Monday, October 30, 2017

ህወሃት ጣእረሞት ባጭሩ ሲዳሰስ (መስቀሉ አየለ ,October 24, 2017)


Meles Zenawi on fireለዘር ፖለቲካ የበላይነት በመስጠት ኢትዮጵያዊነትን ለማዳከም የቋንቋ ባቢሎን ገንብቶ ክልላዊ አድረጃጀትን ሲገነባ የኖረው ወያኔ የዘራው ዘር ፍሬ አፍርቶ ዛሬ የሱን ልሳን የሚናገሩ ሚሊዮኖች በየአቅጣጫው እንደ እንጉዳይ መፍላት ጀምረዋል። በዚህም የተነሳ ማእከላዊ መንግስቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ግባተ መሬቱ ተፈጽሟል ማለት ይቻላል።
በመሆኑም ከታሰበላቸው አቅም እጅግ አልፈው በመሄድ ለራሱ ለህወሃት የማይበጁበት ብቻ ሳይሆን የህልውናው ስጋት ወደ መሆን ደረጃ የደረሱትን ክልሎች እንደገና በማዳከም ብሎም ማእከላዊ መንግስቱን በተወሰነ ደረጃ በማጠናከር የህወሃትን የበላይነት መልሶ ለማስጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት መቀሌ ከትሞ የከረመው የትግራዩ ገዥ ጉጅሌ አንድ እስትራቴጅ ይዞ ወጥቷል።
ይኸውም በለማ መገርሳ፣ ዶር አቢይና አዲሱ አረጋ በኩል የታየው መቀናጀት፣ በተሾሙ በአጭር ግዜ ውስጥ ያገኙት የህዝብ ተቀባይነት እንዲሁም ከብአዴን ጋር የጀመሩት የጎንዮሽ ግንኙነት ቀጣዩን አደጋ ቁልጭ አድርጎ ያሳየው በመሆኑ በእድገት ሽፋን ወደ ፌደራል መንግስቱ አምጥቶ ከህዝብ በመነጠልና ሽባ በማድረግ እነሱን የተሻለ ሎሌ ሆነው ሊተኩ በሚችሉ አዳዲስ አሽከሮች ለመተካት ከስር ሰዎች አዘጋጅቶ የጨረሰ ሲሆን ሂደቱም ሃይለማርያም ደሳለኝን በራሱ በለማ መገርሳ እስከመተካት ድረስ ዘልቆ ሊሄድ እንደሚችል ፍንጮች መታየት ጀምረዋል።
ነገር ግን ይህ አካሄድ የማያዋጣ እና ህዝባዊ ተቃውሞውም የሚቀጥል ከሆነ “ማእከላዊ መንግስቱ ሃላፊነቱን ባለመወጣቱ የአገሪቱን ህልውና ሊያስጠብቅ ስላልቻለ በህዝቡ ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለመቀልበስ መከላከያው ላልተወሰነ ግዜ አገሪቱን የመምራት ሚናውን እንዲወጣና ጸጥታ እንዲያስከብር ሃላፊነቱን ወስዷል” በሚል አጭር የማርሻል አዋጅ ቤተመንግስቱን በታንክ በመክበብ የሃይለ ማርያምን ካቢኔ ጠራርጎ በማውረድ በኩዴታ ስልጣኑን ለሳሞራ የኑስ ወደማስረከቡ ይሄዳል ማለት ነው።
የመጀመሪያው አማራጭ የማይሰራ ከሆነና ወደ መፈንቅለ መንግስቱ መሄድ የግድ ከሆነበት ደግሞ ለዚሁ እርምጃ እንደዋና ግብአት ይሆነው ዘንድ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ዘር ተኮር የሆኑ ግድያዎችና ዘረፋዎች በስፋትና በተቀናጀ መልኩ በተጏዳኝ እንዲካሄዱ ህወሃት ያለውን አቅም ሁሉ አሟጦ እየተጠቀመ ነው። እዚህ ላይ ወያኔ አሁን ባለው የዘር ክፍፍልና ውሱን አቅም እንደ ግብጹ ሴሴ መፈንቅለ መንግስት አደርጋለሁ ቢል ይሳካለታል ብሎ ማሰብ አይቻልም። ይልቁንም ለህወሃት እንደዳይኖስረስ እራሱን በራሱ በልቶ ለመጨረስ የመጨረሻው ደወል መሆኑ አይቀርም።
በመሆኑም በተለያዩ የኦሮሞያ ግዛቶች ሰሞኑን በከፋ መልኩ ሲፈጸም እያየነው ያለው ከኢንተርሃሞይ የማይተናነስ የዘር ማጽዳት ከጌታቸ አሰፋ እየተቀበለ የሚያስፈጽመው ሰው ረዳት ኮሚሽነር ደመላሽ ገ/መስቀል ይባላል። ይኽ ሰው የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ነው።የትውልድ ስፍራው ምእራብ ሸዋ ዞን፣ የትምህርት ዝግጅት፦ በፖሊስ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በአመራር ሳይንስ እና በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን ሁለተኛ ዲግሪ ሲኖረው የስራ ልምዱ በኦሮሚያ ክልል ከወረዳ አንስቶ እስከ ክልል የፖሊስ አመራር፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።እዚህ ድረስ የደረሰው ለህውሓት ታማኝ በመሆኑ እና በጣም ጨካኝ እንደሆነ ይነገራል።

ESAT News (October 30, 2017)
A member of the European Parliament who is a fervent critic of the TPLF said current political developments in Ethiopia could lead to conflict with tremendous consequences to the Horn of Africa.
Speaking to ESAT on the phone, the Portuguese politician said she fears that the ongoing conflicts in various parts of the country will go out of hand with serious ramifications to the region and even to Europe.
Ana Gomes, who was an observer for the rigged 2005 election in Ethiopia, said the 2015 election in the country was a farce and no one came to observe it. As a result, the MP said the Ethiopian regime has no legitimacy. She wonders why the U.S. and EU still continue support the regime.
“It is really shocking to me that powers such as the U.S. and the EU and its member states know very well that TPLF has no legitimacy and democratic bases in Ethiopia and still continue to support under the pretext that it is an ally against terrorism,” Gomes said.
She said recent resignation by officials of the government and members of the army show that there is “tremendous fragmentation” and “lack of coherence with in the TPLF.”
“It shows that the situation is fast unravelling.”
“Those in U.S. and Europe used excuses to turn a blind and have neglected the democratic aspiration of the people of Ethiopia. The fact that they have supported and turn a blind eye to the totalitarian regime of the TPLF is going to provoke an uncontrolled explosion in Ethiopia. I am very very worried for Ethiopia as well as the Horn of Africa and Europe too because it has an implication for Europe,” Gomes added.
Speaking about Bereket Simon, who recently announced his resignation, and an official whom she dealt with during the 2005 election, the Member of Parliament described him as “cynical, cruel and despicable.”
“After Meles, he was the most despicable character i had to deal with.
He has a murky character. He could be operating from behind. I had always been extremely suspicious about him.”.
She also talked about Dr. Tedros Adhanom, the Ethiopian Director General of the WHO who was recently under fire for nominating Zimbabwe's Robert Mugabe. She said Dr. Tedros is “a member the TPLF and responsible for crimes committed by the criminal organization.”
She advised that change in Ethiopia will occur if Ethiopians come together and take matters in their own hands.
“They should not expect someone else come and make changes in the 

Ethiopia: 'Red Terror' war crimes trial begins at The Hague



An Ethiopian soldier stands inside the Martyrs Memorial to the "Red Terror" at the Holy Trinity Church in Addis Ababa, Ethiopia on 24 February 2004.
Image copyright Getty Images
Image 
caption Eshetu Alemu is accused of ordering the execution of 75 people during Ethiopia's "Red Terror"

The war crimes trial of an aide to Ethiopia's former communist ruler has begun in the Netherlands.
Eshetu Alemu, 63, is accused of ordering the execution of 75 people during Ethiopia's "Red Terror" purges in the late 1970s.
The former aide to then ruler Mengistu Haile Mariam is also accused of torture and inhumane treatment. He denies all the charges against him.
More than 300 victims have been named in four war crimes charges.
Ethiopia has sentenced him to death in absentia.Read more about Ethiopia
Prosecutors allege that Alemu, a dual Ethiopian-Dutch national, was a henchman for Mengistu in the north-west Gojjam province.
As his trial opened at a domestic court in The Hague, Eshetu Alemu said that prosecutors had "the wrong person".
"I was really shocked when I heard what prosecutors are accusing me of doing, that I could behave like that as a human being. I deny the charges against me," he told the four judges.

The Mengistu regime and the Red Terror



Image copyright Getty Images
Image caption Mengistu Haile Mariam governed Ethiopia between 1977 and 1991
Marxist strongman Mengistu Haile Mariam ruled Ethiopia between 1977 and 1991 following the overthrow of Emperor Haile Selassie in 1974.
There was significant repression under his communist regime. This became known as the "Red Terror".
Mengistu was ousted in 1991 after a series of revolts by insurgent groups. He then fled to Zimbabwe where he still resides.
In 2007, Mengistu was found guilty in absentia of genocide.

In a statement, prosecutors said that Alemu "allegedly ordered the killing of 75 young prisoners" in a church.
The bodies were then dumped in a mass grave, they said.
Alemu is also accused of "arbitrary detention and cruel and inhuman treatment of civilians and fighters who had laid down their arms" .
It is alleged that he tied prisoners up, suspended them in mid-air and beat their bare feet with sticks.
It is expected that a number of his alleged victims will give evidence during the trial.

'Terrible things happened'

Alemu testified in Dutch and told judges that he was a senior member of the Marxist-Leninist regime which governed the country. He said he was "responsible for propaganda" and had been targeted for assassination by other political groups.
In a statement read by presiding judge Mariette Renckens, Alemu said that "terrible things happened". He responded "no" when asked if he had "ever signed an execution order".
But the judge told Alemu that his signature was on an August 1978 order saying that "revolutionary measures" had to be be taken against more than 70 prisoners.
Orders of this kind, she said, usually meant "execution without trial".
Alemu denied giving the order, saying he lacked the authority to do so. "I was never there," he said.

Most big names already tried

Analysis by Tibebeselassie Tigabu, BBC Amharic service
People in Ethiopia are only really interested in this case because it is happening in The Hague.
Alemu is not a well-known figure from the Mengistu regime. Most of the big names have already been tried - and pardoned - over the past few years.
The trauma of the genocide is still felt among the people because it touched every house across the country.
The thing that interests and troubles people most is the fact that the late president Mengistu Haile Mariam is still at large in Zimbabwe, despite the fact that he has been sentenced to death in absentia.

Ethiopia: “I am worried Ethiopia will explode:” Ana Gomes


ESAT News (October 30, 2017)
A member of the European Parliament who is a fervent critic of the TPLF said current political developments in Ethiopia could lead to conflict with tremendous consequences to the Horn of Africa.
Speaking to ESAT on the phone, the Portuguese politician said she fears that the ongoing conflicts in various parts of the country will go out of hand with serious ramifications to the region and even to Europe.
Ana Gomes, who was an observer for the rigged 2005 election in Ethiopia, said the 2015 election in the country was a farce and no one came to observe it. As a result, the MP said the Ethiopian regime has no legitimacy. She wonders why the U.S. and EU still continue support the regime.
“It is really shocking to me that powers such as the U.S. and the EU and its member states know very well that TPLF has no legitimacy and democratic bases in Ethiopia and still continue to support under the pretext that it is an ally against terrorism,” Gomes said.
She said recent resignation by officials of the government and members of the army show that there is “tremendous fragmentation” and “lack of coherence with in the TPLF.”
“It shows that the situation is fast unravelling.”
“Those in U.S. and Europe used excuses to turn a blind and have neglected the democratic aspiration of the people of Ethiopia. The fact that they have supported and turn a blind eye to the totalitarian regime of the TPLF is going to provoke an uncontrolled explosion in Ethiopia. I am very very worried for Ethiopia as well as the Horn of Africa and Europe too because it has an implication for Europe,” Gomes added.
Speaking about Bereket Simon, who recently announced his resignation, and an official whom she dealt with during the 2005 election, the Member of Parliament described him as “cynical, cruel and despicable.”
“After Meles, he was the most despicable character i had to deal with.
He has a murky character. He could be operating from behind. I had always been extremely suspicious about him.”.
She also talked about Dr. Tedros Adhanom, the Ethiopian Director General of the WHO who was recently under fire for nominating Zimbabwe's Robert Mugabe. She said Dr. Tedros is “a member the TPLF and responsible for crimes committed by the criminal organization.”
She advised that change in Ethiopia will occur if Ethiopians come together and take matters in their own hands.
“They should not expect someone else come and make changes in the 

Monday, September 18, 2017

ፋሽስት ሆይ! ጠገዴ አንድ ቤተሰብ፣ ድንበሩም ተከዜ ነው! (ልሳነ ግፉዓንና የጠለምት አማራ ማንነት ጥምረት ኮሚቴ)


Welkait Tsegede

ፋሽስቱ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባርና ተላላኪው ብአዴን በአዲሱ አመት ዋዜማ ለመላው የጎንደር ህዝብ የሰጡት ስጦታ ቢኖር ሰላምና አንድነትን ሳይሆን አካሉ የሆነውን የጠገዴን ማህበረሰብ ለሁለት እንደ ቅርጫ መቀራምትን ነው።
ታላቋን ኢትዮጵያ የማፍረስና ህዝቧን የማተራመስ ተልዕኮ እንደ ቀደምት ባንዳ አባቶቹ ከጠላቶቻችን የተሰጠው የትግራዩ ወራሪ ቡድን የአማራን ህዝብና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀዳሚ ኢላማው አድርጎ በውድ ሃገራችንና በኩሩው ህዝባችን ላይ መርዙን መዝራት ከጀመረ እነሆ 26 የፅልመት አመታት ተቆጠሩ።
ከሽፍትነት ዘመኑ ጀምሮ ታሪካዊና ለም የሆኑትን የጎንደር መሬቶች በተቀዳሚነት ኢላማው ያደረገው ወራሪው ተ.ሃ.ት የተከዜን ወንዝ በመሻገር የወልቃይትን መሬት ከረገጠበት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ በወገናችን ላይ ያደርስ የነበረው ዝርፊያ፣ እስራት፣ ድብደባና፣ ግድያ እስከ ዛሬም ድረስ የቀጠለ ሲሆን በተለይም ከአንድ አመት በፊት የወልቃይትን ህዝብ ሙሉ ውክልና ይዘውና የህዝብን ጥያቄ አነግበው በሰላማዊ መንገድ ፍትህን የጠየቁ የወልቃይት አማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴ መሪዎችና አባላት በሽብርተኝነት ተወንጅለው በዋና ዋና የህወሃት የማሰቃያ ካምፖች ውስጥ መከራን እየተቀበሉ የሚገኙ ሲሆን፤ወረራውንና መስፋፋቱን በፍፁም ጭካኔና ማንአለብኝነት የቀጠለው ይህ እኩይ ቡድን ወደ ጠገዴና ጠለምት ያደረገውን ወረራ የተቃወሙትን ታሪክ ነጋሪ የሃገር ሽማግሌዎችን፣ ትውልድና ሃገር ጠባቂ ጎልማሳዎችን፣ እንዲሁም ሃገርና ታሪክ ተረካቢ የሆነውን ወጣት ትውልድ በግልፅና በስውር በመጨፍጨፍ ካጠፋ በኋላ ዕርስታችንን በሃይል ወደ ትግራይ በመጠቅለል በይፋ የምትገነጠለው ትግራይ አካል ከተደረገ እነሆ ሃያ ስድስት የሰቆቃ አመታት አሳለፍን።
ምንም እንኳ ህዝባችን በፋሽስቱ ህወሃት የጭቆና አገዛዝ ስር ሆኖ ቃላት ሊገልፁት በማይቻላቸው መከራና ስቃይ ውስጥ ቢገኝም ጭቆናንና ባርነትን አሜን ብሎ መቀበል ከአባቶቹ አልወረሰምና በሚቻለውና ባገኘው ቀዳዳ ሁሉ ተጠቅሞ የጠላቱን እኩይ ሴራ በማክሸፍ ላይ ይገኛል። ይሁንና ይህ ህዝባዊ ተጋድሎ እረፍት የነሳውና ኢትዮጵያን የማፈራረስና ትግራይን የመገንጠል ሰይጣናዊ ተልዕኮ እያኮላሸበት የሚገኘውን የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ህዝብ ለማዳከምና ከፋፍሎ ለማጥቃት በማለም አንድን ቤተሰብ የሆነውን የጠገዴ ማህበረሰብ ለሁለት በመክፈል ግማሹን ጠገዴ ሌላኛውን ግማሽ ፀገዴ በማለት ለያይተው የሚቻላቸውን ክፉ ተግባር ሁሉ ሲፈፅሙብን ኖረዋል።
ይሁን እንጂ ምንግዜም ቢሆን ጀግና መውለድ የማታቆመው የጎንደር እናት ዛሬም እንደ ትላንቱ አንድ ጠገዴ!!! ብለው በተነሱ ልጆቿ አማካኝነት ህዝባዊ ትግሉን በማፋፋም የፋሽስቱን ጎራ እያንቀጠቀጡት ይገኛሉ። “ወላድ በድባብ ትሂድ” እንዲሉ በጠገዴ የቁርጥ ቀን ልጆች የማያወላዳ ጥያቄ የተሸበረውና የዘመናት ሴራው በዜሮ የተባዛበት የተገንጣዩ ጎራ ከጳጉሜ 1, 2009 ዓ.ም ጀምሮ አንዳች የአማራ ህዝብ ድጋፍ በሌለውና እርሱ ህወሃት በአምሳሉ ጠፍጥፎ ከሰራው ብአዴን ተብዬ የአሻንጉሊቶች ስብስብ ጋር በመሆን አንዱን የጠገዴ ቤተሰብና ዕርስቱን ለሁለት በመከፈል መቀራመታቸውን በየፊናቸው እያወጁ ይገኛሉ።
የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ህዝብ ጥያቄ ግልፅና አንድ ነው። ይሃውም ህዝቡ ጎንደሬ/አማራ፣ መሬቱ የጎንደር፣ ድንበራችን ተከዜ ነው! የሚል ነው። ከዚህ ታሪክና ማንነትን መሰረት ካደረገ ህዝባዊ ጥያቄ አንዳች ጎደሎና እንከን የታከለበት ሽርፍራፊ ምላሽ ህዝባችን እንደማይቀበል የአለፉትን ሃያ ስድስት የፅልመትና የጭቆና ዘመናትን በፅናት በማለፍ ዛሬ እንደ አዲስ አይነቱንም ሆነ ይዘቱን ቅንጣት ሳይቀር ዳግም በወጣቱ ትውልድ መነሳቱ አብይ ማረጋገጫ ነው።
ታዲያ ይህን ታሪካዊ እውነታ አንዴ “በወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ” ኮሚቴ አማካኝነት፣ ሌላ ጊዜ “ጠገዴ አንድ ነው” በሚለው የጠገዴ ህዝብ ጥያቄ ሳይወድ በግዱ እንዲጋፈጠው የተደረገው ፍሽስቱና ተስፋፊው የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር “የማይተማመን ጓደኛ በየወንዙ ይማማላል” እንዲሉ ለሃያ ስድስት አመታት በሃይል ከልሎ ሲበዘብዛቸው የኖሩትን የጠገዴ ወገኖችን በተለይም ዕርስታችን የሆኑትን የግጨውና የጎቤ ጎንደሬ/አማራ መንደሮችን ትግሬ ያደረገ የትግራይን ድንበር ከአማራ ጋር ተካልያለሁ በማለት ሎሌዎቹን ሰብስቦ ከበሮ እየደለቀና ሻምፓኝ እየተራጨ ይገኛል።
እኛ በመላው ዓለም የምንገኝ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት ተወላጆች ዛሬም እንደትላንቱ በአንድነት ከህዝባችን ጐን በፅናት በመቆም የትግል አጋርነታችንና አንድነታችን እየገለፅን ከጳጉሜ 1, 2009 ዓ.ም ጀምሮ በህወሃትና በብአዴን መሪዎች አማካኝነት የታወጀው ጠገዴን ከሁለት በመክፈል በተለይም የጎንደር/አማራ ለምና ታሪካዊ የሆኑትን የግጨውና የጎቤ መንደሮችን ወደ ትግራይ መከለል ፍጹም ሰብአዊነት የጎደለውና አንድን ቤተሰብ ለሁለት የሚከፍልና የሚለያይ ጭራቃዊ ተግባር በመሆኑ የምንፀየፈው አጥብቀን የምናወግዘው መሆኑን እየገለፅን፤ ትላንት ከቀጣሪዎቹ በተሰጠው ኢትዮጵያን የማፈራረስ ባንዳዊ ተልዕኮ አንዱ የሆነውን ኤርትራን የማስገንጠልና የህጋዊና ዓለም አቀፋዊ ድንበር ባለቤት የማድረግ ሴራና ድራማ በቅጡ መከወን ያልተቻለው ፍሽስቱ ሟች መለስ ዜናዊ  ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሊያስፈፅም አልጀርስ ላይ ከኤርትራ ጋር የተስማማበትንና በአንፃሩ ደግሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ከጅምሩ አጥብቆ የተቃወመውን መሰሪ ውል ሲያፈርስ እንደ ዋነኛ ምክንያት ሲቀላምድ የነበረው “አንድ ቤተሰብ ለሁለት የሚከፍል” ፍርድና የድንበር ማካለል አልቀበልም በማለት ነበር።
ዛሬ የሙት መሪያቸው ራዕይ ወራሾች ነን በሚል በየመድረኩ ሲምሉና ህዝብን ሲያደነቁሩ የሚውሉ ውልደ ፋሽስቶች ህዝባችን በወኪሎቹ አማካኝነት “እኛ አንድ ቤተሰብ ነን!” “ጠገዴ አንድ ነው!” በሚል ያቀረበው ህዝባዊ ጥያቄ ለአልጀርሱ በተባው የክህደት ምላስና ህሊናቸው “አንድ ቤተሰብ ለሁለት የሚከፍል” ፍርድና የድንበር ማካለል አንቀበልም ማለትን እረስተው ህዝባችንን ዛሬም ድረስ ዘመን መለወጫን እየጠበቁ ያስለቅሱታል። ዕርስታችንም ታላቋን ትግራይ ለመመሥረት በሚል ቅዥት ወደ ትግራይ በማካለል ለሕዝባቸው የአዲስ ዓመት ስጦታነት ያውሉታል።
ይሁን እንጂ ዛሬም ህዝባችን በፍፁም ጨዋነት ያቀረበው ሰላማዊና ህጋዊ ጥያቄ ፍትሃዊ ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረት በተገንጣዮች የእብሪት እርምጃ አሁንም እንዲለያይ በግፍ የተፈረደበት ቤተሰባችን ዳግም አንድ ሆኖ በሃገሩ ላይ በነፃነትና በእኩልነት መኖር እስኪችልና ሰላሙና አንድነቱ እስኪረጋገጥ ድረስ ትግላችን ከምንግዜውም በላይ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ለፍሽስቱ ህወሃትና ለተንበርካኪው ብአዴን አመራሮች፣ አባላትና፣ ደጋፊዎች እያሳወቅን፤ በዚህም ምክንያት ለሚደርሱት ማንኛቸውም ሃገራዊና አካባቢያዊ ችግር ብቸኛ ተጠያቂው ፋሽስቱ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባርና ተላላኪው የብአዴን አመራር አካላት መሆናቸውን ከጥብቅ ማሳሰቢያ ጋር እንገልፃለን።
ጠገዴ አንድ ቤተሰብ፣ ድንበሩም ተከዜ ነው!
ልሳነ ግፉዓንና የጠለምት አማራ ማንነት ጥምረት ኮሚቴ
መስከረም 1, 2010 ዓ.ም
ሰሜን አሜሪካ

ኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች መካከል የተከሰተውን ግጭት የሚያብራሩ አምስት ነጥቦች

by maleda times



BBC AMHARICካርታ

አሁኑ ወቅት በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተቀሰቀሱ ግጭቶች በምክንያት የሰዎች ህይወት ጠፍቷል፤ ከሃምሳ አምስት ሺ በላይ የሚቆጠሩ ዜጎችም ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ ተገደዋል።
የኦሮሚያ ክልል መንግሥት፤ የሶማሌ ልዩ ፖሊስን እንዲሁም ሚሊሻዎች ወደ ኦሮሚያ ዘልቀው በመግባት ጥቃት አድርሰዋል ሲል የሚከስ ሲሆን፤ የሶማሌ ክልል በበኩሉ አጥቂዎቹን በኦሮሚያ ክልል የሚደገፉ ናቸው ሲል በኮሚኒኬሽን ቢሮው በኩል አሳውቋል። መወነጃጀሉና የቃላት ምልልሱ መካረር የክልሎቹ መንግስታት ግንኙነት ያለበትን ደረጃ ከማሳበቁም ባለፈ የግጭቶቹን መረር ማለትም አመላካች ነው። ይሁንና በሁለቱ ክልሎች መካከል ውዝግብ፣ ግጭት፣ ሲያልፍም ደም መፋሰስ ሲያጋጥም የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም።
1.አጨቃጫቂ ወሰን
በቆዳ ስፋቱ ከአገሪቱ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው የኦሮሚያ ክልል፤ ከሁለተኛው ሰፊ የሶማሌ ክልል ጋር የሚያዋስነው 1410 ኪሜ ድንበር አለው። ይህ ድንበር ግን ክልሎቹ አሁን ያሉበትን ቅርጽ ይዘው ከተመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ ውዝግብ አያጣውም። ውዝግቡን ፈትቶ ወሰኖቹን መልክ ለማስያዝ ታስቦም ሕዝበ ውሳኔ ከ400 በሚበልጡ ቀበሌዎች በጥቅምት ወር 1997 ዓ.ም ተደርጓል።
በሕዝበ ውሳኔው መሰረት ከ80 በመቶ በላይ የሚሆኑ ቀበሌዎች በኦሮሚያ አስተዳደር ሥር እንዲጠቃለሉ የተወሰነ ቢሆንም የወሰን ማካለል ሥራው ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቷል። ይህም በየጊዜው ለሚነሱ ግጭቶች አባባሽ ምክንያት መሆኑ አልቀረም።
ባለፈው ሚያዝያ ግን የሁለቱም ክልሎች ፕሬዚዳንቶች ሕዝበ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ያስችላል የተባለ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በተፈረመበት ወቅት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ለማ መገርሳ "ትልቅ ድል" መገኘቱን ሲገልፁ፥ የሶማሌ ክልል አቻቸው አብዲ መሃመድ በበኩላቸው "በሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ዳግመኛ ግጭት አይኖርም።'' ብለው ነበረ።
የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋም የችግሩ ምንጭ ''የድንበር ጉዳይ እንዳልሆነ የሚያረጋግጥልን፤ ድንበር በማንጋራባቸው አካባቢዎች ጭምር ጥቃት ሲፈፀም የነበረው። የድንበሩን ጉዳይ በ1997 ሕዝበ-ውሳኔ መሰረት ለመፍታት በተደረሰው ስምምነት መሰረት እየሰራን ነው።ሥራውም ሰባ በመቶ በላይ ተጠናቋል።'' ሲሉ ሌላ ምክንያት ሊኖር እንደሚችል ይጠቁማሉ።
2.የተፈጥሮ ብት ፉክክር
በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር የሚገኙ የኦሮሞ እና የሶማሌ ክልል አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አድር ሕዝቦችን ግንኙነት ያጠኑት የማኅበረሰባዊ ሥነ-ሰብ ተመራማሪው ፈቃዱ አዱኛ እንደሚሉት ፉክክርና ግጭት በተለይ የቦረና ኦሮሞዎችና የአካባቢው ሶማሌ ጎሳዎች መገለጫዎች ሆነው ቆይተዋል ይላሉ።
ፉክክርና ግጭቶቹ በብዛት ውሃ እና የግጦሽ መሬትን በመሳሰሉ የተፈጥሮ ሃብቶች ተጠቃሚነት ዙርያ የሚያጠነጥኑ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ አንስቶ የብሔር መልክ እየያዙ መምጣታቸው ይወሳል።
በአገሪቱ ፖለቲካዊ አወቃቀር የብሄር ድንበሮች የፖለቲካ ድንበሮች ጭምርም በመሆናቸው፤ በማኅበረሰቦቹ ዘንድ ያለውን የፉክክር መንፈስ ክልላዊ ገፅታ አላብሶታል ሲሉ ይከራከራሉ አቶ ፈቃዱ። ለዚህም በማሳያነት የሚጠቅሱት ከዚህ ቀደም በአንፃራዊነት ሰላማዊ ግንኙነት የነበራቸው የአርሲ ኦሮሞና አጎራባች የሶማሌ ጎሳዎች ደም ወዳፋሰሰ ግጭት መግባታቸውን ነው።
አካባቢዎቹ ለድርቅ ተጋላጭነታቸው ከፍ ያለ መሆኑ በተፈጥሮ ሃብት ፍላጎቶች ላይ ለሚነሱ ቅራኔዎች ተጨማሪ ነዳጅ የሆኑ ይመስላል።



ተፈናቃዮችን የሚያሳይ ምስል

3.የሕዝበ-ውሳኔ ራስ ምታት
ለተመራማሪው ፈቃዱ አዱኛ፤ መንግሥት ለአካባቢዎቹ ወሰን ተኮር ግጭቶች ፖለቲካዊ መፍትሄ ለመስጠት ባደረገው እንቅስቃሴ ሕዝበ-ውሳኔ ማከናወኑ የአካባቢዎቹን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነው። የአካባቢው ኗሪዎች በአብዛኛው አርብቶ አደሮች እንደመሆናቸው ከሥፍራ ሥፍራ ይንቀሳቀሳሉ። ይህም ወሰኑን ቁርጥ ባለ ሁኔታ ማስቀመጥን አዳጋች ያደርገዋል።
የህዝበ-ውሳኔው ውጤት በሁለቱ ክልሎች መካከል የተነሳውን ጥያቄ ምላሽ ሰጥቷል ቢባልም የተካሄደበትን ወቅት መሰረት ያደረገ ሌላ ጉዳይ አሁን እንደተነሳ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር "ከሶማሌ ክልል በኩል የሚነሳው ጥያቄ ሕዝበ-ውሳኔው የተካሄደበት ወቅት የሶማሌ ክልል የራሱን ግዛት ሊያስጠብቅ በማይችልበት አቅም ላይ በነበረበት ጊዜ በመሆኑ ብዙ ግዛት ተወስዶብኛል የሚሉ ጥያቄዎች እያነሳ ነው።" ይላሉ።
4.ሞትና መፈናቀል
ባለፈው ነሐሴ የተካረሩ ግጭቶችን ያስተናገደው የሚኤሶ አካባቢ ለወትሮውም ለዚህ መሰል ፍጭቶች ባይታወር አይደለም። ሕዝበ ውሳኔን ባስተናገደው የ1997 ዓ.ም በመኢሶና በቦርደዴ አካባቢዎች በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እንዲፈናቀሉ ያስገደዱ ግጭቶች ተከስተዋል ይላል የአይ ዲ ፒ ፕሮጄክት ሪፖርት።
በ2005 ዓ.ም ደግሞ በሞያሌ አካባቢ በተቀሰቀሰ የሁለቱ ብሔር አባላት ግጭት ከ20ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ሸሽተው ኬንያ መግባታቸውን የኬንያ ቀይ መስቀል ማህበር በዚሁ ወቅት አስታውቆ ነበር። በወቅቱ ለግጭቱ መቀስቀስ ምክንያት ተደርጎ የተጠቀሰው በግጦሽ መሬት ይገባኛል ቢሆንም ግጭቶቹ ብሄር ተኮር ይዘት እንዳላቸውም አብሮ ተዘግቧል።
ባለፈው ዓመት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባደረጉት ንግግር የሚከሰቱት ግጭቶች መንስዔ የብሄር ይዘት አለው ባይሉም፤ በግጦሽ መሬትና በውሃ የተቀሰቀሰ ነውም አላሉም። ከዚያ ይልቅ ለጉዳዩ ቅርበት አላቸው ያሏቸውን የአካባቢውን አስተዳዳሪዎችን ወቅሰዋል።
5.ማኅበረ-ባህላዊ ልዩነቶችና አንድነቶች
የኦሮሞና ሶማሌ ሕዝቦች ከምስራቅ ኩሽ የቋንቋ የዘር ግንድ የሚመዘዙ ሲሆን በኢትዮጵያ ሶማሌዎችና በተለይም እስልምና በገነነባቸው የኦሮሞ አካባቢዎች መካከል መልካም የሚባል ግንኙነት ተመስርቶ መቆየቱን የሚያነሱት አቶ ፈቃዱ፤ ባሌ ውስጥ የሚገኘው የሼክ ሁሴን መስጊድ በሁለቱም ሕዝቦች እንደ ቅዱስ ቦታ መቆጠሩን ያስታውሳሉ።
የሶማሌና የኦሮሞ ሕዝብ አብሮ ከመኖሩ አንፃር በርካታ አንድ የሚያደርጓቸው ነገሮች እንደሉ የሚጠቅሱት የፖለቲካል ሳይንስ መምህሩ፤ ምንም እንኳን እነዚህ ግዛቶች በወሰን ቢከፋፈሉም አሁንም የሁለቱ ህዝቦች የሚንቀሳቀሱባቸው ከተሞች አሉ፤ በማለት የሁለቱ ሕዝቦች አብሮነት እንደማይቋረጥ ይናገራሉ።