Sunday, December 16, 2018

ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት እና የሠራተኛው መደብ አምባገነንነት ፅንስና በኢትዮጵያ ውስጥ ያስከተለው ሰቆቃ በነገሰ ጉተማ




                                                                                     መግቢያ
The TPLF.ይህ ፅሁፍ  ስለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት ምንነትና  አመጣጥ እንዲሁም  ባለፉት 40 ዓመታት በኢትዮጵያ ሕልውናና እድገት ላይ ያሳደረውን  የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የባህላዊ  ተጽእኖ  ይዳስሳል።  በማጠቃለያውም ተቃዋሚ  ፓርቲዎችና ዴሞክራሲያዊ  ድርጅቶች  ያለባቸውን  ታሪካዊ  ኃላፊነት በአንድነት እንዲወጡ ይጠይቃል። ጠለቅ ያለ ምርመራ ማድረግ ለሚፈልጉ በማጣቀሻዎች ሥር ያሰፈርኳቸውን  መፃሕፍትና ድረገጾች መመርመር ጠቃሚ ነው።
ካርል ማርክስ፣ ቭላድሚር ሌኒን እና የ”ሠራተኛው መደብ (ፕሮሌታሪያት)” አምባገነናዊ መንግሥት   አመሠራረት
በ1917 ዓ. ም.  እ.አ.አ. በቭላድሚር ሌኒን የሚመራው የሩሲያ ኮሚኒስት ፓርቲ (ቦልሼቪኮች) በጥቅምቱ አብዮት (ኦክቶበር ሬቮሉሽን) የሩሲያውን ዳግማዊ ኒኮላስን መንግሥት ከሥልጣን በማውረድ “የሠራተኛውን (ፕሮሌታርያት) መንግሥት” መሠረተ። ሶቪየት ሕብረትም ተፈጠረች። በጊዘው በቦልሼቪኮች የተመራው አብዮት“ሠራተኛውን መደብ ወይም ፕሮሌታሪያቱን” ሥልጣን ላይ ቢያመጣም የሩስያው ሠራተኛ (ፕሮሌታርያት)ብዛት፣ ጥንካሬና የንቃት ጥልቀት እንደሌሎቹ ካፒታሊዝም የጎለመሰበት የአውሮፓ ኡገሮች ሠራተኞች ስላልነበረ በሌኒን የሚመራው የሩሲያ ኮሚኒስት ፓርቲ  የሠራተኛው መደብ ፊታውራሪ (Vanguard of the proletariat) ሆኖ የሠራተኛውን ጥቅም እንዲያስጠብቅ ሞግዚት ሆኖ ራሱን ሾመ። ምንም እንኳን በ1840ዎቹ የሠራተኛውን አምባገነናዊነት ፅንሰ-ሀሳብ የቋጨው ካርል ማርክስ፣ ማንኛውም በሥልጣን ላይ ያለ መንግሥት አምባገነን ስለሚሆን ፕሮሌታርያቱም ሥልጣን ከያዘ የሠራተኛው አምባገነንነት (Proletariat Dictatorship) ይፈጥራል ብሎ ነበር። ሆኖም በሩስያው የጥቅምት 1917 አብዮት አምባገነንነቱ የፕሮሌታርያቱ መደብ መሆኑ ቀርቶ የፊታውራሪው  ሞግዚት የኮሚኒስት ፓርቲው  ተቆናጠጠ። ከአብዮቱ በፊት በኮሙኒስት ፓርቲ ምሥረታ ወቅት አንዱ ውይይት የነበረው ሩሲያ ገና ከፊውዳል ሥርዓት ሙሉ በሙሉ ስላልተላቀቀችና ሩስያ ውስጥ ጠንካራና ብቁ ፕሮሌታርያት ባለመኖሩ ማርክሳዊ ርእዮተአለምን ሙሉ በሙሉ መተግበር አይቻልም በሚለው ሃሳብ ዙርያ ነበር።  የነሌኒን ውሳኔውም በሩሲያ ውስጥ በቅድሚያ የፕሮሌታሪያቱን አምባገነናዊ ሥርዓት በመመሥረት አብዮቱ በሁለት ደረጃዎች ተካሂዶ  ወደ ኮሚኒዝም መሸጋገር አለበት የሚል መርሆ ተከተሉ። ለዚህም የሚሆን የተለየ ድርጅት መመሥረት እንዳለበትና ይህም ድርጅት “የሠራተኛውና የጭሰኛው አብዮታዊ  ዴሞክራሲያዊ አምባገነንነት” እንዲሆን ተደነገገ። በዚህ ፅንሰ ሃሳብ፣ ፓርቲው በማዕከላዊ ቁጥጥር የጠነከረ እንዲሆንና አመራሩም በርዕዮተ አለሙ ባመኑ አብዮተኞች ብቻ እንዲሆን ተወሰነ። እነዚህም አብዮተኞች በዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት ተደራጅተው መዋቅሮች ዘርግተው በገበሬውና በፋብሪካ ሰራተኞች ውስጥ ሰርገው  በመግባት ትግሉን ይመራሉ ብሎ በማሰብ ነበር። ይህም ሥርዓት የሠራተኛውን (ፕሮሌታሪያቱን) የሥልጣን በላይነት አስጠብቆ ወደኮሚኒስት ሥርዓት ለመሸጋገር ያዘጋጀዋል ተብሎ ታምኖበት ነበር። ሌኒንና የኮሚኒስት ፓርቲው ጨቅላው የሠራተኛው መደብ በተደራጁ የቀድሞው መንግሥትና ፀረ-አብዮተኞች (አድሃርያን) በቀላሉ ሊገለበጥ ይችላል የሚል ፍርሃት ነበራቸው።
ከምሥረታውም ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት ዴሞክራሲን ለሁሉም ሕብረተሰብ ያለአድሎ ለመተግበር ሳይሆን በሥልጣን ላይ ላለው ድርጅት አምባገነናዊ አገዛዝን ለማመቻቸት ነው። በተጨማሪም በፓርቲው ውስጥም ሆነ በፓርቲው ሥር ባሉ ድርጅቶች ውስጥ ነጻ የሆነና የተለያዩ ወይም የሚቃረኗቸው ሐሳቦች መወያየት ፓርቲውን ይከፋፍለዋል የሚል እምነት ስለነበረ የፓርቲውን የበላይነት ለመጠበቅ ሲባል ተቃራኒ ሃሳቦችንና ተቃዋሚ አንጃዎችን አይፈቅዱም።
በዲሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት(አምባገነንነት) ሥር የፖሊቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሚሊታሪ መዋቅሮች ተጠያቂነታቸው ለገዥው ፓርቲ ወይም መሪ ነው። በዚህ ሥርዓት ውስጥ የገዢ ፓርቲው ወይም መሪው እነዚህን መዋቅሮች የራሱን አምባገነንነት እና ህልውና ለማረጋገጥ እንደፈቀደው የማዘዝና በተቃወሙትም ላይ ሽብር መፍጠር  እንደተገቢና እንደመብቱ ይቆጥረዋል። ሌሎችንም በሥሩ የፈጠራቸውን መዋቅሮች እንደዚሁ ርእዮተ ዓለሙንና የፖለቲካ መስመሩን ለማስከበርና ተቃዋሚዎችን ለመጨቆን ይጠቀምባቸዋል። በእውነተኛ ዴሞክራሲ ላይ የተመሰረተ ሥርዓት የህዝቡን ሰብዓዊ መብቶች ልዑላዊነት ሲያረጋግጥ፣ የመደራጀት፣ የመሰብሰብ፣ ያለምንም ተፅዕኖ ሃሳብን መግለፅን፣ በፈለጉበት እንዲኖሩ፣ ተወካዮቻቸውን ያለመንግሥት ተፅዕኖ እንዲመርጡ ሲያከብርና ሲጠብቅ በማዕከላዊነት ላይ የተመሠረተው “ዴሞክራሲ” ደግሞ የገዢው መንግሥት ፍፁማዊ አገዛዝ ያስከብራል።
ቀዝቃዛው ጦርነት፣ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት እና  የቅኝ ሐገራት ነፃነት እንቅስቃሴ 
ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ድምደማ በኋላ በሶቪየት ሕብረት የሚመሩ የሶሻሊስት ሐገሮች በአንድ ወገን፤ በአሜሪካ መሪነት የተሰማራው የምዕራቡ የካፒታሊስት ሐገሮች ደግሞ በሌላው ወገን በመሆን እስከ 1990ዎቹ  የቆየ የቀዝቃዛው ጦርነት (cold war)  ያካሄዱ ነበር። በዚህም ጦርነት ጊዜ ሶቪየት ሕብረት የምስራቅ ብሎክ (Eastern Bloc) ወይም የኮሚኒስት ብሎክ የሚባል ቡደን ፈጥረው የዴሞክራቲክ ሶሻሊዝም ንቅናቄዎችን ለማስፋፋትና ኮሚኒዝምን የዓለም ሥርዓት ለማድረግ (ስለዚህም ኢምፔሪያሊዝምን ለማጥፋት)  ራዕያቸውን ሲተገብሩ በአሜሪካ የሚመራው የካፒታሊስት ሐገሮች ቡድን ደግሞ የምዕራብ ብሎክ (Western Bloc) ተብሎ የሶቪዬት መስፋፋት ለመግታት ተሰልፈው ነበር። ሁለቱም ኃያላን ቡድኖች በዚሁ ጊዜ ዘመናዊ የጦር መሳርያ መገንቢያና ማከማቻ፤ የጦር ሰራዊታቸው  ማሰልጠኛና ማጠንከሪያ፤ የፕሮፓጋንዳና የስለላ ጦርነት ማካሄጃ አደረጉት። ሁለቱም ጎኖች ለሚደግፉት ሃገር ወይም ተዋጊ ግንባር ገንዘብ በመስጠትና መሳርያ በማስታጠቅ ጦርነታቸውን በወኪል ተዋጊዎች (Proxy Warriors) ማድረጉን መረጡ።
በዚሁ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ብዙዎች በቅኝ ግዛት ሥር የነበሩ የአፍሪካ፣ የእስያና የደቡብ አሜሪካ ሐገሮች የነፃነት ትግል ሲያካሂዱ ርዳታ ያገኙት ከሶቪዬት ሕብረት ነበርና ከነፃነት በኋላ ብዙዎቹም የሶቪየት ሕብረትን ፈለግ በመከተል አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሶሻሊዝም በመገንባት ላይ ተሰማሩ። አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ሶሻሊዝም  የፖለቲካ ኃይል በጥቂቶች እጅ አከማችቶ በማዕከላዊነት ላይ የተመሰረተ አምባገነናዊ አገዛዝን አሰፈነ።   እነዚህም ሐገሮች ከአፍሪቃ አንጎላን፣ ዚምባብዌን፣ ሞዛምቢክን፣ ሳኦ ቶሜ ፕሪንሲፕ፣ ኮንጎ ብራዛቪል፣ ናሚቢያ፣ ጊኒ ቢሳዎና የመሳሰሉትን ሲጨምር፤ ከደቡብ አሜሪካ ኩባ፣ ኒካራጉዋ፣ ግሬናዳና የመሳሰሉት ሆነው፤ ከእስያ ደግሞ ኢንዶቻይና የመሳሰሉት ነበሩ። ቻይናም በኮሚኒስት ፓርቲው በኩል የሯሳን ማኦይስት ሞዴል መሥርታ እነኮሪያ፣ ቬትናም፣ አልባኒያና የመሳሰሉትን ከኋላዋ አስከተለች።
ከላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትና የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አፈጣጠር የአንድን ድርጅት የበላይነት ለማረጋገጥ ነው።
ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት በደርግ ዘመን
ኢትዮጵያ እንደሌሎቹ የአፍሪቃ ሐገሮች በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ሥር ባትወድቅም ብዙ የአውሮፓ መንግሥታት ቅኝ ሊያደርጓት ብዙ ሞክረዋል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ጣሊያን ከሐገራችን ተባርሮ የመልሶ ግንባታው ሲጀመር የኢኮኖሚ አርዳታና የመከላከያ ኃሎቿን መገንቢያ ከምዕራብ ሐገሮች ስታገኝ ቆይታ ከ1966 አብዮት በኋላ ሥልጣን የተቆናጠጠው “ጊዜያዊ” ወታደራዊ መንግሥት በማርክሲዝም-ሌኒኒዝም ርዕዮተ ዓለም በመጠመቁ ከምዕራብ ፊቱን ወደሶቪዬት ሕብረት  አዞረ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሁሉም የእርዳታና መሳርያ ምንጩ የምስራቁ ብሎክ ሆነ፣ አገዛዙም እንደዚሁ። ውጤቱም ሐገሪቷ በወታደርዊ አምባገነንነትና በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥ ውስጥ ለ17 ዓመታት ማቀቀች። ይህም የ17 ዓመታት አባዜ ሐገሪቷን በሁሉም ዘርፍ አድክሟት ለሕወሐት ሰለባ ዳረጋት። የተገላቢጦሽ ደግሞ የሕወሐት አማካሪ፣ ደጋፊና መሳሪያ አቀባይ የምዕራቡ ብሎክ ሐገሮች፣ በተለይም አሜሪካ ሆነች። ከደደቢት ጀምረው አዲስ አበባ እስከገቡ ድረስ በአሜሪካው የስለላ ድርጅት እንክብካቤነት አድገው  የደቀቀች ኢትዮጵያን ወረሩ ።
አምባገነናዊ ማዕከልነት በሕወሐት-ኢሕአዴግ እጅ እያደረሰ ያለውን ሰቆቃ እያየን ነው። የሕወሐት-ኢሕአዴግ ስንኩል ሕገመንግሥትም በሕዝብ ፊት “ሕጋዊነትን” እንዲያገኝ ይህንኑ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አምባገነንነት መሥርቶ ላለፉት 27 ዓመታት ሕዝቡን የመከፋፈያና የራሱን ሕይወት ማራዘሚያ አድርጎታል። በነዚህ ዓመታት የሠራተኛውም ሆነ የገበሬው መደብ ሥልጣን መያዝ ቀርቶ ስማቸውም አይጠቀስም። ለሰብዓዊ መብት ታጋዩ ፕሮፈሰር አለማየሁ ገብረማርያም ይህንኑ የሕወሐት አምባገነንነት “… a thugocracy privatelymanaged and operated for theexclusive benefit of bloodthirsty thugtators.” (6) ብሎ ሰይሞታል።
ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት :- የሕወሐት-ኢሕአዴግ ቆርጦ ቀጥል ሥርዓት
የሕወሐት-ኢሕአዴግም መንግሥት የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን አገዛዝ የሚደግፉትን መሾሚያ፣ የሚቃወሙትን  መደፍጠጫ፣ ሕዝቡን በዘርና በጎሳ መከፋፈያ መሳሪያ አድርጎታል። በሥሩም የተፈጠሩት የተለያዩ ድርጅቶች የሕወሐት-ኢሕአዴግ አምባገነናዊነት ምሰሶ ከመሆን ሌላ እውነተኛ ዴሞክራሲን የሚያሳድጉ ተቋሞች መሆን አይችሉም። ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊት ኢ-ዴምክራሲያዊ ስለሆነ የመድብለ ፓርቲንና ሁሉን የሕብረተሰብ ክፍሎች የያዘ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በተግባር አይቀበልም። ሕግ አውጭው፣ ሕግ ተርጓሚውና ሕግ አስፈፃሚው አንድ ሲሆን የሚያገለግለውም በሥልጣን ላይ ያለውን ፓርቲ ነው። ሕጉንም የሕወሐት-ኢሕአዴግ መንግሥት አንዳመቸው ሲለውጠውና አዲስ ሕግም ሲደነግግ ነበር። በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እነዚህ ሦስት አውታሮች አብሮ መሥራት ብቻ ሳይሆን እርስበርስ በመቆጣጠር የአገሪቷን ሕጋዊ ጉዳዮች ያካሂዳሉ። በዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት ሦስቱም አውታሮች እንደአሻንጉሊት ክሮች የሚስበው የሕወሐት-ኢሕአዴግ መንግሥት ነው። በተጨማሪም የተለያዩ የኢኮኖሚው አውታሮችን፣ ምክር ቤቱን፣ የደህንነት ጥበቃውን፣ የመከላከያ ሰራዊቱን እና የመሳሰሉትን ለራሱና ለደጋፊዎቹ ጥቅም ያውላል።
ዶክተር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ሕልሞች – የኢህአዴግ ቆርጦ ቀጥል ፖለቲካ” በተሰየመው መጽሐፋቸው ውስጥ የኢህአዴግ አብዮታዊ ዴሞክራሲ የፈጠራቸውን (ያስከተላቸውን) ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታም ሆነ ለልማት ብልፅግና አንቅፋት የሆኑትን አሥር ነጥቦችን በትክክል አስፍረዋል። ከነዚህም ውስጥ አንዱ ነጥብ “… የኢህአዴጉ ‘አብዮታዊ ደሞክራሲ’ ከሁሉም በላይ መንግሥትንና የመንግሥት ተቋማትን የአንድ ፓርቲ የግል ሃብት የሚያደርግና የመንግሥት ተቋማት ዋና ሥራቸው መሪዎችን ሥልጣን ላይ ለማቆየትና በሕግ የሚታወቀውን መንግሥትን ተክቶ የሚሠራ መንግሥት መፍጠሩ ነው። የዚህ ሁሉ ችግሮች እናት ሁሉ….. ደግሞ ከኢህአዴግ ‘አብዮታዊ ዴሞክራሲ’ የሚመነጨው የአንድ ፓርቲ የበላይነት (hegemony) ሕልም ነው።”(1)
ሕወሐት ለራሱ አመቻችቶ የፈጠረውን ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊ አምባገነንነት የ1968ቱን ማኒፌስቶ እቅድ ከግብ ለማድረስ እየተጠቀመበት ነው። ኢትዮጵያን በዘር ከከፋፈሏትና የሕዝቡንም አንድነት ካዳከሙት የሕወሀት-ኢሕአዴግ ተግባሮች ጥቂቶቹን ከዚህ በታች ቀርፌ አቅርቤአለሁ።
አንደኛ – ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን በመጠቀም እንደ ደቡብ አፍሪቃው አፓርታይድ ሥርዓት ሕዝቡን በጎሳ፤ በቋንቋ፤ በክልል ከፋፍለው በማዳከም፤ የጨቋኝና ተጨቋኝ ብሔሮች ግንኙነት ፈጥረው የሐገሪቷን አንድነት አቃወሱት። ይህም ሕወሐት የራሱን ክልል ለማልማትና ሌሎቹ፣ በተለይም አማራውና ኦሮሞው፣ ኦሮሞውና ሱማሌው፣ ደቡቦችም እርስበርስና ከጎረቤቶቻቸው ደም አንዲፋሰሱ በማድረግ ብዙ ችግሮችን ፈጥረዋል። በሕወሐት-ኢሕአዴግ የተፋፋመው የዘር ክፍፍል ለኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ህመም መሆኑ እንደማይቀር አይጠረጠርም።
ሁለተኛ – የሥርዓቱን የብዝበዛና የሌብነት መርበብ ዘርግተው የሐገሪቷን ሐብት ለግላቸውና ለደጋፊዎቻቸው መበልፀጊያ አድርገው የኢትዮጵያን ሕዝብ በኢኮኖሚያዊ ገደል አፋፍ ተንጠልጥሎ እንዲሰቃይ አደረጉት። ያለገደብ አንዲያድጉና እንዲዘርፉ የተለቀቁት እንደ ሜቴክ፣ ኤፈርት፣ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽንና የሌሎችም ትላልቅ ኩባንያዎች የዝርፊያ መናኸሪያዎች ሆነው የባለሥልጣናትን፣ የዘመዶቻቸውንና የአጎብዳጆቻቸውን የውስጥና የውጭ ባንኮች አካውንቶች አንዲሞሉና የቅምጥል ኑሮ እንዲኖሩ አድርገዋል።
ሦስተኛ – ከማዕከላዊ መንግሥት ውጭ ለመሥራት የሞከሩ፣ ሥርዓቱን በተቃወሙ፣  አረመኔያዊ ተግባራቸውን ለዓለም ለማጋለጥ የታገሉት ጦማሮችን፣  ዓይን ባወጣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በሽብርተኝነት ወንጀል ሰብስበው በየእሥር ቤት ከተቱ፤ ገረፉ፤ ሰለቡ፤ አሰደዱ፤ ገደሉ። ይህንንም ግፍ ሲፈፅሙ በአስቸኳይ ጊዜያዊ አዋጅና በፀረ-ሽብር ሕግ ጥላ ሥር ተደብቀው ነው። የሕወሐት ፀረ ሽብር ሕግ በ1967 ዓ. ም. ከታወጀው የደቡብ አፍሪቃው ፀረ ሽብር ሕግ ጋር ተመሳሳይ ነው። የፕሪቶሪያው ዘረኛ መንግሥት እነዊኒ ማንዴላንና ሌሎችንም አፓርታይድን የሚዋጉ አካሎች በዚህ ሕግ ተጠቅመው ነበር ሲያስሯቸው፣ ሲገርፏቸውና ሲገድሏቸው የነበረው።(2)
አራተኛ – ሕወሐት-ኢሕአዴግ በወታደራዊ ትጥቅ፣ በገንዘብ፣ በቁሳቁስና፣ በምክር ርዳታ ሰጥተው ለሥልጣን ያበቋቸውን የምዕራብ ሃገሮችን ለማስደሰት ሲሉ የነፃ ገበያን (free market) ከዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊ አምባገነንነት  ጋር አዳቅለው መላቅጡ የጠፋበት የኢኮኖሚ መዋቅር ፈጠሩ። በኢትዮጵያ ሁኔታ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን ከነፃ ገበያ ጋር ለማደባለቅ መሞከር አምባገነኖች ጡንቻ ለማጠንከርና ከላይ በተጠቀሱት የመንግሥት ሞኖፖሊዎች መበዝበዝን መርዳትና  ሌላውን የግል ነጋዴዎችን እንዳይንሰራፉ ለማድረግ ነው። ያልተገደበ ዴሞክራሲያዊ ነፃነት (የመናገር፣ የመሰብሰብ፣ እንደልብ የመንቀሳቀስና በንግድ ሥራ መሠማራት) በሌለበት ሁኔታ ከራሱ አምባገነናዊ ጥቅም ውጭ የማይፈቅድን ሥርዓት ነፃ ገበያን በተግባር ላይ ሊያውል አይችልም(1,5)።
አምስተኛ – የምርጫ ቦርዱን እንደራሳቸው መሳርያ በመጠቀም የምርጫ ውጤቶችን በማስለወጥ ሲሸነፉ በማጭበርበር አሸናፊ ሆኖ መቅረብ፤ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላትን በማሰርና በመግደል እውነተኛና አድልዎ የሌለበት ምርጫ እንዳይካሄድ አድርገዋል። ይህም የማጭበርበሪያ የምርጫ ቦርድ በነሱ ቁጥጥር ሥር ሆኖ  የነሱ ዕድሜ ማርዘሚያ  አንጂ ገለልተኛና አድልዎ የሌለበት ምርጫን ለማስተግበር አልነበረም። በዶክተር መረራ አገላለጽ የምርጫው ቦርድ ለሕወሃት ሥልጣን ላይ መቆያ ከሆኑት ሁለት ምርኩዞች አንዱ ሆኖ ቆይቷል። ሁለተኛው ምርኩዝ የጠመንጃ አፈሙዝ ነው።
ስድስተኛ – በካድሬዎቻቸውና በስለላ መርበቦቻቸው በሰፈርና በቤተሰብ ውስጥ ጠልቀው በመግባትና ሕዝቡን ለረጅም ዘመናት ያስተሳሰረውን የባሕል “ድርና ማግ” በመበጣጠስ፤ የሕዝብን መሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች በመወንጀል ከሥልጣን አውርደው የራሳቸውን ካድሬዎችና ታማኞች በመትከል፤ ሕዝቡ እርስ በርሱ እንዳይተማመንና በጥርጣሬና በፍርሃት እንዲጠላላ አድርገውታል። ይህ ዓይነቱ የከፋፍለህ ግዛ ተንኮልና የራሳቸውን ጎሳ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የባህል ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን በመያዝ የበላይነትን እንዲያገኙ የማድረግና የሌላውን ሕዝብ በነዚሁ አውታሮች የበታች እንዲሆኑ በመጨቆን፣ ቀድሞ የነበረውን የሕብረተሰብ ክፍል በማባረር ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን በመተካት ከፍተኛ የህብረተሰባዊ  ምህንድስና (ሶሻል ኢንጂነሪንግ) በማከናወን ላይ ተሰማርተዋል። በዘርና በብሄር ለይቶ ሰውን የበላይነትና የበታችነት  መፍጠር የባርያ ሥርዓት ባሕርይ ነው።
የለውጥ ጭላንጭል
ኢትዮጵያና ሕዝቧ ከ40 ዓመታት በላይ በፈጀ አምባገነናዊ አገዛዝ ሥር ተቆራምተው ብዙ መቶ ሺዎች ሕዝብ ካለቀ በኋላና ያንኑም ያህል በስደት ከተበታተነ በኋላ አሁን የለውጥ ጭላንጭል እየታየ ነው። ይህም የለውጥ ጭላንጭል ሊመጣ የቻለው የኢትዮጵያ ሕዝብ የረጅም ጊዜ ትግል  በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደማይመለስበት ደረጃ (critical juncture) ላይ በመድረሱና ምንም ዓይነት ጊዜያዊ አዋጅም ሆነ የጠመንጃ ጋጋታ ሊያቆመው አለመቻሉ ነው።  ይህም ሕዝባዊ አመጽ የገዢውን ፓርቲ ከመሠረቱ አናግቶት የጠቅላይ ሚንስቴር ኃይለማርያም ደሳለኝን በ”ፈቃደኝነት” ከሥልጣን  መውረድን አፋጥኖ የዶክተር አብይ አሕመድን  ወደሥልጣን መምጣት ጥርጊያ መንገድ ከፍቷል።
ክቡር ጠቅላይ ሚንስቴር ዶክተር አብይ አሕመድ ድርጅታቸው ቢወድም ባይወድም ያለፉትን የሕወሐት-ኢሕአዴግን አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የመንግሥት ሽብርተኝነት አምኖ በግልፅ ጥፋቱን በመቀበል ራስን የማነፅና ሥሕተቶችን የማረም ጉዞ ጀምሯል። ይህ ሂደት በራሱ የኢትዮጵያን ሁኔታ ልዩ ያደርገዋል። አንድ  አምባገነናዊ ገዢ ፓርቲ በምንም ዓይነት ሁኔታ ቀጥቅጦ ሲገዛው ለኖረው ሕዝብ እራሱን አጋልጦና ስህተቱን በግልፅ አምኖ ይቅርታ በመጠየቅና ለውጦች ለመተግበር የተነሳበት ሁኔታ በታሪክ ጥቂት ነው።
የክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ከሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቢደገፍም ከራሱም ፓርቲ ውስጥ ተቃውሞ ደርሶበታል፤ በአደባባይ የግድያና የመፈንቅለ መንግሥት  ሙከራዎች ተደርገውበታል። ሆኖም ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ይህንን ለውጥ ከግቡ ለማድረስ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው። እሱና ደጋፊዎቹ ለለውጡ መቆማቸውን በወሰዱት እርምጃዎች አሳይተዋል፤ እያሳዩም ናቸው። በግፍ የታሰሩ ተቃዋሚዎችንና የሚዲያ ሰዎችን ፈተዋል፤ ሰብዓዊ መብትን የጣሱና የኢትዮጵያን ሕዝብ ያሰቃዩትን ሰብስበው በሕግ ተጠያቂ ማድረግ ጀምረዋል፤ የካቢኔና የአመራር ለውጥም እያካሄዱ ነው። ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ድርጅቶች እንዲመለሱና የዴሞክራሲያዊ  ሥርዓት መመሥረቱ ላይ እንዲሳተፉ በሩን ከፍተዋል፤ የሐገሪቷን የመከላከያ ኃይልም ከአንድ ፓርቲ አገዛዝ ለማላቀቅ አየሠሩ ነው፤ በሌብነት ሐገሪቷን ያራቆቱትንም እያሳደዱ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃም ብዙ የሚያረኩ ድርጊቶችን አስመዝግበዋል።  ከ18 ዓመታት በላይ የፈጀውን የኤርትርያና የኢትዮጵያን ፍጥጫ ወደሰላም አድርሰዋል።
በተቃራኒውም ጥቅማቸው የተነካባቸው የገዢው ፓርቲ ተጠቃሚዎችና ደጋፊዎቻቸው አንዲሁም ከሐገሪቷ ውጭ ሆነው ሃገሪቷን ሊበታትኑ የሚፈልጉ ድርጅቶች ለውጡን ለመቀልበስ ሌት ተቀን እየጣሩ ናቸው። ፀረ-አንድነት ወሬዎችን በአስመሳይ ሶሻል ሚድያ በመዝራት፤ ገንዘብና ትጥቅ በመስጠት ሐገሩን በዘርና በቋንቋ ለያይተው ለማጋደል እየሠሩ ናቸው።  የሕወሐት አባላትና ሎሌዎቻቸውም የአብዮታዊ ዴሞክራሲና ሕገመንግስቱ ይከበር እያሉ እያለቀሱም ናቸው። በዚህም ለቅሷቸው ምን ለማለትና ለማድረግ እንደሚፈልጉ ማወቅ አያዳግትም።  ግምገማና ተሃድሶ! እያሉም ደጋግመው የሚጮሁ የሕወሐት ሰዎችም እስከዛሬ ድረስ በዚያው በግምገማና ተሃድሶ ሕዝቡን ሲያታልሉት ኖረው የሃገሪቷን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ሰብዓዊ መብቶችን ተሰምቶ ከማይታወቅበት አሳፋሪ ዝቅጠት ውስጥ ከተውታል። ከመጀመሪያው በተጣመመ መሠረት ላይ የተገነባውን መዋቅር ምንም ዓይነት ግምገማና ተሃድሶ ሊፈውሰው እንደማይችል ለማየት ተስኗቸዋል። እነሱ ግምገማና ተሃድሶ ባደረጉ ቁጥር የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰቆቃ እየባሰበት እንጂ እየቀነሰለት አልሄደም። ለሕወሐት ደላሎችና ካድሬዎች ግምገማ እናድርግ ማለት “ጨቁነናችሁ አላበቃንምና ዘይቤያችንን አድሰን ለበለጠ ብዝበዛ እንድንመለስ ሌላ ዕድል ስጡን” ማለት ይመስላል።
መዘንጋት የሌለብን አብዮታዊ ዴሞክራሲ ወይም ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት አሁንም የሕወሀት-ኢሕአዴግ መንግሥት አምባገነናዊ የአገዛዝ ስልት ሆኖ እንዳለ ነው። የአሁኑም  አምባገነናዊ ሥርዓት በእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መተካትና  ሕገመንግሥቱ ዴሞክራሲን እንዲደግፍ መሻሻል ወይም መለወጥ ይኖርበታል። ስለዚህም ይህን ለውጥ ወደፊት ማራመድና እውነተኛው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲፈጠር ተግቶ መሥራት  የሁላችንም ሃላፊነት ነው።
ይድረስ ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ድርጅቶች
ቁጥራችሁ የበዛ አገር አቀፍ እና ክልላዊ ፓርቲዎች ተደራጅታችሁ እንዲሁም ሌሎች ተቃዋሚ ድርጅቶች፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ተሳትፋችሁ የሕወሐት-ኢሕአዴግን መንግሥት ስትጋፈጡት  ቆይታችኋል። ለዚሁምበድርጅትም ሆነ በግለሰብአስከፊ ስቃይ ተቋቁማችሁ ለአገራችሁም ፍቅር ከፍተኛ ዋጋ ከፍላችኋል። በተቃራኒውም ሲታይ ልዩነቶቻችሁ የጠነከረ ድርጅት አንዳትፈጥሩና በሕብረት እንዳትታገሉ እንቅፋት ሆኖባችኋል። ይህም እውነታ ሕዝቡንም በመከፋፈል በጠነከረ አንድነት አንዳይታገል አድርጓል። ይህንንም ድክመት የሕወሐት-ኢሕአዴግ መንግሥት የራሱን ሥልጣን ላይ ማራዘሚያ አድርጎ ተጠቀሞበታል። አሁንም ልዩነታችሁን ወደጎን አስቀምጣችሁ ይህን  የለውጥ ዕድል ተጠቅማችሁ ጠንካራ ድርጅት በመመሥረት ለሐገራችን ዴሞክራሲያዊ  መንገድ መቀየስ ይኖርባችኋል። ይህንም ማድረግ ባትችሉና የኢትዮጵያን ሕዝብ እንደገና ለጭቆና ቀንበር አሳልፋችሁ ብትሰጡ ውርደቱ የናንተና የናንተ ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብም ይፋረዳችኋል። በዶክተር አብይና ረዳቶቹ በሩ ተከፍቷል። ለምን ጊዜ ያህል ተከፍቶ እንደሚቆይ የሚወሰነው በእናንተና በኢትዮጵያ  ሕዝብ ነው።  በምንም መንገድ የ97ቱም ሆነ የ2002ም ሆነ የ2007 የምርጫ ቀውሶች መደገም የለባቸውም። ከአሁን ወድያ የምርጫ ሳጥኖች ተስፋ በቆረጠ ሕዝብ “የስድብና የተበላሹ የምርጫ ወረቀቶች”(5)ተሞልተው ማሸነፍ የሌለበት ፓርቲ የሚያሸንፍበት ምንም ምክንያት አይኖርም። ኢትዮጵያ ወደፊት የመራመድ እንጂ ወደኋላ የመመለስ ምርጫ የላትም።
ማጣቀሻዎች፡
  1. ዶክተር መረራ ጉዲናየኢትዮጲያታሪክና የሚጋጩ ህልሞችየኢህአዴግ ቆርጦ ቀጥል ፖለቲካ, 2008 እትመት
  2. Nelson Mandela – Long Walk to Freedom
  3. ኤርሚያስ ለገሠየመለስ ልቃቂት
  4. በተለያዩ አከባቢዎች ለሚቀሰቀሱግጭቶች ህወሓቶች እና አክቲቪስቶች ተጠያቂ ናቸው! Seyoum Teshome October 27, 2018 – https://ethiothinkthank.com/2018/10/27/the-role-of-tplf-elites-and-activists-in-inciting-ethnic-conflict/
  5. ሀብታሙ አያሌውከህወሓት ሰማይ ሥር, 3 እትም
  6. ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም – “The End of Thugtatorship and Rise of the Rule of Law in Ethiopia”. November 19, 2018.  https://ecadforum.com/2018/11/19/the-end-of-thugtatorship-and-rise-of-the-rule-of-law-in-ethiopia/
  7. Daren Acemoglu & James A. Robinson -Why Nations Fail –
  8. https://www.britannica.com/topic/democratic-centralism
  9. http://nazret.com/blog/index.php/2006/12/10/ethiopia_tplf_revolutionary_democracy
  10. https://www.opride.com/2017/12/29/ethiopia-eprdf-ditch-democratic-centralism-avoid-civil-war/
https://yefiyefitun.wordpress.com

Wednesday, November 7, 2018

Mycobacteriosis in fish(By Rodrigo Orrego)










Mycobacteriosis in fish is a disease that is difficult to detect and therefore often underdiagnosed. For the same reason, information about the effects of this disease on the fish farming industry has been limited
The development of two diagnostic tests has led to the discovery of a mycobacterium which causes disease in both cod and salmon and has never been detected in Norway before. Reports submitted to the authorities of mycobacteriosis (tuberculosis) in fish have been sporadic and have only stemmed from aquarium fish or wild fish, not farmed fish. This is probably due to underdiagnosis. Adam Zerihun’s doctoral research has led to the development of two methods of diagnosis based on real-time PCR and immunohistochemistry respectively. The tests are extremely sensitive and have been instrumental in detecting a mycobacterium that has never been found in Norway before. The bacterium was found both in farmed salmon and in burbot and experimental infection showed that Atlantic cod was very susceptible to the bacterium and became diseased. The isolated bacterium was identified as Mycobacterium salmoniphilum.In cod and burbot infected with M. salmoniphilum, Zerihun discovered serious nodules, while only small or no such changes were found in infected Atlantic salmon. The formation of nodules in cod was shown to undergo several phases of development. The identification and characterization of these different stages are important for the appraisal of disease development and in order to estimate the time of infection. Zerihun’s study indicates that the occurrence of the disease in farmed Atlantic salmon and in cod is more widespread than previously thought, both with regard to the range of host and climate variations.Since the formation of nodules is not a typical symptom in salmon infected with M. salmoniphilum, it is highly probable that many cases of tuberculosis in salmon remain undiscovered. Fish that lose weight without there being any apparent disease or specific cause are classified in fish farming as “lost fish”. A mycobacterial infection can be lurking behind various different symptoms, where weight loss is one characteristic.
For this reason, many salmon infected with tuberculosis can be the undetected reason for losses in the industry. The stress that arises when many fish are kept in closely packed surroundings weakens their immune system and allows mycobacteria to reproduce in many individuals. These factors are known to promote the occurrence of mycobacteriosis.DVM Mulualem Adam Zerihun defended his doctoral research on 11th January 2013 at the Norwegian School of Veterinary Science with a thesis entitled: “Mycobacteriosis in marine and freshwater fishes: characterization of the disease and identification of the infectious agents”. Biography: Mulualem Adam Zerihun was born in Ethiopia and qualified as a veterinary surgeon at Humboldt University in Berlin, Germany in 1989. He has worked as a district veterinary surgeon, ranch manager and researcher in Ethiopia and as a researcher at the Norwegian Veterinary Institute in Oslo since 2004, where he was a research fellow from 2006-2010. Contact information: Mulualem Adam Zerihun Tel.: + 47 67 53 92 95 Tel. work: + 47 23 21 64 40 Mobile: + 47 415 09 453 Email: adam.zerihun@vetinst.no Magnhild Jenssen, Information Officer at NVH Tel.: +47 77 66 54 01 Mobile: +47 957 94 830 Email: magnhild.jenssen@nvh.no

Wednesday, September 26, 2018

ከሰሞኑ የከሸፈው የመንግስት ግልበጣ ሙከራ ሚስጢሮች ( ዳነኤል)


የጠ/ሚ አብይ መንግስትን የመገልበጥ ሙከራ እንቆቅልሽ!

የመንግስት ግልበጣ ውጥን ነበር ከሽፏል! ፥,አሁንም ያልከሸፈው ከግልበጣው ጀርባ ያለው ፓለቲካዊው ቁማር ነው:: ይህም ቀጥሏል::
የመንግስት ግልበጣው መሃንዲስ ህወሃት ሲሆን የሴራው ተባባሪዎቹ አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦነጋውያን(OLF)ና አክቲቪስቶች ናቸው:: 


A). የመንግስት ግልበጣ ጠንሳሾች የጋራ አላማና አንድነት bበአጭሩ:-

1. ህወሃት(TPLF) አፓርታይዳዊ የህዳጣን ሥርዐቱን ለመመለስ፣ ይህ  ደግሞ ካልተሣካ ኢትዮጵያን ለመበታተን

2. የጠ/ሚ አብይና የፕ/ት ለማ መገርሣን  ኢትዮጵያዊ ቀመር በሁለቱም ሃይሎች አለመወደድ

3. አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ ኦነጋውያን(OLF)ና አክቲቪስቶች አንድም ኦሮሚያን የመገንጠል ይህ ካልሆነ የብዝሃን ጎሣ አምባገነን መንግስት (multiethnic government)መመስረት ህልም ለመተግበር

4. የአርበኞች ግንቦት 7 መምጣትና ይህን ተከትሎ በትላልቅ ከተሞች ላይ የታየው የኢትዮጵያዊነት መንፈስ መነቃቃት፣ ማበብና ማንሰራረት ለህወሃትም ይሁን ለአክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞች (OLF, TPLF).ምቾት ስለነሳቸውና በነዚሁ ከተሞች ያለው ሕዝብ እንደማይመርጣቸው ማወቃቸው ዋነኛው ምክንያት ነው::

 የመንግስት ግልበጣው ሴራና ዕቅድ!


ሀ). የመንግስት ግልበጣው ቅድመ ዕቅድ (pre-coup d’etas Contingency plan)

በድሬዳዋ፣ ቡራዩ፣  አዋሣና አሰላ የዘር ጭፍጨፋ በማድረግ ሕዝቡ በቁጣ ገንፍሎ የፕሮፓጋንዳቸው ሠለባ ማድረግና ለአመፅ መገፋፋትና የጠሚ አብይን መንግስት ከቁጥጥሩ በላይ የሆነ ክስተትን መቆጣጠር አልቻለም የሚል ግንዛቤን በሕዝብ ውስጥ በማስረፅ ለቀጣይ ዕቅድ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ነበር::
ለ). የመንግስት ግልበጣ ድህረ ዕቅድ
(post - coup d’etas Contingency plan)

1. አዲስ አበባ አቀፍ ሰልፍ መጥራትና በሰልፈኞቹ መንገድ  በመዝጋትና ማህበራዊና የንግድ አገልግሎትን ማሰናከል

2. ኢቲቪ*ETV(ና ፋና ሬዲዮ ጣቢያን መቆጣጠር

3. ኦሮሚያ ባህል ማዕከልን፣ ባንክ ፣ ኢንሹራንስ መንግስታዊና የግል የንግድ ተቋማትን በመቆጣጠር፣ በመዝረፍና በማቃጠል የአካባቢውን የኦሮሞ ገበሬን በቁጣ በመቀስቀስ ከተማዋን ማስወረር የትግራይ ተዎላጆችን ንብረት የሆኑትን ህንፃን መዝረፍና ማቃጠል

4. የ"ጎሣ ፌደራሊዝምን" (ethnic federalism)እና የተዎሰኑ ብሔረሰቦችን  ነጥሎ በመፈክር በማውገዝና በመዝለፍ  ሰንደቅ          ዓላማ  በመቀየር "ህገ መንግስቱ ተጣሰ" በሚል ሴራ  ሐገራዊ ድጋፍን ማሰባሰብ
5. "ሥራዓት አልበኝነት በሃገሪቱ ነግሷል" በሚል ሽፋን "ሕዝብን ከእርስ በርስ እልቂት ለመከላከል ፣ለመጠበቅና ወንጀልን                 ለመከላከል" ጦሩ ጣልቃ ገብቷል የሚል በድርጊት የታገዘ ፕሮፓጋንዳ በማሰራጨት ከዓለም አቀፋዊ ማህበረሰብ ድጋፍን              ማሰባሰብ
6. ህወሃት በሚስጥር ባሰረጋቸውና በአዲስ አበባ የሚገኙ የደህንነትና የጦር ሃይሉች አማካኝነት የጠሚ አቢይን መንግስት ሁኔታው      ከቁጥጥሩ ውጭ ነው በሚል ዶር አቢይን ከስልጣን ማውረድና የጠቅላይ /ሚኒስተር  የለውጥ ቡድን(team Lemma)ና              አጋሮዎቸን ማፈስና ማሰርና (Replacement of incumbent leaders with another)
7. የገቡ የለውጥ ሃይሎችን ሃገር ጥለው እንዳይወጡ የአየርና የምድር ትራንስፖርት በማገድ በቁጥጥር ስር ማዋል

8. የመንግስት ግልበጣው ውጥን የተነደፈው በግንቦት 7 እንደሆነ በማስመሰል ጦሩም ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ ጣልቃ       እንዲገባ ማድረግ የድራማው ክፍል ነበር::

C). የመንግስት ግልበጣው እንዴት ከሸፈ?

የመንግስት ግልበጣው ውጥን ከሰላማዊ ሰልፉ ጥሪ ጋር የተያያዘ ነው:: ሠልፉን የጠራው ይህ የግልበጣ ቡድን ነው:: ውጥኑንም በቅድሚያ የደረሰበት በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ የደህንነት አታሼ ሲሆን የግልበጣውን ዝግጅት
ለጠ/ሚ አብይ መንግስት በጊዜው አሣወቋል:: ለግልበጣውም መክሸፍ አይነተኛ ሚና ተጫውቷል:: የግልበጣው ጠንሳሾች ታውቀዋል:: የጠ/ሚ አብይን  መንግስት ቀጥተኛ እርምጃ ለጊዜው በነዚህ ሐይሎች ላይ እንዳይወስድ ኤምባሲው ጫና አሳድሯል:: በግልበጣው ጠንሳሾች ላይ የሚወሰድ እርምጃ የሚያስከትለውን ፓለቲካዊና ወታደራዊ አንደምታና መዘዝ የጠ/ሚ አብይን መንግስት መመከት አሁን የማይችል በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲያደርግና ስልት እንዲነድፍ በተለይም በወታደራዊውና በደህንነት ዘርፉ ላይ የፍፁም የበላይነትን አቅም ፈጥኖ እንዲፈጥር መክሯል:: ይህ ምክንያታዊም ይመስላል::

D).ከግልበጣው ጀርባ ያለው ፓለቲካዊው ቁማርና ሚስጥር!

የመንግስት ግልበጣው ውጥንና ዕቅድ  ከሸፈ እንጂ የፓለቲካው ሴራና አሻጥሩ ቀጥሏል:: የሀገራችን እጣ እጅግ ፈታኝና አደገኛ አዙሪት ውስጥ ገብቷል::

የመንግስት ግልበጣው መክሸፍ በሁዋላ ሁለት ዓይነት መንግስት አንድ ሐገርን እያስተዳደረ ነው:: አንደኛው የጠ/ሚ አብይ እና ቡድናቸው ነው:: ሁለተኛው በጃዋር
(team Jewar)፣ እዝቅኤልና በቀለ ገርባና በፀጋዬ አራርሳ አማካሪነት የሚመራውና በህወሃት የሚታገዘው የለሌውና  ቤተ መንግስት ያለው "የቄሮ መንግስት" ነው:: ተከታዩን ማየት ይበጃል::

ሀ). የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው (de jour)

ይህ ቡድን አጣብቂኝ ውስጥ ያለ ነገር ግን  የኢትዮጵያ 
ብቸኛው ሕልውና ተስፋ ነው:: ይህ ቡድን በህወሃት ሰራሹ ፓርላማ ውስጥ ማህበራዊ መሠረቱን ኦህዴድን (ኦዴፓ) አድርጎ በደህዴንና በብአዴን ድጋፍ የቆመ መንግስት ነው  ነገር ግን ከኢትዮጵያዊያንና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ድጋፍ አለው:: ስለዚህም ይህን መንግስት የሚደግፉት ድርጅቶች አባላት አንዱ የሆነው ህወሃታውያንና የመኖር ህልውናቸው በጎሣ ፌደራሊዝም ታማኝነት ላይ የተገነባ ነው:: ኢትዮጵያውያኑ "የጎሣ ፌደራሊዝም" በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲተካ የሚፈልጉ ናቸው:: የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው በእነዚህ ፍላጎቶች መካከል የሚወዛወዝ ነው:: በመንግስት የስልጣን እርከን ውስጥ እራሱን ለማቆም በአንድ በኩል በህወሃት በሌላ ጎኑ አክራሪ ኦሮምኛ ተናጋሪ  ኦነጋውያን ድርጅቶች(OLF)ና አክቲቪስቶች ፈተና የሚሰጠውም  በእነዚህ ምክንያት ነው::

ለ). በጃዋር፣ እዝቅኤልና በቀለ ገርባና በተልዕኮ በፀጋዬ አራርሳ አማካሪነት የሚመራ፣ በህወሃት የሚታገዘው የኢሊሊው ሆቴልን ቤተ መንግቱ ያደረገው "የቄሮ መንግስት" (de facto government )

ይህ "የቄሮ መንግስት" መንግስት ያልሆነ ግን እንደ መንግስት የሚሰራና የሚወስን (non-state actor) ነው:: በጠ/ሚ አብይ መንግስት ውስጥ ያሉ ባለስልጣኖችን፣ የፓሊስና ወታደራዊ አዛዦችን በጎሣ ምንነት ሰርጎ ገብቶ የጠ/ሚ አቢይንና ቲም ለማን(team Lemma) ቡድን የሚያዳክም ነው:: ሕዝብ አዋኪ የጥፋት አጀንዳዎችን የሚነድፍም ነው:: በቀጥታም ለነዚህ ሹመኞች ትዕዛዝ እየሰጠ የአዲስ አበባን ወጣቶች በመንግስት ግልበጣ ሰበብ ዴሞክራሲያዊውን ጎራ ለማዳከም እያሣሰረም ነው:: ቡራዮ እንደታየው ግጭቶችን በመፍጠር ጭፍጨፋን የሚተገብርም ነው:: የዚህ ቡድን ድንጋጤ የተከሰተው በአዲስ አበባ በጳጉሜ 4/2010 ዓ.ም ግንቦት 7ን ለመቀበል ናዝሬት፣ አርባምንጭ፣ ጎንደር፣ ጎጃም፣ ወሎ፣ ሸዋና ድሬዳዋ ሕዝቡ በኢትዮጵያዊነት ደምቆና ገዝፎ መውጣት እረፍት ነስቶታል:: በዋነኛ ከተሞች ውስጥ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ አብላጫ ድምፅ እንደማያገኝ ስለተረዳ ቢችል የከተሞቹን ጎሣዊ ስብጥር ለማዛነፍ የጎሣ አባላቱን ለማስፈርና ግጭቶችን በመቆስቆስ ነዋሪዎቹን  ለቀው የሚወጡበትን የማፈናቀልና የጭፍጨፋ ዕቅድ የሚነድፍም ነው:: በዚህ ዕቅዱም ደስተኛ የሆኑ የኦህዴድ ባለስልጣናትና አባላትም ይተባበሩታል:: እየተባበሩም ነው:: የቡራዮ ገዳዮችን ትተው ግድያውን የተቃወሙ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ያፍሳሉ:: ይህ ኢ-ፍትሃዊ ብቻ ሣይሆን መዘዝ ያለው ግፍ ና ወንጀል ነው::

E). የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው ብቸኛ ምርጫ!

የመንግስት ግልበጣው ከሽፏል ማለት እንደገና አይጠነሰስም ማለት አይደለም:: ሀገር በሁለት መንግስት አትመራም:: 

የጠ/ሚ አብይና ቡድናቸው የተኩት የኢህአዴግን መንግስት እንጂ በመንግስት ውስጥ ያለውን የህወሃት መንግስት አልነበረም:: አሁንም የጠ/ሚ አቢይና ቡድናቸው የኢህአዴግ መንግስት ይሁኑ እንጂ በመንግስት ውስጥ የተሠራ የአክራሪዎቹ የእነጃዋር 'በመንግስት ውስጥ ያለ መንግስት (Deep State)' አለ:: ይህ ለጠ/ሚ አቢይና ቡድናቸው ይሁን ለሐገራችን ኢትዮጵያ የህልውና ችግር ነው:: ይህ የነጃዋር ቡድን ባለስልጣኖችን እያዘዘና እየተጠቀመ በራሱ ወንጀል የህዝብን ልጆች እያሣፈሰ መንግድታቸውን ሕዝብ እንዲጠላው እያረገ ነው:: ከመደመሩ ማዕቀፍ ውስጥ በአስቸኳይ ተቀንሰው ለፍርድ መቅረብና በOMN የሚሰጡትን አፍራሽ ቅስቀሳ ማቆም አለባቸው:: ህወሃት ቆሰለ እንጂ አልሞተም:: ህወሃትን እያከሙ ያሉት እነዚሁ አክራሪዎች ናቸው:: ለእራት እያሰቧችሁ ነውና ቀድማችሁ ቁርስ አድርጉዋቸው:: ህወሃት ሲያገግምም እናንተውኑ ይበላል::

F). የኢትዮጵያንውያን ብቸኛ ምርጫ!

በመንታ መንገድ ላይ ያለች ሐገራችንን ከመፈረካከስ ለማዳን ያለን ብቸኛ ምርጫ በኢትዮጵያዊነት ከኢትዮጵያውያን ጋር በሕብረት መቆም ነው:: ከዳር ሆነን ከምንተች መሃል ገብተን ለመለወጥ በተለይም ይደረጋል የተባለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዳይደናቀፍ መስራት አለብን:

Thursday, August 16, 2018

ለማ መገርሳ እና ፖል ካጋሜ በጨረፍታ (ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ ታዬ)



Lemma Megersa
ሩዋንዳ በምሰራቅ አፍሪካ የምትገኝ ትንሽ አገር ስትሆን በ1994 እንደ አ.አ ከደረሰበት የሁቱና ቱትስ  እልቂት አገግማ ዛሬ ሰላማዊ አገር ሆናለች፡፡ የሩዋንዳ የዘር ፍጅት የሰው ልጅ አረሚያዊ ማነቱን ያሳየበት አንዱ የታሪክ ክስተት ነበር፡፡ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች  ሁቱና ቱትስ በዘውግ ተቧድነው አንድ ሚሊዮን ገደማ የሚደርሱ ዜጎቻቸውን ያጡበት ክስተት ዋናው ምክንያት የዘርን ጥላቻ በሚሰብኩ የፖለቲካ ሊህቃን ምክንያት ነው፡፡
በሩዋንዳ በ1994 ከተፈጸመው የዘር ፍጅት በፊት የሩዋዳ ዜጎች በቋንቋ አንድ ቢሆኑም በብሔር ተከፋፍለው  በዘውግ መታወቂያ ደብተር ላይ ቱትሲ፣ ሁቱ እና ትዋ በሚል የዘር መታወቂያ ካርዶች ልዩነታቸው ገዝፎ ነበር፡፡ ጭካኔ በተሞላበት የዘር ፍጅት መታወቂያቸው ላይ የተጻፈው የብሔር ማንነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡ ከዘር ፍጅቱ በኋላ የፖል ካጋሜ ስልጣን መያዝ ተከትሎ የብሔርና እና የኃይማኖት ማነትን የሚገልጽ ስያሜ በመታወቂያቸው ላይ እንደዳይሰፍር ተደረገ፡፡ ዛሬ በሩዋዳ ውስጥ ቱቲስ እና ሁቱ የሚል መከፋፈል እንደነውር የሚቆጠር ሆኗል፡፡ ዜጎች በችሎታቸው ብቻ የሚለኩበት ስርዓት በመፈጠሩ ፖል ካጋሜ ሀገሪቱን እያዘመናት ይገኛል፡፡
ከሩዋንዳ የዘር ፍጅት ትምህርት የቀሰሙት እንደ ታንዛንያ ያሉ ሀገራት በዜጎቻቸው መታወቂያ ላይ ምንም ዓይነት የኃይማኖትና የብሔረ ማንነትና የሚገልጽ ቃላት እንደይኖሩ በማድረግ ከ120 በላይ ያሉ ብሔሮች በሰላም ለማስተዳደር ችለዋል፡፡
የህወኃት ወራሹ ስርዓት በ1983 ስልጣን ከጋዛ በኋላ የብሔር ጥላቻን የሚፈጥሩ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ፣ በብሔር ስም ህዝቡን በመከፋፈል በርካታ የጎሳ ግጭት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፡፡ ዘረኞች መሰረተ-ቢስ በሆነ ጥላቻና በራስ ወዳድ ማነታቸው ምክንያት ህዝቡን በዘር እያቧደኑ በሚፈጠረው ግጭት የስልጣን እድሚያቸውን ለማራዘም ብዙ ጥረዋል፡፡ ይህም ይሳካላቸው ዘንድ በመታወቂያቸው ላይ የብሔር እና የኃይማኖት ማንነታቸንን በግዴታ ጭነውብን ለ27 ዓመታት ለጎሪጥ ስንተያይ፣ ስንጋጭ፣ ስንጋደል፣ ስንሰደድ ቆይተናል፡፡
ፖል ካጋሜ በሩዋንዳ ላይ ከተፈጠረው እልቂት ተምሮ ከዘር ፍጅቱ በፊት የነበረውን የብሔር ማንነት አጥፍቶ አንድነት የሰፈነባት ሩዋንዳን ሲመሰረት ብልሁ፣ ወጣቱ መሪ ለማ መገርሳ ደግሞ ያንዣበበውን የብሔር ግጭት ተረድቶ የዘር ፍጅቱን በማስቀረት አገሪቱን ከዶ/ር አብይ አህመድ ጋር ሊታደጓት እየታተሩ ነው፡፡
አሁን ለሚታየው የለውጥ ሂደት ጠንሳሽ እና ፊታውራሪ የሆነው የቁርጥ ቀን ኢትዮጵያዊ  ለማ መገርሳ በአገሪቱ ያንዣበበውን አደጋ በመረዳት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ሀገሪቱን እየታደጋት ይገኛል፡፡ ለማ መገርሳ  ከወሰዳቸው በርካታ እርምጃዎች አንዱ የብሔር ማንነትን በዜጎች መታወቂያ ላይ ፍቆ በኢትዮጵያ ዜግነት መተካቱ ነው፡፡የቆራጥ መሪያችንን የለማ መገርሳን አርያን በመከተከል ለሌሎችም የክልል ርእሰ-መስተዳደር ከዜጎቻቸውን መታወቂያ ላይ ከብሔር ማንነት ይልቅ ኢትዮጵያዊነት በማስፈር በአንድነታችን ጉዞ ላይ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የህወኃት ወራሹ ስርዓት ባለሟልና ተቆርቋሪ ነን የሚሉ የሰርኣቱ አጋፋሪዎች ከጎሳ ድርጅት ይልቅ በአስተሳሰብ ልዩነትን ያማከለ የፖለቲካ ድርጅት መሰረት ላይ ማንነታቸውን እንዲገነቡ እና የጎሳ ፖለቲካ እና የብሔር ቡድነኝነት ከአንድነት ይልቅ መለያየትን፣ ከመተማመነን ይልቅ መጠራጠርን ከሰላም ይልቅ ግጭትን፣ ከፍቅረ ይልቅ ጸብን የሚያራግብ እንደሆነ ከበቂው የታሪክ መዛግብት ትምህርት ቢቀስሙ መልካም ነው ፡፡

ኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ጥቅም ለአሁኗና ለወደፊቷ ኢትዮጵያ



ከፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም. 
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ 
“ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን” ብለው አንድነታችንን የሚያጠናክር ንግግር ሲናገሩ የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ጥቅም በሚገባ እንደ ገለጹት ተረድተናል። ቀጥለውም ኢትዮጵያን ከኢትዮጵያ መውሰድ ይቻላል! ነገር ግን ከኢትዮጵያዊ ልብ ኢትዮጵያ ዘላለም አትወጣም ትኖራለች! ብለው የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ጥቅም ደግመው አጉልተውታል። ኢትዮጵያ የጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ በብዙ ጥቁር ሕዝቦች ዘንድ ኢትዮጵያ ልዩ ቦታ አላት። ኢትዮጵያውያን ብዙ ላናውቅና ላንረዳ እንችላለን እንጂ፣ ከኢትዮጵያ ከኢትዮጵያዊነት የኢትዮጵያዊኒዝም አስተሳሰብና ፍልስፍና ተወልዷል።1 ኢትዮጵያኒዝም የተፈጠረው በኃይማኖትና በፖለቲካ ከጭቆና ውስጥ የነበሩ የጥቁር ዘር ባላቸው ሰዎች ነው። አፈጣጠሩ አፍሪቃ ለአፍሪቃኖች ትገባለች የሚለውን የፓናፍሪካ ፍልስፍና አስቀድሞ በመጀመሪያ የገለፀ ነው። ሲጠነሰስ ጀምሮ መንፈሳዊነትን ከሰው ልጆች ነፃነት ጋር አጣምሮ አቀናጅቶ አስተባብሮ የተፈጠረ ፍልስፍና ነው።2 ኢትዮጵያኒዝም በስፋት የተጀመረው 1660 ዓ.ም. ጀምሮ ሲሆን ከ1776 ከአሜሪካ የነፃነት ትግል በኋላ እያየለ መጣ። አፍሪቃ/አሜሪቃኖች በአሜሪካ ነፃነት በተፈጠረው ለቀቅ ያለ ሁኔታ በመጠቀም ኢትዮጵያኒዝምን ፈጠሩ። በ1808 ዓ.ም. የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ቤ/ክ በአሜሪካ አቋቋሙ።3 በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና በዓለም ተስፋፋ። የሚገርመው ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙም የታወቀ ፍልስፍና ሆኖ አልገባም። ትልቁ ጥያቄ አሁን ኢትዮጵያኖች እንዴት ይህን ፍልስፍና ያዩታል? የሚለው ነው። ስለ ሐገሪቱ የወደፊት አቅጣጫ ይጠቅማል ብለው ይሄን ፍልስፍና መመርመርና መወያየት ቢችሉ ጥሩ ነው የሚል አስተያየት አለን። እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ቀላል የምንቆጥረው ኢትዮጵያዊነት በኢትዮጵያኒዝም መልክ በሌሎች ሕዝቦች ዘንድ ያለውን አዎንታዊ ተጽእኖ ብንረዳው የበለጠ ኢትዮጵያዊነታችንን ለማጠናከር ሊረዳንም ይችል ነበር።4 የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍናን ያስፋፉት እነማን ናቸው? ኢትዮጵያኒዝምን በመጀመሪያ ያስፋፉት በ19ኛው ክፍለ ዘመን በመንፈሳዊ ዓለም የተሰማሩት በአሜሪካና በደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ቄሶች ናቸው። በመሠረቱ ዘረኝነት በፖለቲካና በኢኮኖሚ ዓለማዊ ዙሪያ ላይ ብቻ ሳይሆን በጥቁሮች መንፈሳዊ ዓለም ላይም ከባድ ጫና ነበረው። በሃይማኖት ሳይቀር ጥቁርን እንደ ሰይጣን ነጭን እነደ መልዓክ ማየት የተለመደ የነጭ ቄሶች እምነትና ተግባር ነበር። ገጽ 2 የ8 በመሠረቱ ነፃነት የሚፈልጉ የጥቁር ቄሶች ሁለት ችግሮች ገጠሟቸው፤ የነጭ ቄሶች ሲሰብኩ ጥቁርን እንደ ሉሲፈር (ሰይጣን) ስለሚቆጥሩ የነሱ ቄስ ሆኖ ማገልገል በራሳቸው በጥቁሮች ላይ መንፈሳዊ ኩነናን እንደ መቀበል መስሎ ስለ ታያቸው መቀበል አልዋጥላቸው አለ። በሁለተኛ ደረጃ የነጭ ቄሶች ለጥቁር ቄሶች ምንም ቢሆን ያመራር ተግባር እንዳያገኙ ከለከሏቸው። ሌላው በጣም ያማረራቸው ደግሞ የነጭ ቄሶች ሲሰብኩ የጥቁር ቄሶች ቀና ብለው ወደ ላይ አምላክን ከማየት ወደ ታች አንገታቸውን ደፍተው ቁልቁል እንዲያዩ አምላክን አሻቅበው እንዳያዩ የነጭ ቄሶች እንዳገዷቸው እንደሳፈሯቸውና እንደ ጨቆኗቸው ይናገራሉ። ጭቆናው እየቀጠለ በሄደ ቁጥር ነጮች በሚቆጣጠሯቸው ቤተክርስቲያን መቀጠል እንዳንገፈገፋቸው ይናገራሉ። በአንድ በኩል ቤተክ/ያን እንዲቀይሩ ጥያቄ ያቀርባሉ፤ ካልተቀየረ ግን ሌላ ቤተክ/ ለማቋቋም አቋም ይወስዳሉ። ያቀረቡት ጥያቄ ሙሉ የመንፈሳዊ ነፃነት ማግኘት እንደ ምዕመናን ወደ እግዚአብሔርና ወደ ክርስቶስ ካላንዳች ዘረኝነትና አድልዎ የሚያገናኝ ሃይማኖትና ቤተክ/ ፈለጉ። የነጮች ቤተክ/ ይህንን ጥያቄያቸውን ሊያሟሉ አልቻሉም፤ ስለዚህ አዲስ ቤተክ/ ማቋቋም ወይም የነበረውን ቤተክ/ መቀየር ፈለጉ፤ እናም በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ስለ ሆነች የኢትዮጵያ ቤተክ/ እያሉ ማቋቋም ፈለጉ። ኢትዮጵያ የጥቁር ሐገር በመሆኗ ሌላው ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ስለሚል ያለምንም መድልዎና ዘረኝነት ወደ እግዚአብሔር እምታገናኘን ቤተክ/ ናት ብለው ኢትዮጵያኒዝምን አቋቋሙ።5 ኢትዮጵያኒዝምን ያዩት እንደ መንፈሳዊ ጎዳና ከእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር በቀጥታ መንገድ ከፋች፤ ሌላው ደግሞ ኢትዮጵያ የጥቁር ሐገር ሆና እራሷን ማስተዳደር የቻለች ታላቅና ክቡር እንዲሁም የራሳችው ሐገርና እንደ አለኝታ በመቁጠር ነበር የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና በመንፈሳዊ ትግል የጀመሩት፤ ያነፁትና የገነቡት።6 የሚገርመው የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና መንፈሳዊ መሠረት ይኑረው እንጂ ለተጨቆኑት የዓለም ሰዎች ሁሉም መመሪያ አድርገው ነው የመሠቱት። ከመንፈሳዊ መሠረቱ ወደ ዓለማዊ ጭቆናዎችን ለመቋቋም የኢትዮጵያኒዝም የሚከተሉትን ስምንት ባሕሪያት ያጠቃልላል፤ 1. መንፈሳዊ ነፃነት 2. በራስ መተማመን 3. ለራስ ክብር 4. እራስን መቻል 5. የውጭ ጭቆናን መቋቋም 6. መንፈሳዊ ነፃነት ከዓለማዊ ነፃነት ጋር ማጋራት አብሮ እንዲሔድ ማድረግ 7. የተጨቆኑ ሰዎች በጋራ መተባበር 8. ሰብአዊነት፣ መረዳዳትና እርስበርስ መተሳሰብ። እነዚህ ስምንት ታላላቅ ፅንሰ ሀሳቦች የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና የሚያራምዱና በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያኒዝምን ተከትሎ የመጣውን ፓንኣፍሪካኒዝምን ለአፍሪቃ ነፃነት አንድነት ሕድስና ስር መሠረት የሰጡ ታላቅ አስተዋጽኦ ያደረጉ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸው። የኢትዮጵያ ነፃነትም ጠቅሟል።7 ገጽ 3 የ8 እንግዲህ ኢትዮጵያኒዝም በ16ኛው ክፍለ ዘመን ተጀምሮ 18ኛው ክፍለ ዘመንን ተደግፎ እሰከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ የቆየ ፍልስፍና ነው።8 ኣሁንም ቢሆን የቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝዳንት ታቦይ ኢምቤኪ እንደሚሉት የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና አሁን ላለንበት ዘመን ያስፈልጋል ይላሉ።9 እናም የኢትዮጵያ ቤተክርስትያኖችም በደቡብ አፍሪቃ በአሜሪካና በካሪቢያን ሀገሮች አሉ፤ አሁንም ቢሆን እነዚህ ቤተክርስትያኖች ከመንፈሳዊ አገልግሎት በተጨመማሪ ያላለቀውን የነፃነት ትግል የገለፁ ናቸው። ኢትዮጵያኒዝም በዓለም መድረክ ያመጣቸው ለውጦች በደቡብ አፍሪቃ የአፍሪቃን ናሽናል ኮንግሬስ ያቋቋሙት በደቡብ አፍሪቃ የኢትዮጵያ ቤተክ/ ቄሶች ናቸው፤ እናም የመጀመሪያው የአፍሪቃ ናሽናል ኮንግሬስ ፕሬዝዳንት ጆን ላንጋቢሌሌ ዱቤ በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍናቸውና አቋማችው ታስረው ከተፈቱ በኋላ የአፍሪቃ ናሽናል ኮንግሬስ ፕሬዝዳንት ሆነዋል።10 የስማቸው ቅፅል ግልፅ ኢትዮጵያዊ ሁልጊዜ አደጋ ላይ ያሉ ይሏቸው ነበር፤ እናም ነጮቹ 1906 የኢትዮጵያኒዝምን ፕሮፖጋንዳ አንቋሽሸው ኢትዮጵያኒስትን ማሰርና አልፎ አልፎም መግደል ጀመሩ። ቀጥለውም የኢትዮጵያኒዝም እንቅስቃሴን እንደ አደጋና እንደ ረብሻ አሰራጭ ቆጥረው የወታደር ኃይላቸውን አሳደጉ። የዙሉ እንቅስቃሴ 1906 ቀጥሎም ባንባታ በሌሎችም አካባቢዎች ያፓርታይድ ተቃውሞ እንቅስቃሴ ተጀመረ። እንቅስቃሴውውንም ያስጀመሩት እንዲሁም ይመሩት የነበሩት ኢትዮጵያኒዝሞች ነበሩ። እንዲሁም በተለያዩ የአፍሪቃ ሐገሮች በእንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ፖርቱጋል፣ በቅኝ ግዛት ተገዝተው የነበሩ በኢትዮጵያኒዝም በመጠቀም ሃይማኖትን ከፖለቲካ ጋር በማገናኘት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት ተጠቅመውበታል። ራስተፈሪያኒዝንም የፈለቀው ኢትዮጵያኒዝም በሚለው ፍልስፍና ነው። አፍሪቃ ለአፍሪቃዊያን የሚለው አስተሳስብ የመጣው ኢትዮጵያኒዝም በሚለው ፍልስፍና ነው። ቅኝ ግዛትን በመቃወም እነፕሬዝዳንት ጆሞ ኬኒያታ ሳይቀሩ በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና እሰከ 1960 ዓ.ም ድረስ ተጠቅመውበታል። በተለያየ መንገድ ቢገለፅም የተለያዩ ሰዎች በተለያየ መንገድ ቢጠቀሙበትም መሠረታቸው ኢትዮጵያኒዝም እንደ ሆነና አፍሪቃን ሙሉ ከቅኝ ግዛት ለማውጣት እንደ ችቦ መብራት እነደ ተጠቀሙብት ጥርጥር የለውም። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያኒዝም የኢትዮጵያ ሚና በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ምንድነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። በመጀመሪያ ኢትዮጵያን የኢትዮጵያኒዝም መሠረት አድርጎ ሲፀነስ ሐገሪቷ ልዩ ቦታ እንደ ተሰጣት ምንም ጥርጥር የለውም። በመሆኑም ኢትዮጵያ መንፈሳዊ ምግብ ለዓለም የሰጠች መሆኑ ምንም የሚያሻማ ነገር የለውም። ዛሬ ቁሳቁሳዊ እርዳታ ከሚሰጡት እንደ አሜሪካ ካሉ ሀገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ መንፈሳዊ የነፃነት ምግብ ለዓለም የሰጠች ታለቅ ሐገር መሆኗ ጥርጥር የለውም። እንግዲህ ኢትዮጵያን ሊጎዷትና ሊገድሏት ያሰቡ ሐገሮች ግለሰቦች እንዲሁም ቡድኖች ማወቅ የሚገቧቸው ነገሮች ቢከሷትም በታሪኳ ቢፈርዱም ብትሞትም ዘላለም የምትኖር ሐገር ናት። ሁላችንም ቢሆን ይህችን ሀገር እንዲህ ያለ የተጨቆነውን ዓለም በሙሉ ያከበረውን መንፈሳዊ ስጦታ ያበረከተች ሐገር አሳልፈው የሰጡንን አባቶቻችንና እናቶቻችንን ማክበር እንጂ በውጭ ገጽ 4 የ8 ሐገር ፕሮፖጋንዳና በማናውቀው ሥልጣኔ ባልገባንና ባልተረዳነው ተውጠን ይህችን ሐገር መናቅ ትልቅ ስሕትተ ነው። በተጨማሪም ኢትዮጵያኒዝም የተመሠረተው በክርስትና ሃይማኖት ላይ የነጭ ቄሶች ዘረኝነትን በማስፋፋት የእግዚአብሔርን መልክ በነጭ ቅልፅ በመግለፅ ሌሎችን በማግለልና መጠቀሚያ ብቻ በማድረግ እንደማይቻል በመቃወም ነበር። የእስልምና ሃይማኖትን በኢትዮጵያኒዝም አመለካከት ስናየው ተቃውሞ በተነሳበት ጊዜና ምዕመናኑ ስደት ባጋጠማቸው ወቅት የኢትዮጵያ ድጋፍ ትልቅ ልዩነት እንዳመጣ ታሪክ ይመሰክራል።11 ኢትዮጵያ ለሙስሊሞች ያደረገችው ድጋፍ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ይገልፃል። ከእኛ ምን ይጠበቃል? በመጀመሪያ ይህንን ታሪክና ፍልስፍና ማወቅ ይገባናል። ይህንን ታሪክና ፍልስፍናን መሰረት አድርገን ዘመናዊነትን ለመገንባት ዝግጁ መሆን ያሰፈልጋል። ከውጭ የተለያዩ ሀሳቦችን እየኮረጅን ሐገራችን የፈጠረችውን ፍልስፍና ማንቋሸሽና ታሪኳን መወንጀል አላግባብ መፍረድ አይገባም። መጠየቅ ያለብን የራሳችን ሐገር ምን ፈጠረች፣ ለምን በዓለም ዙሪያ ያሉ ሐገሮች እንደዚህ ተማሩባት አከበሯት ብለን በትሕትና ሐገራችንን አክብረን ያለባትን የተወሳሰቡ ችግሮችን አጥንተን ተወያይተን ተባብረን አንድ መንገድ ፈጥረን በሐገሪቷ ባህል መሰረት ካላንዳች ኩረጃ ታላቋን ኢትዮጵያ መፍጠር እንችላለን። መደምደሚያ ሃሳብ የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ለአዲስ ብሔራዊ ውይይት አሁን አዲስ የብሔራዊ ውይይት ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል። ስለ ሐገራችን ነባራዊ ሁኔታ በሰለጠነ አስተሳሰብ መወያየትና ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል። ለውጥ መጣ በተባለበት ዘመን ማለትም ባለፉት ዓርባ አመታት ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ የውይይት መድረክ ነበር ማለት ያስቸግራል። ከእንግዲህ ወዲህ ግን ይህ የብሔራዊ ውይይት መድረክ መፈጠር አለበት። ኢትዮጵያ የት ነው ያለችው፣ ወደ የት ነው ምትሔደው? ያለችበት ጎዳና ትክክል ነው ወይስ አይደለም በሚሉ ሀሳቦች ላይ በጋራ በመወያየት ስምምነት ላይ በመድረስ በኢትዮጵያኒዝም በመጠቀም አሁን ሐገራችን ካለችበት ውስብስብ ችግር መውጣት እንችላለን። ባጠቃላይ ከእንግዲህ ወዲህ ለውይይት የሚጠቅሙን ኢትዮጵያ በንፅህናዋ የተበጀውን ፣ በመንፈሳዊ ኃይል የተመራውን የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ተጠቅመን ትልቅ እንደ ነበረች እንደ ገና ትልቅ ለማድረግ ተሳስበን ተደማምጠን በታላቅ ትሕትና በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንገንባት። ሁሉ ነገር ከሃገራችን ስለ ተፈጠረ ለሌሎች ምሳሌ ስለ ሆንን ሃገራችን ወደ ፊት እንድትሄድ ጠንክረን እንሥራ። ከእርስዎ አመራር ምን ይጠበቃል? ገጽ 5 የ8 ሌሎች ሃገራት በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ተጠቅመው ነጻ የወጡና ሃገራቸውን ወደ ተሻለ መንገድ የመሩት በእኛ ኢትዮጵያዊነት ጥንካሬ እና የደረሱብንን የተለያዩ ተግዳሮቶች ተቋቁመን በነፃነት መኖር በመቻላችን ነው። አሁን ሃገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ስንመለከት በዘር፤ በኃይማኖት እና በጎሳ ተከፋፍሎ ሕዝቡን በቋንቋ እና በክልል አዋቅሮ በመግዛት፤ ከኢትዮጵያዊነት በፊት ለጎሳ ቅድሚያ እንዲሰጥ፣ በሥራ ምክንያት ከቦታ ወደ ቦታ በነፃነት እንዳይንቀሳቀስና ሥራ እንዳይሠራ አድርጓል። ሕገ መንግሥቱ በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን በክልል መንግሥት አደረጃጀት የተመሠረተ ስለሆነ ሕዝቡ ከሃገሩ ይልቅ ቅድሚያ ለብሔሩ እና ለክልሉ እንዲሰጥ አድርጎታል። ይህ የክልል አደረጃጀት እስካልተስተካከለ ድረስ አሁን ሃገራችን ከገባችበት ውጥንቅጥ ችግር ውስጥ መውጣት አትችልም። ሃገራችን ከገባችበት ዘርፈ ብዙና ውስብስብ ችግር ልትወጣ የምትችለው የክልል አወቃቀር ተስተካክሎ ዜጋው ከቦታ ወደ ቦታ በነፃነት የመዘዋወር፤ የመሥራት፣ የመማርና የመኖር መብቱ ተጠብቆ ሊያስኬድ የሚቻለው ለኢትዮጵያዊነት ቅድሚያ የሚሰጥ ሕገ መንግሥት ሲኖር እንደሆነ እሙን ነውና ሕገ መንግሥቱ መሻሻያ ቢደረግበትና ቢስተካከል ለሃገራችን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት ይቻላል። ሃገራችን ኢትዮጵያ ለውጪው ዓለም በተለይም ለተጨቆኑ ሕዝቦች ራሷ ተቸግራ እና የደም ዋጋ በመገበር የሰጠችው መንፈሳዊ ፀጋ ቀላል የሚባል አይደለም፣ ከራሷ አልፋ ለተጨቆኑ ሕዝቦች ሁሉ ምሳሌ እና አርዓያ የሆነች ሕገራችንን ችግሮቿን እና እንከኖቿን እኛ ልጆቿ በሰለጠነ እና በሰከነ መንገድ በመነጋገር በመደማመጥና በመከባበር ልንፈታና አሁን ካለችበት ወደ ተሻለች ኢትዮጵያ ልናሸጋግራት ይገባል። የሃገራችን የትኛውም ዓይነት ችግር መፈታት ያለበት በራሷ ልጆች መሆን አለበት! በፖለቲካ አመለካከት እና አመከንዮ ባንግባባም እንኳ ለሃገራችን እና ለሕዝቧ ቅድሚያ በመስጠት ወደ መፍትሔ መንገድ መምጣት እንችላለን። እርስዎ የጀመሩት ኢትዮጵያዊነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በአራቱ አቅጣጫ አስተጋብቷል! ሕዝቡም ሲናፍቀው የነበረ ዓቢይ ጉዳይ ነውና ተቀባይነትዎ ጨምሯል! ይጨምራልም። አሁን የተጀመረውን ኢትዮጵያዊነት መነቃቃት ወደ ተሻለ እና ከፍ ወደሚል ደረጃ ለማድረስ እርስዎ ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነቱን መወጣት እና አሁን ካለንበት የብሔር እና የሃይማኖት ችግር ወጥተን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሃገሩ ተከብሮ የሚኖርበትን ዕድል ለመፍጠር ሁላችንም በጋራ የምንሠራበት ዕድል መፈጠር ይኖርበታል። አሁን ከሚታየው ተስፋ እና ጅማሮ በመነሳት ሃገራችን ወደ ቀድሞ ክብር እና ዝናዋ የምትመለስበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም። በእርስዎ አመራር የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባሮች እንዲከናወኑ በትሕትና እናመለክታለን፤ 1ኛ/ የኢትዮጵያኒዝም መንፈስ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪቃና በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ፤ እንዲዘረጋና እንዲዳብር ማድረግ፤ 2ኛ/ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ሙሉ መሻሻል እንዲያስገኝ መለወጥ ከሚገባቸው ብዙ ጉዳዮች አንዳንዶቹን እንጠቁማለን፤ ገጽ 6 የ8 የክልል አስተዳደር ኢጣልያኖች ኢትዮጵውያንን መግዛት የሚቻለው በመከፋፈል ነው በማለት የዘረጉት አስቀያሚ ሥልት ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ መላቀቅ አለባት። በዘር፤ በኃይማኖት፤ በቋንቋ የኢትዮጵያን ሕዝብ መከፋፈል እንደ ሀጢአት የሚቆጠር በመሆኑ ሐገራችን በክፍለ፟ ሐገር እንድትደራጅ ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር የሃገራችንን ረጅም ታሪክ፤ ጥበብና ዕውቀት በሚያጎላ መንፈስ እንዲስፋፋ ይሁን። በተለይ ሰንደቅ ዓላማው ኣረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ቀለማት ብቻ የሚታይበት ሆኖ መንግሥት በተቀየረ ቁጥር ሊለዋወጥ አይገባም። በአፍሪቃ አፍሪቃውያን የፈጠሩት ፊደል ግዕዝ ብቻ ነው። ስለዚህ በዚህ ታሪካዊ ፊደል መጠቀም ሲገባን በሌሎች ባእድ ቋንቋዎች ፊደሎች ለምሳሌ በላቲን መጠቀም ተገቢ አይደለም።12, 13 ከኢትዮጵያ አካባቢ እንደዚሁም የመላ አፍሪቃ አንድነት በጣም አስፈላጊ ነው። በእዚህ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያ ልዩ ሚና እንዳላት መገንዘብ ያስፈልጋል። ይኸውም በዓለም ሕዝብ ከ1829 እስከ 1929 ድረስ የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ጊዜ የነበረ መሆኑ በዓለም ተሰራጭቷል። በኢትዮጵያ ስም ሁለት ማኒፌስቶዎች (መመሪያዎች) በ1829 ዓ.ም. በአሜሪካ፤ በ1896 በደቡብ አፍሪቃ፤ ከአድዋ ጦርነት ድል በኋላ ተሰራጭተዋል። አፍሪቃ በሙሉ በኢትዮጵያ ስም የሚታወቅበት ጊዜም እንደ ነበረ ማስተዋል ይገባል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ያከናወነችውን አሁንም እንድትቀጥልበት ያስፈልጋል። ይህም ታሪካዊ መሠረታችን ነው። ከእዚህ ቀደም የነበረው የእርስ በርስ መፈራረጅ፤ የመለያየትና ችግር ሲያጋጥም ወደ ጦርነት ከማዘንበልና በውጭ ሃገሮች መሣሪያ ከመጠቀም፤ ወደ መወያየት፤ መግባባትና መመካከር ባሕል መለወጥ ይጠቅማል። የኢትዮጵያን ችግር በኢትዮጵያውያን መፍትሔ ማስወገድ ይገባል። በውጭ እጅ ላይ መተማመን መክፋፈል ያስከትላል። የመንግሥቱ አወቃቀር ግልጥነት፤ የወስጥ ቁጥጥር፤ ውጤታማነት የሚያሰፍን ሊሆን ይገባዋል። የመንግሥት ሠራተኞችና ባለሥልጣኖችም ሊመደቡ የሚገባው በተገቢ መስፈርት ብቁነታቸው ብቻ ሳይሆን ተደጋጋሚ ሥልጠናም እየተከናወነላቸው በቂ ቅልጥፍናና ከሙስና የተላቀቀ አገልግሎት እንዲያበረክቱ ማድረግ ያስፈልጋል። የበላይ አመራሩ የጊዜ ገደብ ይወሰን። 3ኛ/ ኢትዮጵያ ካለችበት ቀውጢ ጊዜ ተላቅቃ አስተማማኝ ወደ ሆነ ጎዳና እንድትገባ ሁሉም ማለት የፖለቲካ፤ የማሕበረ ሰብዓዊ፤ የመንፈሳዊ፤ ወዘተ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የሽግግር ሒደት ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ። የእርስዎንም የአስተዳደር ዘመን እስክ መጨረሻው ለሃገር የሚበጅ ውጤታማ እንዲሆን እንመኛለን። ኣገርን በጎሳ መከፋፈል ኢትዮጵያን ሰማንያ ቦታ መከፋፈል ነው። በኢትዮጵያዊነቱ ተከባብሮ መኖር የማይችል ሕዝብ በየቤተሰቡ መንግሥት ፈጥሮ መኖር ኣይችልም። ለኣፍሪቃውያን መከታና ኣለኝታ ሆኖ የቆየው ኢትዮጵያዊነት ኣፍሪቃ ኣንድ ኣገር ሆና መብቷ በዓለም ደረጃ እስኪመለስ ከመንደርና ጎሳ ኣስተሳሰብ መላቀቅ ይገባናል። ከታላቅ አክብሮት ጋር! እግዚአብሔር ሃገራችንን ይባርክ!! 
1 ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ 
2 ፕሮፌሰር ሲሳይ አሰፋ 
3 ፕሮፌሰር ብርሃኑ መንግስቱ 
4 ፕሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦ 
5 ዶ/ር ኣበራ ሞላ 
6 ዶ/ር ወርቁ አበራ 
7 ዶ/ር ጌታቸው ተመስገን ገጽ 7 የ8 
8 ዶ/ር አበባ ደግፌ 
9 ዶ/ር እጀቡሽ አርጋው 
10 ወ/ሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታ
11 የተከበሩ የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ ግርማ ሰይፉ 
12 አቶ ምንተስኖት መንገሻ  አቶ ሰይፉ ኣዳነች ብሻው
13 አቶ በትሩ ገብረ እግዚአብሄር  አቶ ኪዳኔ አለማየሁ
14 አቶ እርቅርማሪያም ደረስ  አቶ ተፈራወርቅ አሰፋ  አቶ ይልማ ዘሪሁን  አቶ ይርጋለም ጎበዜ 
15 አቶ ከድር ሰይድ  አቶ መሸሻ ካሳ 
16 አቶ ኤሊያስ ማሞ 
17 አቶ ብርሃኑ ገመቹ 
18 ወ/ሮ አስቴር ኃይሌ 
19 አቶ በቀለ ተገኝ 
20 አቶ አብርሃም ቀጀላ 
21 አቶ ግርማ ካሳ 
ዋቢ 1. Ethiopianism, http://www.druglibrary.net/olsen/RASTAFARI/campbell.html
2. ETHIOPIANISM IN PAN-AFRICAN PERSPECTIVE, 1880-1920, https://www.upjournals.co.za/index.php/SHE/article/view/85
3. Abyssinian Baptist Church, New York City (1808- ) http://www.blackpast.org/aah/abyssinian-baptist-church-1808
4. Ethiopianism in African Christianity, https://repository.up.ac.za/bitstream/handle/2263/21579/011_Chapter10_p258- 277.pdf?sequence=12 5. Ethiopianism and African Nationalism in South Africa before 1937, https://www.persee.fr/doc/cea_0008-0055_1986_num_26_104_1689
6. Ethiopianism, http://www.blackpast.org/gah/ethiopianism
 7. Ethiopianism and the Independent Church Movement, http://www.worldhistory.biz/sundries/4707
8-ethiopianism-and-the-independent-churchmovement.html 8. Ethiopianism, https://www.britannica.com/topic/Ethiopianism
9. Ethiopianism a symbol of resistance to injustice, http://www.aau.edu.et/blog/ethiopianism-a-symbol-of-resistance-to-injustice-thabo-mbeki/
10. John Dube, http://www.anc.org.za/content/john-dube ገጽ 8 የ8
11. Ethiopian Muslims History, http://www.selamta.net/ethiopian%20muslims%20history.htm
12. http://www.ethiomedia.com/1000dir/oromigna-be-amara-kilil-be-geez-fiddelendiset.pdf
 13. http://www.ethiomedia.com/1000dir/open-letter-to-president-lemma-megersa.pdf8

ክስተቱ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮችን አስቆጥቷል



ዋዜማ ራዲዮ- የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የሕዳሴው ግድቡ ዉሀ የሚተኛበትን ሰፊ ቦታ ከደን ነጻ እንዲያደርግ 2 ቢሊዮን ብር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን የተሰጠው ከዓመታት በፊት ነበር፡፡ አሁን ግን ገንዘቡ ሳይባክንብኝ አልቀረም እያለ ነው፡፡ ይህ ገንዘብ የተከፈለው ከመንግሥት አሠራር ውጭ ፣ ያለምንም መደበኛ ውል፣ ሥራው ተሠርቶ እንደተፈጸመ ተደርጎ መቶ እጅ ክፍያን በመፈጸም ነው፡፡
ሜቴክ ገንዘቡን ከተቀበለ በኋላ ግን ሥራው መስተጓጎል ገጥሞታል፡፡ ገንዘቡን ጠፍቶበታል፡፡
ፕሮጀክቱ የሚጠይቀው የሰው ኃይል እጅግ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ ሁኔታ መሠራት ቢኖርበትም ሜቴክ በወቅቱ ያዘጋጀውን ጨረታ በመሰረዝ የቀድሞው የሕወሓት ታጋዮች መቋቋሚያ እንዲሆናቸው በሚል ሥራውን ያለጨረታ አሳልፎ ሰጥቷቸው ነበር፡፡
ኾኖም ነባር ታጋዮች ለተሰጠው እድል አመስግነው ሥራውን በወቅቱ የተረከቡ ቢሆንም የስራውን ስፋት ከግምት በማስገባት ለሌላ ሦስተኛ አካል ‹‹ሰብ ኮንትራት›› መስጠት እንዳለባቸው ከስምምነት ደርሰው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት በግምት ከአዲስ አበባ እስከ ዝዋይ ያክላል የሚባለውን ይህን ሰፊ በደን የተሸፈነ ቦታ መመንጠር የሚችሉ በሺ ለሚቆጠሩ የተደራጁ ወጣቶች ሥራውን በስምምነት አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ስምምነቱም ወጣቶቹ እንዴትም ብለው ምንጠራውን በብቃት እንዲወጡና ክፍያ ሲፈጸም ግን ሰባ በመቶውን ለነባር ታጋዮች እንዲያካፍሉ የሚል ነው፡፡
ይህን ስምምነት ተከትሎ በሺ የሚቆጠሩና ራሳቸውን በ72 ማኅበራት ያደራጁ ወጣቶች ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘምተው ነበር፡፡ መቶ ሚሊዮን ብር ለሥራ ማስኬጃ ቅድመ ክፍያ የተቀበሉት እነዚህ ወጣቶቹ በከፍተኛ ሞራልና ተስፋ ወደ ስፍራው በመዝመት፣ ከአጎራባች አካባቢዎችና በተለይም ከጎጃም የጉልበት ሠራተኞችን በገፍ በመመልመል የዛፍ ቆረጣውን ሥራ ጀምረውት ነበር፡፡
‹‹በባህላዊ መንገድ ዛፎቹን መመንጠር የጀመርነው ዘመናዊ መጋዞች ከአየር ንብረቱ ጋር ስላልተጣጣሙልን ነው›› ይላል በዚህ ሥራ ተሠማርተው ከነበሩ ማኅበራት የአንዱ አስተናባሪ ለዋዜማ ሲናገር፡፡ ‹‹እውነት ለመናገር የገንዘቡን ትልቅነት እንጂ የሥራው ስፋት ሳንረዳ ነበር የገባንበት›› የሚለው ይኸው ወጣት በእድሜ ልክ የማያገኙትን ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ውሎና አዳራችንን ጫካ ውስጥ በቀለሷቸው ድንኳኖች ለማድረግ ተገደው እንደነበር ያስታውሳል፡፡
1500 ኪሎ ሜትር እስኩዌር እንደሚሸፍን የሚነገረው ይህ ደን ግድቡ ካለበት ወደ ኃላ በትንሹ 200 ኪሎ ሜትር ይሸሻል፡፡
በስድስት ወራት ብቻ 56ሺ ሄክታር ደን ጨፍጭፈን ከጨረስን በኃላ በስምምነታችን መሠረት ሁለተኛ ዙር ክፍያ ስንጠይቅ ‹‹አትቸኩሉ›› ተባልን የሚለው ይህ ወጣት የመጀመርያ ክፍያውን በዋናነት ለቁሳቁስ መግዣና ለዕለት ቀለብ ስላዋልነው ሁለተኛውን ክፍያ በጉጉት ለመጠበቅ ተገደን ነበር ይላል፡፡
‹‹ቀላል ሥራ አልነበረም፡፡ 12ሺ የጉልበት ሠራተኞች ተሳትፈውበታል፡፡ ዛፎችን ለመገንደስ ትልልቅ መጋዞች ሊቋቋሙት ባለመቻላቸው በሺ የሚቆጠሩ መጥረቢያዎች ከተገዙ በኋላ በሰው ጉልበት ነበር ሥራው ያሠራነው፡፡ 12ሺ የጉልበት ሠራተኞች ቁርስ ምሳና እራት እንዲሁም የበረሀ ድንኳን ማቅረብ፣ ሕክምናና ሌሎች ፋሲሊቲዎችን መስጠት የኛ ድርሻ ነበር፡፡ በዚህ አስቸጋሪ ሂደት ሰዎች ሞተውብናል፤ እባብ የነደፋቸው የጉልበት ሠራተኞች፣ ወንዝ የወሰዳቸው ዛፍ ቆራጮች አሉ፡፡›› ሲል ፈተናው እንዴት አስቸጋሪ እንደነበር ለዋዜማ ተናግሯል፡፡
ቃል የተገባልን ክፍያ በጣም ሲዘገይብን ግን እኛን ከቀጠሩን ታጋዮች ጋር ሆነን ከፍተኛ ባለሥልጣናትን በደብዳቤና በአካል መጠየቅ ጀመርን ሲል ሂደቱን ያስረዳል፡፡
‹‹በመጨረሻም ከጄኔራል ክንፈ ጋር ቀጠሮ ተይዞልን መነጋገር ስንጀምር ገንዘቡ ለሌላ አጣዳፊ ነገር ውሎ ሊሆን ስለሚችል ያንን እስካጣራ እናንተ ሥራችሁን ቀጥሉ እንዳሏቸው ይናገራል፡፡ ሥራችንን ምን ይዘን እንደምንቀጥል አልገባንም ነበር ይላል፡፡
ከዚያ በኋላ በነበሩ ተከታታይ ስብሰባዎች ግን ነገሮች እየተበላሹ እንደመጡና ነባር ታጋዮችና ጄኔራሉ ሊግባቡ አለመቻላቸውን ያብራራል፡፡
‹‹ለዚህ ሥራ ተብሎ 2 ቢሊዮን ብር ለሜቴክ እንደተከፈለው እናውቅ ነበር፤ ብሩ ግን ሳይባክንባቸው እንዳልቀረም›› የሚለው ይኸው ወጣት ‹‹ምክንያቱም የሜቴክ ሰዎች ሲነግሩን ብሩ እኮ የለም፣ ከየት ነው የሚከፈላችሁ? ይሉን ነበር፤ እኛ ግን አላመናቸውም ነበር›› ይላል፡፡
‹‹እንዲህ አይነት ትልቅ ብር ባከነ ሲባል ለማመን አስቸጋሪ ነበር››
ነገሮች እየተካረሩ እንደመጡ ሲያስረዳም፣ ‹‹እኔ ማኅበሩን በመወከል አልፎ አልፎ ስብሰባዎቹ ላይ እገኝ ነበር፡፡ በትግርኛ ኃይለቃል ሲለዋወጡ እንሰማለን፡፡ በተለይም በአንድ ወቅት የጄኔራሉ የቅርብ ቤተሰብ ነው የሚባል የቀድሞ ታጋይ ‹‹የዕድል ጉዳይ ሆኖ ነው አንተ እዚህ ወንበር ላይ፣ እኔ ዊልቸር ላይ የተመጥነው›› ብሏቸው ስብሰባ ረግጦ እንደወጣ አልተመለሰም ይላል፡፡
ጄኔራሉም ከዚያ በኋላ ስሜታዊ በመሆን ‹‹ይሄ አገራዊ ፕሮጀክት ነው፣ ገንዘብ ገንዘብ አትበሉ፤ እኛ ጨረታ ማውጣት አቅቶን አይደለም፤ እናንተን እናግዝ ብለን ነው የሰጠናችሁ›› ሲሉ መናገራቸውን ያብራራል፡፡
በጄኔራሉ ተስፋ የቆረጡት ታጋዮች ፖስታ ቤት ቅጥር ግቢ ወደሚገኘው የዶክተር ደብረጽዮን ቢሮ በቀጥታ በመግባት መፍትሄ እንዲፈልጉላቸው ጠይቀዋቸው ‹‹ክንፈን አናግሬው እኔ ራሴ መልስ ይዤላችሁ እመጣለሁ፣ በጭራሽ አታስቡ›› ብለው በእርግጠኝነት መልሰዋቸው ነበር ይላል፡፡ ሆኖም ዶክተሩ ቃላቸውን ባለመጠበቃቸው የኛ ተወካዮች አቶ አስመላሽ ጋር በመሄድ እንዲያሸማግሏቸው ተማጽነው ይህም ውጤት ሳያስገኝ ቀርቷል፡፡
ይህን የሰሙት ጄኔራሉ የኛን ተወካዮቹን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠርተው፣ ‹‹ስማችንን በየቢሮው እየሄዳችሁ ታጠፋላችሁ፣ ነገሩን በእልህ ለመጨረስ ካሰባችሁ እኛ እንብሳለን›› በማለት እንዳስፈራሯቸው ይናገራል፡፡
ከዚህ የተራዘመ ሂደት በኋላ ብዙዎቹ ተስፋ ቆርጠው ነገሩን እርግፍ አድርገው የተዉ ሲሆን 12 የሚሆኑ ማኅበራት ግን እውቅ ጠበቆችን በመያዝ ፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸውን ይኸው ወጣት ይናገራል፡፡ ሌሎች ማኅበራት መክሰስ ያልፈለጉት በሌላ ሳይሆን ፍርሃት ስላደረባቸው ነው ይላል፡፡ ‹‹ሜቴክን ከሰን የት እንደርሳለን›› ያሉ ነበሩ፡፡ የመጣው ይምጣ ብለው የከሰሱም ነበሩ ይላል፡፡
ወደ ፍርድ ቤት ከሄዱት ማኅበራት የተወሰኑት ጉዳዩን እንዲይዙላቸው እውቅ ጠበቆችን መቅጠራቸውንና ከነዚህም መሐል የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የአቃቢ ሕግ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ እሸቱ ወልሰማያትና ቀድሞ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩም ይገኙበታል ይላል፡፡
ኾኖም የፍርድ ሂደቱ ከሁለት ዓመት በላይ የወሰደ ሲሆን ዳኞች ጉዳዩ እያሰጋቸው ነው መሰለኝ ቶሎ ቶሎ ይለዋወጡ ነበር ብሏል፡፡
አንዱ በፍርድ ቤት ጉዳዩን አከራካሪ ያደረገው ለማኅበራቱ መከፈል ያለበት የምንጣሮ ሥራ የቦታ ስፋት መለካት ያለበት በጂፒኤስ ነው ወይስ በሜትር የሚለው ሲሆን ሜቴክ በጂፒኤስ ይለካልኝ ሲል ማኅበራቱ በሜትር ነው መለካት ያለበት የተስማማነውም በዚህ መንገድ ነው ብለው ተከራክረዋል፡፡ ምክንያታቸውን ሲያስረዱም የመሬቱ አቀማመጥ ወጣ ገባ ስለሚበዛው በጂፒኤስ ቦታውን መለካት አካባቢው ጠፍጣፋና ሜዳማ እንደሆነ ታሳቢ እንደሚያደርግና የምንጣሮውን ልፋት ግምት ውስጥ የማይከት ያደርገዋል ባይ ናቸው፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ የመጀመሪያዋ ዳኛ የኢትዮጰያ ካርታ ሥራዎች ድርጅት ሞያዊ አስተያየት እንዲልክ በማዘዛቸው የከሳሽ ጠበቆች ቦታው በሜትር መለካት እንዳለበት የሚያስረዳ ደብዳቤ ከዚሁ መሥራያ ቤት አምጥተው ለውሳኔ ቀጠሮ ሊሰጥ ሲል የሜቴክ ጠበቆች ከተመሳሳይ መሥሪያ ቤት ቦታው በጂፒኤስ መለካት እነዳለበት የሚያስረዳ ሌላ ተጻራሪ ደብዳቤ አጽፈው በማምጣት መቻላቸው ፍርድ ቤቱን አስገርሟል፡፡ ሁለቱም ደብዳቤዎች የተፈረመባቸው በተመሳሳይ ሰው መሆኑም ሌላ አግራሞትን ፈጥሯል፡፡
ችሎቱን የምታስችለው ዳኛ በጉዳዩ በመደመም ችሎቱን ድንገት በትና የወጣች ሲሆን ከዚህ ዕለት ጀምሮም ችሎቱን የሚያስችሉት ዳኛ መቀየራቸው ተነግሯል፡፡ ዳኛዋ ከዚህ ውሳኔ ያደረሳቸው ምናልባት ቀደም ብለው የሜቴክ ኃላፊዎች መጥተው እንዲመሰክሩ የሚለው ትእዛዝ ሊከበርላቸው ስላልቻለ ሊሆን ይችላል፡፡
እኚህ ዳኛ ለማኅበራቱ የሚያደላ ውሳኔ ሊወስኑ ይችላሉ በሚል ለውሳኔ ቀጠሮ ከመሰጠታቸው ቀደም ብሎ የሜቴክ ጠበቆች ‹‹የኛ ሠራተኞች ጉዳይ የሚታየው በጦር ፍርድ ቤት ነው›› የሚል ነገር ለችሎቱ ማሰማታቸው ዳኛውን ሳያስቀይማቸው እንዳልቀረም ይገመታል፡፡
ሜቴክ በኮንትራት ለሚሰጣቸው ሥራዎች በጊዜውና ተገቢውን ክፍያ መክፈል ባለመቻሉ ተደጋጋሚ ቅሬታዎች ይቀርቡበታል፡፡
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ በስተምዕራብ 600 ኪሎ ሜትር በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባቦራ፣ ያዩ ወረዳ የድንጋይ ከሰል እያወጣ መሸጡ የሕዝብ ቅሬታን በመፍጠሩ በተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄን አስነስቶ ነበር፡፡
በሌላ ዜና የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን መስርተው ለስምንት ዓመታት ያስተዳደሩት ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኜው ሰሞኑን የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ሳምንታዊው የቢዝነስ ጋዜጣ ፎርቹን ዘግቧል፡፡

Saturday, February 3, 2018

ለትግሉ ወገናዊ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ፣-የአርበኞች ግንቦት ሰባትና የደሚሂት የጋራ መገለጫ በሚመልከት


 1. ማናቸው ድርጅት አርበኞች ግንቦት 7 ጨምሮ ከአባላቱም ፣ከደጋፊዎቹም። ከህዝብም የሚመጣ ትችት መቀበል የግድ ነው (ግዴታው ነው)። ፍጹም ሰው እንደሌለ ሁሉ ፍጹም ድርጅት ሊኖር አይችልም። የሚሰሩ ደግሞ ይሳሳታሉ። ስህተቶችን በአግባቡና ገንቢ በሆነ መልኩ በልዩ ልዩ መስመሮች ሲገለጽ አንድን ድርጅት የሚማርና ስህተቶቹንም እየረመ የሚሄድ ያደርገዋል። በዚህ አመለካከት ያለውን ለትግሉ ወገናዊ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይስማማሉ ብዬ እገምታለሁ።


2. ሰሞኑን የወጣውና ብዙ ውዝግብ ያስነሳው የአርበኞች ግንቦት ሰባትና የደሚሂት የጋራ መገለጫ በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ እንደ ሆነ ምንም የሚያጠያይቅ አይደለም። ስርዓትን መለወጥ ብቻ ሣይሆን የተረጋጋ ሐገር ለመፍጠር እንደሚንቀሣቀስ የፖለቲካ ሃይል በበደል ብዛት የተቆጡ ኢትዮጵያውያን ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ዉስጥ እንዳይገቡ ማሣሠቡ ተገቢ ይሆናል።በመግለጫው እንደተቀሠው ሠማን እንጂ አረጋገጥን ተብሎ አልተጻፈም፤ በሐገሪቱ ክልሎች የሕወሐት አባላትና የሕወሐት መልዕክተኞች መኖራቸውንም በመግለጫው በግልፅ ያመለክታል፤ በአጠቃላይ የመግለጫው ይዘት ትናንት ከተከሠተው ይልቅ ሥለነገው የሚጨነቅ መሆኑንም ማስታወሡ ተገቢ ነው፡፡ የመግለጫው ዓላማ ይህ ቢሆንም በአንድ በተሻለና እወነታውን በተጨባጭ ከማሳየት ይልቅ አሻሚ በሆነ ቋንቋ በተጻፈ አንድ አንቀጽ ( በአንዱ ዛፍ) .ጫካው በመሸፈኑ ውዥንብር ተከስቷል፡፡

3. በዋናው ጭብጥና መንፈስ (በጫካው) ወስጥ የተካተተው መልክት ሕዛብዊ ወያኔ አርነት ትግራይ (ህወአት) በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ኢትዮጵያን ካልገዛሁ ኢትዮጵያን አፈርሳታላሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ፣ ይህንንም ተግባራዊ ለማድርግ የትኛውንም ስልት ከመጠቀም ወደሁዋላ እንደማይል፣ ከነዚህም መሰሪ ስልቶቹ ወስጥ በዋነኘት የትግራይን ህዝብ ምሽግ ለማድረግ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማናከስና ወደ የማይታረቅ ቅራኔ ወስዶ የትግራይን ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያ ህዝብ መነጠል ብሎም መገነጠል በመሆኑ
ሀ) “የትግራይ ህዝብና ህወአት አንድና የማይነጣጠሉ ናቸው” የሚለውን የ 26 አመታት የወያኔ ትረካና ፕሮፕጋናዳ መናድ፣ ማፍረስ ወሳኝ የትግሉ አካል መሆኑን ።
ለ) የትግራይ ህዝብ ፣ የትግራይ ምሁራን፡ የትግራይ ድርጅቶች የዚህ የወያኔ መሰሪ ተግባር ሰለባ እንዳይሆኑ እንዲያውም ትግሉን ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመሆን እንዲያቀጣጥሉ ጥሪ ማቅረቡ።
በትክክሉ፡ በጥልቀትና በረጅሙ በማሰብም የኢትዮጵያ ሀገራችን የወደፊት ሰላም ፣ ሀገራዊ አንድነት፡ የህዝቦች አብሮ መኖር መጻኢ እድል ለሚያስስበው ማናቸውም ቅን (ቅንን የሚለው ይሰመርልኝ) ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህ መልክት ወቅታዊም አንገብጋቢም መሆኑን ሊያጡት አይችሉም ።
4. የወያኔ ፋሽስቶች የትግራይን ህዝብ ምሽግ አድርጎ የአምባገናዊ የዘረፋና የዘረኘነት ስረአቱን ለማሰቀጠል የሚያደርገውን የአልሞት ባይ ተጋዳይ እንቅሳቃሴ ለማምከን የኢትዮጵያ ህዝብ የጀመረውን ሁለ ገብ ትግሎችና ከወያኔ ፋሽስቶች ጋር የሚያድርገውን ትንንቅና ፍልሚያም በሚያፋፋምበት በአሁኑ ሰአት በሁሉም አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦችና ታጋዮች ሁሉ (በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ የኣርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮችን ጨምሮ) የህወአትን ሰላዮችና ገዳዮች ከስርአቱ ጋር ምንም ቁርኘት ከሌላቸው የትግራይ ተወላጆች ነጥሎ መመታት አስፈላጊና ፡ ህዝቡም በትግሉ ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው ነው በመግለጫው የተገለጸው።
5. ሌላው የመገለጫው ጫካ ዋና መንፈስ የአግ7 ንቅናቄ በወያኔ ፋሽቶች የአልሞት ባይ ተጋዳይነት ተንኮልና መሰሪነት ሊመጣ የሚችለውን የእርስ በእርስ ጦርነት ከፍተኛ ስጋት እንዳለው ነው የተገለጸው። በዚህ ፋሽታዊው ሕወአት በሸረበው ወጥመድ ውስጥ ታጋዩ ማህበረሰብ እንዳይገባ፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ነው ያሰመረበት፡ እነዚህ ዋና ዋና መልክቶች መግለጽ ሃላፊነት ከሚሠማው የፖሊቲካ ድርጅት የሚጠበቁ ተግባራት ናቹው፡፡

6. በእርግጥ በዚሁ ብዙ አነጋጋሪ በሆነው መግለጫ ላይ የተጻፈው አንድ አንቀጽ (አንድ ዣፍ) የሚሰጠው ትርጉም ከላይ በስተመጨረሻ #5 ከተጻፈው የተለየና ብዙዎች በሌላ መልኩ እንዲረዱት ማድረጉ ለተነሳው ውዝግብ መንሴኤ ሆናል።
7. በብዙሃን ቅን ኢትዮጵያውያን (አባላት፡ ደጋፊና፡ ለትግሉ ቀናዊ ከሆኑ) ኢትዮጵያውያን ወንድሞችና እህቶች አወዛጋቢዎችን አንቀጽ በሚመለከት የተነሱ ጥያቄዎች፣ ገንቢ አስተያየቶችና ፡ እርምት እንዲደረግና ንቅናቄው መልስ እንዲሰጥበት ከሚያስስቡ መልክቶች ሁሉ እንደተጠበቁ ሆነው ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከወያኔ ይልቅ ትግላቸውን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ጋር ለማድረገ የወስኑ ክፍሎችን በተመለከተ በአጭሩ ለማለት የምፈልገው በእርግጥ የሕዝቡ ሥቃይ ይሰማችኃልን ? በእርግጥ ከተሰማችሁ ሕዝብን ከሚያሠቃየውና ከሚጨፈጭፈው ሕወሐት ይልቅ ሕወሐትን የሚታገለው አርበኞች ግንቦት 7 እንዴት ዋነኛ ጠላታችሁ ሊሆን ቻለ? .መልሡን በቅንነት ለሚዳግፏቸው ወገኖቻችን እንደሚሰጡ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
8. የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ምንም ሳይደርስባቸው ገና ከጅምሩ በጠላትነት ፈርጀውት ከወያኔ ይልቅ ዱላቸውን በሙሉ ጊዜና ህይል ሳይቆጥቡ ለዚህ የጎንዮሽ ልፊያና ጠለፋ የሰጡ፣ ነገር ግን ለዚህ ውስብስብና ብዙ አቀበትና ቁልቁለት ለበዛበት ትግል ምንም ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ የማያደርጉ ግለሰቦችና ቡድኖች ማህበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት እያየን ነው፡
9. በአንጻሩ ይህን ትግል ዳር ለማድረስ ምን ያህል መስዋእትነት እየተከፈለና በተግባርም ብዙ ብዙ ተግባራዊ ስራዎች በሀገር ውስጥም በውጭም እየተሰሩ እንደሆነ የሚያውቁ፣ የሚረዱ፣ ለትግሉም ቀናኢ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የዚህ መሰሪ አካሄድ ሰለባ ላለመሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና ፡ በስሜት ሳይሆን በአምክንዮና ለትግሉ የሚጠቅመውን፡ የወያኔን ፋሽታዊ አገዛዝን የሚያስጨንቀውና የሚያዳክመውን፣ የኢትዮጵያን ህዝብ ለድል የሚያደርሱ፣ የሚያበቁ ፣ ለሀገራችን ኢትጵዮጵያ ትንሳኤን የሚያፋጥኑ ተግባራት ላይ ማተኮር ይገባል። በሰከነ አእምሮ ማሰብ የሚያስፍልግበት ስሱ ወቅት ስለሆነ፡ ቆም ብለን ፡ ትንፋሽ ወስደን በረጅሙና ከፊታችን በተደቀነው ተግባሪዊ ትግል ላይ አይናችንን እንዳናነሳ ማድረግ ያስፈልጋል። ጥንቃቄ እንዳርግ በሚል በትህትና ለማሳሰብ እወዳለሁ።
ነአምን ዘለቀ