚት ሊቀመንበር ታጋይ ሞላ ኣስግዶም ለ፩፬ ኣመታት በበረሃ በነበረበት ሰኣት ምንም ኣይነት ይሄ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ኣለማድረጉ በኣመራሩ ውስጥ ቅሬታ ሳይኖር እንዳልቀረ ይገመታል። ኣሁን የተጀመረው ትግል በፍጥነት መሄድ ኣለበት፤ ኣንድ ላይ ሁናችሁ ስሩ የሚል ከኤርትራ ባለስልጣናት በኩል በተደጋጋሚ ይጠየቅ እንደነበር ነው። ይህም የዶር ብርሃኑን መግባት ጨምሮ ኣሁን ለተደረሰበት ውሳኔ በጋራ መስራት ኣስተዋጻኦ እንዳደረገ ነገር ግን ኣቶ ሞላ ኣስግዶም ይህን  መቀላቀል መቃዎማቸውን ብሎም  የራሳቸው የደሚት ስራ ኣስፈጻሚ ኣመራር ሁሉም በጋራ ለመወሃድ ኣብሮ ለመስራት ያሳዩት ትብብር ና ፍላጎት መሪውን እንዳላስደሰታቸው ይገመታል። ከደምሂትም ከጥምረቱም በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ እየተጠበቀ ነው።
ላአገር እና ለዓላማ ታማኝነትን የማንም ግለሰብ እርምጃ አያሳንሰውም።ከተነሳበት ዓላማ ርቆ የሄደ ሰው ድርጊት ዓላማውን የተሳሳተ አያደርገውም።ዛሬ የትግሉ መስመር መጥራቱ ጥምረቱ የጠና መሰረት ላይ እንዲቆም ከወዲሁ ያረጋግጣል።የተያዘው አገር አድን ትግል ከግለሰቦችና ቡድፋዊነት እጅግ የገዘፈ ነው።በጠላት ወረራ ኢትዮጵያ ስትያዝ “አንድ ሳር ቢመዘዝ ያፈሳል ወይ ቤት ?” ተብሎ ነበር ወደ ጠላት የወገኑትን ተግባር ለመግለጥ።ወያኔ ወታደራዊ መረጃ አገኘሁ ማለቱና፤ለአንድ ሰሞን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚሆን የወሬ ስንቅ አገኘሁ ማለቱ የማይቀር ነው።ይህ ደግሞ የተፋፋመውን ትግል በምንም አይነት አይጎዳውም።የጠራ መስመር፤የበረታ አመራር የሚወጣው እንዲህ ያለው ክስተት ሁሉ ታልፎ ነው።እንዲህ ያሉ ሁኔታዎች የትግሉን መምረር አመላካቾች ናቸው። በተግባ ለተግባር መነሳሳት ሳይኖር ይህ ሁኔታ አይከሰትም ነበር።የህዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሀይሎች ጽናት፤ብርታታቸው የሚታይባቸው እድሎች ከፊታቸው ናቸው።የሞላ አስገዶም መሄድ የወያኔን ባህሪ አይለውጥም፤ለወያኔ የሚያክለው ብርታት የለም።ከጥምረቱ የሚወጣውን መግለጫ መጠበቁ ይመረጣል ከዚህ ሌላ ከመናገር።

1 comment:

  1. Mari Padilha Graças Amarração forte:
    Escreva na sola do pé esquerdo o nome da pessoa amada. Aperte o pé no chão forte dizendo 3x: “Debaixo do meu pé esquerdo te prendo (A S), te amarro (A S) e te mantenho (A S) pelo poder das 13 Almas Benditas. Que assim seja. Que você venha me procurar em 24 horas dizendo que me ama e quer ficar comigo pra sempre.
    Enquanto você não vier, não irá comer, não irá dormir, e nem irá ter vontade de outra mulher a não ser eu. Assim seja, é e será (Publicar 4x e não contar o sonho a ninguém)[

    ReplyDelete