Wednesday, May 29, 2013

ማንዴላ በመጨረሻዋ የፍርድ ቀን ለዘረኞች ያለው Print PDF ሉሉ ከበደ


Former South African president Nelson Mandelaኢትዮጵያን በቁጥጥሩ ስር ያዋላት የትግራይ ዱር አራዊት ቡድን ዛሬ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየጫነ ያለውን የአፓርታይድ አይነት ስራት እነ ኒልሰን ማንዴላ ከደቡብ አፍሪካ ምድር ከስሩ መንግለው ለመጣል እጅግ ብዙ መስዋእትነትና ምእተ አመት የሚጠጋ ጊዜ ነበር የወሰደባቸው።
ምእራቡም ሆነ ምስራቁ አለም ለአፍሪካውያኑ የነጻነት ትግል ፈጥኖ እውቅናና ድጋፍ አለመስጠቱና በተለይ ምእራቡ ከነጮቹ ጋር ተመሳጥሮ በተዘዋዋሪ እነሱን መደገፉ ትግሉ ረጅም ጊዜ እንዲወስድና የነጻነቱም ቀን እንዲርቅ ቢያደርገውም፤ በትግሉ መሪዎች ፍጹም ቆራጥነትና ለሞት መዘጋጀት እንዲሁም በህዝቡ አንድነትና ጽናት አፓርታይድ ተወግዶ የደቡብ አፍሪካ ህዝብ መሪ መሾምና መሻር ችሏል በነጻነት።
እርግጥ  በኢትዮጵያ የበላይነቱን የተቆጣጠሩት የህውሀት ዘረኛ ሰዎች ከደቡብ አፍሪካ ነጮች ጋር ሊያነጻጽራቸው የሚያስችል ስልጣኔና ለነጩ አለም ቀረቤታ አላቸው ባንልም፤ ለሀያላኑ መንግስታት በሎሌነት እስከቀረቡና የሚታዘዙትን እስከፈጸሙ ድረስ ድጋፋቸውን እንደማይነፍጓቸው ባይናችን እያየነው በመኖር ላይ ነን። ይሁንና ከሁሉም በላይ ለወያኔ መቅበጥና ከልከ ማለፍ፤ ለነሱ የልብልብ ማግኘትና በላያችን ላይ መግነን ተጠያቂው እራሳችን ነን። አንድ ሆነን በቶሎ እነሲህን የኢጣሊያ ጣእረመንፈስ ነጋሲያን ፋሺሽቶች ማስወገድ ተስኖን የህዝቡን ደም እየጠቡ፤ የሀገሪቱን ሀብት እየዘረፉ መወፈራቸውን ቀጥለዋል።
የደቡብ አፍሪካውን የጥቂት ነጮች አፓርታይ መንግስት ለማስወገድ ኤ ኤን ሲ በ1912 ዓም ኢ ኤ አ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ከአርባ አመት በላይ ሰላማዊ የትግል ስልት ነበር ሲከተል የቆየው። ህዝባዊ እንቢታ፤ እቤት የመዋል አድማ፤ የሥራ ማቆም አድማ፤ ይለፍ ወረቀት ሳይዙ በጅምላ ሆ ብሎ የተከለከለ ቦታ ሄዶ መታሰር፤ ወዘተ…. ያሁሉ ግማሽ ምእተ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ የተካሄደው ሰላማዊ ትግል የህዳጣኑን መንግስት ጭቆናና ጭካኔ አባባሰው እንጂ ለደቡብ አፍሪካ ህዝብ የፈየደው ነገር አልነበረም።
ኋላ ላይ ግን እነማንዴላ ሀሳባቸውን ለመቀየር ተገደዱ። ሰላማዊው ትግል በትጥቅ ትግል መደገፍ እንዳለበት አመኑ። ይህንንም ወሰኑ። የሽምቅ ውጊያ ለመጀመር በርካታ የ ኤ ኤን ሲ ታጋዮች ማንዴላን ጨምሮ ወደተለያዩ ሀገሮች ለወታደራዊ ስልጠና ተሰማሩ። ማንዴላም ወደ ኢትዮጵያ አቀና። እናም እ ኤ አ በ1961 ዓም የ ኤ ኤን ሲ ወታደራዊ ክንፍ በማንዴላ መሪነት ተመስርቶ በመንግስቱ የኢኮኖሚና ወታደራዊ ተቋማት ላይ አደጋ መጣል ጀመረ።
የነጮቹ መንግስት የትግሉ ትኩሳት እየተሰማው በመጣ ቁጥር ወያኔ እንደሚያደርገው በየጊዜው አዳዲስ ህግ ማውጣትና ድርጅቶችን ሁሉ ማገድ፤ ህዝቡንና ታጋዮቹን ማሳደድ፤ ማሰርና ማዋከቡን በሙሉ ሀይሉ ቀጠለ። የትግሉን መሪዎች የደረሰበትን በቁጥጥር ስር አዋለ ያልተያዘውም ከሀገር መሰድድና ትግሉን ከጎረቤት ሁኖ መምራት ግድ ሆነበት። የታሰሩት መሪዎች የሀገር ክህደትና መንግስትን በሀይል ለማስወገድ መሞከር  በሚል ክስ ለሞትና ለድሜልክ እስራት ያዘጋጃቸው ጀመር አፓርታይድ ።
እ ኤ አ አቆጣጠር 1962 ዓም ማንዴላ ያለፍቃድ ከሀገር ወተሀል፤ ህዝብን ለአድማ አነሳስተሀል ተብሎ አምስት አመት ተፈርዶበት እስር ላይ እንደነበረ ነበር ይህ አዲሱ ክስ የተደረበለት። ከዘረኞች ፍርድ ቤት ለነጻነት ታጋዮች ፍትህ የለምና ከረጅም ጌዜ ከንቱ ክርክር በኋላ እነማንዴላ ጥፋተኞች ናቸው ብሎ ነጩ ዳኛ ፈረደ። የፍርዱን ልክ ከመበየኑ በፊት ተካሳሾች የፍርድ ማቅለያ ክርክራቸውን እንዲያሰሙ በታዘዙት መሰረት ማንዴላ አራት ሰአት የፈጀ ታሪካዊና ድፍረትና ሀቅ የሞላበት ንግግር  በጽሁፍ  አቅርቦ ነበር።
በዚያ የመጨረሻዋ የፍርድ ቀን ለችሎቱ የተናገረውን ማንዴላ በጻፈው መጽሀፍ ውስጥ አሳጥሮ አቅርቦታል። ያ የአላማ ጽናትና ቆራጥነት የተሞላበት ንግግር አንዷለም አራጌን እስክንድር ነጋን ያስታውሳል። በሀገራችን ካለው ሁኔታ ጋር ምን ያህል እንደሚመሳሰል ለማስገንዘብ ወደ አማርኛ መልሸዋለሁ።
ማንዴላ ተከሳሽ ሳጥን ውስጥ ቆሟል። ተራው ደርሶ የክርክሩን ማክተሚያ ያነብ ጀመር።
አንደኛ ተከሳሽ ነኝ። በባችለር ኦፍ አርት የመጀመሪያ ዲግሪ አለኝ። ጆሀንስበር ውስጥ ከሚስተር ኦሊቨር ታንቦ ጋር በሽርክና ሆነን ለተወሰኑ አመታት የጥብቅና ሙያ ሰርቻለሁ። በ 1961 ግንቦት መጨረሻ ላይ ህዝብን ለአድማ ማነሳሳት እና ካለፍቃድ ከሀገር መውጣት በሚሉ ክሶች የአምስት አመት ፍርድ ተፈርዶብኝ በእስር ላይ የምገኝ ፍርደኛ ነኝ።
ነሀሴ ወር 1962 ለእስር እስከተዳረኩበት ድረስ በጉዳዩ ከፍተኛ ሚና የተጫወትኩና ኡምኮንቶ ሱዚዌ፤ የኤ ኤን ሲን ወታደራዊ ክንፍ ለማደራጀት ከረዱት መካከል አንዱ መሆኔን እቀበላለሁ።
ከሁሉ በፊት መንግስት በመግቢያው ላይ በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው ትግል፤በውጭ ሀይሎች ወይም  በኮሙኒስቶች ተጽእኖ ስር ያለ ነው የሚለውን ሀሳብና ግምት ባጠቃላይ ስህተት ነው ለማለት እሻለሁ። ያደረኩትን ነገር አድርጌአለሁ። እንደ ግለሰብም እንደ ህዝብ  መሪነትም። ይህንን ሳደርግ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባለኝ ተሞክሮና በፍጹም አፍሪካዊ ኩራትና ክብር እንጂ የውጭ ወገኖች ባሉትና በሚሉት ተመርቼ ተነሳስቼ አይደለም።
በወጣትነት ዘመኔ ትራንስኪ ውስጥ የጎሳችን  አረጋውያን ስላለፈው የጥንት ዘመን ታሪክ ወግ ሲነግሩን እሰማ  ነበር። ሽማግሌዎች ከሚያወሷቸው የሗላ ታሪካችን ከኔ ጋር የሚያመሳስሉት የነበረው “ ያባትን ሀገር “ ለመከላከል ያደረጓቸውን ጦርነቶች ሲያነሱ’ የእነ ደንጌ እና ባንባታ፤ ሂንሳና ማካና፤ ኩንቲና ዳላሲል፤ ሞሾሾና ሲሁሁኔ ስሞች ሲጠቀሱ፤ የመላው አፍሪካ ክብርና ኩራት ሆነው ይሞገሱ ይወደሱ ነበር። ያኔ ያን ታሪክ ሥሰማ ተስፋ አደርግ  ነበር። ለህዝባችን የነጻነት ትግል የበኩሌን ጥቂት አስትዋጾ እንዳበረክት፤ ህይወት አንድ አጋጣሚ ትቸረኝ ይሆናል እያልኩ። በዚህ ጉዳይ ላይ ክስ ሲመሰረትብኝ እንደጥፋት የተጠቀሰውን ሁሉ እንዳደርግ መነሻና ግፊት የሆነኝ ይኸው የኋላ ታሪካችን ነበር።
ይህን እያልኩ የአመጹን  ጥያቄ አነሳና ፈጥኜ ጥቂት ዘለግ ላለ አፍታ ያለውን  ነገር ላስረዳ ግድ ይለኛል። እስካሁን ለችሎቱ ከተነገሩት ነገሮች ገሚሱም እውነት ገሚሱም እውሸት ናቸው። የሆነው ይሁንና ሻጥር ( በመንግስት የኢኮኖሚ ተቋማት ላይ አደጋ መጣል) ማቀዴን አልክድም። ይህንንም ሳቅድ በግዴለሽነትና በዘፈቀደ መንፈስ ተሞልቼ ወይም ደግሞ አመጽን የምወድ ሰው ሁኜ አይደለም። የረጅም ዘመን አንባገነንነት ያስከተለውን የነጮች  ብዝበዛና ጭቆና የተንሰራፋበትን የፖለቲካ ሁኔታ በሰከነ  አእምሮና  በተረጋጋ ሁኔታ ስገመግም ከኖርኩ በኋላ ነው በውጤቱ ይህን እርምጃ ለማቀድ የወሰንኩት።
ለችሎቱ ለማስረዳት የሞከርኩት ይህን የአመጽ እርምጃ ስንወስድ ሀላፊነት ሳይሰማንና ያልተጠበቀ ውስብስብ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል  ሳናስብ ቀርተን እንዳልነበር ነው። አንድም አይነት ጉዳት በሰው ህይወት ላይ እንዳይደርስ ለማድረግ መወሰናችንን አጽንኦት ሰጥቼ ነበር።
እኛ ኤ ኤን ሲዎች ምንጊዜም የቆምነው ከዘረኝነት የጸዳ ዲሞክራሲ  እንዲሰፍን ነው። ጎሳዎችን እስካሁን ካሉበት ሁኔታ  በባሰ መልኩ ከሚያራራርቅ ማናቸውም ድርጊት እንታቀባለን። ጠጣሩ እውነታ ወይም ሀቅ ግን የሀምሳ አመት ሰላማዊ ትግል ለአፍሪካውያን ያተረፈው ያስገኘው ነገር ቢኖር እየበዛ እየበዛ የመጣ የመጨቆኛ ህግና እያነሰ እያነስ የሄደ መብት ብቻ ነው። ለዚህ ችሎት ይህን መረዳት ቀላል ላይሆን ይችላል። ህዝቡ ለረጅም ዘመን ሀይል ስለታከለበት አመጽ ሲነጋገር መኖሩ እሙን ነው። የአመጽን አማራጭ ተተው በሰላማዊ ትግሉ እንዲቀጥሉ እኛ የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች ብንመክርም፤  ከነጮች ጋር ተዋግተው የሀገራቸው ባለቤት ስለሚሆኑባት ቀን ይወያያሉ። ግንቦትና ሰኔ 1961 ዓም ገሚሶቻችን ይህን እየተነጋገርን በነበረ ወቅት ከዘረኝነት የጸዳ መንግስት እንዲኖረን ለማድረግ የሰላማዊ ትግሉ ፖሊሲ ምንም ውጤት እንዳላመጣ መካድ አልተቻለም ነበር። ተከታዮቻችን በዚህ ፖሊሲ ላይ መተማመን እያቃታቸው፤ የሀይልን አመጽ እንደአማራጭ በአእምሮ ውስጥ ማጎልበት ጀመሩ። የሚረብሽ የአሽባሪነት እሳቤ።
የ ኤ ኤን ሲ ወታደራዊ ክንፍ ህዳር 1961  ዓም ተመሰረተ። ይህን ውሳኔ ስናስተላልፍና በተከታታይ እቅዳችንን ስንነድፍ የ ኤ ኤን ሲ ሌጋሲ ከአመጽ  በጸዳ ትግል ህብረ ዘርነት እውን የሚሆንበት ሀሳብ አብሮን እንዳለና እንደያዝነው ነበር። ሀገሪቱ በጥቁሮችና   በነጮች መካከል ወደሚቀሰቀስ የርስበርስ ጦርነት በሚያስኬድ ጎዳና ላይ እየተጓዘች እንዳለች ይሰማናል። ነገሩን የምንመለከተው በማስጠንቀቂያ ደወል ነው። የርስ በርስ ጦርነት ማለት ኤ ኤን ሲ የቆመለትን እሴት ማውደም ማለት  ነው። የርስ  በርስ ጦርነት ከተነሳ ማናቸውም ዘር ሰላም የማግኘት እድሉ እጅግ የከፋ ይሆናል። ጦርነት የሚያስከትለውን የከፋ ነገር ለማወቅ በደቡብ  አፍሪካ ታሪክ ውስጥ በቂ ምሳሌ አለን። በደቡብ አፍሪካ አንግሎ – ቦር  ጦርነት ያስከተለው ጠባሳ ለመሻር ከሀምሳ አመት በላይ ወስዷል። ዘር በዘር ላይ ተነስቶ ከሁሉም በኩል በቀላል የማይገመት ህዝብ በሚያልቅበት ሁኔታ ጦርነት ቢካሄድ ጠባሳው ለመሻር ምን ያህል ዘመን ይፈጃል?
በተግባር አይተን እንዳመነው፤ አመጽ፤ ለመንግስት፤ ህዝባችንን በጅምላ መጨረስ የሚያስችል ገደብ የሌለው እድል ይሰጠዋል። በርግጥም የደቡብ አፍሪካ ምድር፤ አፈር፤ ዱሮ በንጹሀን አፍሪካውያን ደም ጨቅይቷል። ሀይልን በሀይል መክተን ራሳችንን ለመከላከል የመዘጋጀት የረጅም ጊዜ ስራ መስራት ተግባራችን እንደሆነ ይሰማናል። ጦርነት አይቀሬ ከሆነ ጦርነቱ መመራት ያለበት ለህዝባችን ሁኔታ በተመቸ መልኩ እንዲሆን እንሻለን። ለኛ አንድ ነገር ያጎናጽፋል፤ እናም በሁለቱም ወገን አነስተኛ የህይወት መስዋእትነት የሚያስከፍል ይሆናል  ብለን ያልነው የሽምቅ ውጊያ ነው። ለዚሁ ዝግጅት ለማድረግ ወሰንን።
ነጮች  በሙሉ የግዴታ ወታደራዊ ስልጠና ይሰጣቸዋል። ለጥቁሮች ይህ ነገር አይደረግም። የሽምቅ ውጊያውን ሊመሩ የሚችሉ፤ ወታደራዊ ስልጠና ያላቸው ሀይሎችን መገንባት መሰረታዊ እሳቤአችን ነው። ሳንዘገይ ለዚህ መዘጋጀት አለብን።
ውይይታችን በዚህ ደረረጃ ላይ እንዳለ በአፍሪካ ሀገሮች ልዩ ልዩ ጉባኤዎችን ለመካፈልና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ካገር እንደወጣሁ አስረዳሁ። የሽምቅ ውጊያ ቢጀመር ከህዝቤ ጋር አብሬ ለመቆም ለመዋጋት እንድችል፤ ወታደራዊ ስልጠና መውሰዴን ተናገርኩ።( ማንዴላ ወታደራዊ ስልጠና የወሰደው ኢትዮጵያ ነበር ) በ ኤ ኤን ሲና በወታደራዊ ክንፉ መካከል ያለውን የሚለያቸውን መስመር ለችሎቱ ገለጽኩ። ሁለቱ እንዴት የተለያዩ መሆን እንዳለባቸው እንዳደረግን ተናገርኩ። ፖሊሲያችን  ነበር። ተግባር ላይ ለማዋል ቀላል አልነበረም። በህግ መታገድ መታሰር ሁሉ ስለነበረ ሰዎች በሁለቱም ውስጥ መስራት  ነበረባቸው። የኮሙኒስት ፓርቲውና ኤ ኤን ሲ አንድ ዓላማ አላቸው የሚለውን የመንግስት ክስ ተከራሬዋለሁ።
የ ኤ ኤን ሲ ርእዮተ ዓለም መርህ ምን ጊዜም አፍሪካዊ  ብሄረተኝነት ነው። “ ነጭን ወደ ባህር ንዳው “ የሚለው አይነት የአፍሪካ ብሄረተኝነት ጩኽትም አይደለም። ኤ ኤን ሲ የቆመለት አፍሪካዊ ብሄረተኝነት፤ አፍሪካውያን በምድራቸው ምሉእ ሆነው በነጻነት እንዲኖሩ የሚያስችል ጽንሰ ሀሳብ ነው። የ ኤ ኤን ሲን ዓላማና አቋም የሚያንጸባርቀው ሰነድ በ ኤ ኤን ሲ የጸደቀው የነጻነት ቻርተር ሰነድ ነው። በምንም መልኩ የሶሻሊስት መንግስት እቅድ አይደለም። ለሀገሪቱ ታሪክ  ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ መዋቅር ኤ ኤን ሲ መቼም አብዮታዊ ለውጥን ደግፎ አያውቅም። እስከማውቀው የካፒታሊዝምንም ስራት አውግዞ አያውቅም።
ከኮሙኒስት ፓርቲው በተለየ መልኩ ኤ ኤን ሲ በአባልነት አፍሪካውያንን ብቻ ነው የሚቀበለው። ዋና አላማውና ግቡም አፍሪካውያን አንድነትና የተሟላ የፖለቲካ መብት እንዲቀዳጁ ማድረግ ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ ዋና አላማ  በሌላ መልኩ ካፒታሊስቶችን ማስወገድና በሰራተኛው መደብ መንግስት መተካት ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ ለመደብ ልዩነት አጽንኦት ሲሰጥ ኤ ኤን ሲ በህብር አብረው የሚጓዚበትን ሁነት ይፈልጋል።
እርግጥ ነው በ ኤ ኤን ሲና  በኮሙኒስት ፓርቲው መካከል የቅርብ ትብብር አለ። ትብብሩም የጋራ የሆነ ግብ  መኖሩን የሚያረጋግጥ ነው።  ጉዳዩ የነጮችን የበላይነት ማስወገድ  ነው። ይህ ማለት በሁሉም አቅጣጫ የጋራ አቋምና የጋራ ግብ እንዳለ ያረጋግጣል ማለት አይደለም። የአለም ታሪክ በተመሳሳይ ምሳሌዎች የተሞላ ነው። ምናልባትም ስሜት የሚሰጠው ስዕል፤ ታላቋ ብሪታንያ፤ አሜሪካና ሶቬት ህብረት ናዚ ሂትለርን ለመውጋት ያደረጉት ትብብር ነው። ሂትለር ብቻ ካልሆነ በስተቀር፤ ቸርችልን ወይም ሩዝቬልትን ወደ ኮሙኒስትነት ተቀየሩ ብሎ ማንም ሰው ለመናገር የሚደፍር አይኖርም። ወይም ደግሞ አሜሪካና እንግሊዝ የኮሙኒዝምን ስራት ለማስፈን እየሰሩ ነው የሚል አይኖርም። ልምድ ያላቸው አፍሪካውያን ፖለቲከኞች ኮሚኒስቶችን ለምን ጥሩ ወዳጅ አድርገው እንደሚቀበሏቸው ስር የሰደደ መጥፎ አመለካከት በነሱ ላይ ላላቸው የደቡብ አፍሪካ ነጮች መረዳት በጣም ሊከብዳቸው ይችላል። ለኛ ግን ምክንያቱ ግልጽ ነው። በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ለብዙ አስርት አመታት ጥቁሮችን እንደሰው ለማስተናገድ የተዘጋጁ፤ ኮሙኒስቶች ብቻ ነበሩ። እኩልነታቸውን የተቀበሉ፤ አብረውን ለመብላት ለመጠጣት የተዘጋጁ፤ አብረውን ለማውጋት፤ አብረውን ለመስራትና ለመኖር የተዘጋጁ። በዚህም ምክንያት ዛሬ ብዙ አፍሪካውያን ናቸው ኮሙኒዝምን ከነጻነት ጋር እኩል አድርገው የማየት ዝንባሌ ያላቸው።
እኔ ምንጊዜም ራሴን እንደአፍሪካዊ አርበኛ የምመለከት እንጂ ኮሙኒስት አለመሆኔን ለችሎቱ አስረዳሁ። መደብ አልባ ስራት  በሚል አስተሳሰብ መማረኬን ወይም ደግሞ የኮሙኒስት አስተሳስብ ተጽእኖ እንዳሳደረብኝ አልካድኩም።
ካነበብኳቸው የኮሙኒዝም ጽሁፎችና ከተወያየሗቸው ማርክሲስት ግለሰቦች እንደተረዳሁት ኮሙኒስቶች የምእራባውያንን የፓርላማ ስራት ኢዲሞክራሲያዊና አድሀሪ እንደሚሏቸው ተገንዝቤአለሁ። በተቃራኒው ግን እኔ የዚያ አይነቱ አሰራር አድናቂ ነኝ።
ማግና ካርታ ( መሰረታዊ መብት ማረጋገጫ ሰነድ)፤ ፔቲሽን ኦፍ ራይት፤ ቢል ኦፍ ራይትስ፤ የሚባሉት ሰነዶች  በመላው ዓለም የሚገኙ ዲሞክራቶች ዘንድ በክብር የሚያዙ ሰነዶች ናቸው። ለብሪታንያ የፖለቲካ ተቋማት ታላቅ አክብሮት አለኝ። ለሀገሪቱ የፍትህ ተቋማትም እንደዚያው። የብሪያንያን ፓርላማ በዓለም ከፍተኛው ዲሞክራሲያዊ ተቋም አድርጌ  ነው የምመለከተው። የፍትህ ተቋማቷ ራስ ገዝነትና ያለ ወገንተኝነት መስራት አድናቆቴን ሳያጭሩ የቀሩበት ጊዜ የለም። የአሜሪካን ኮንግረስ፤ የሀገሪቱ ስልጣን ክፍፍል፤ የፍትህ ተቋማቷ ራስ ገዝነት ተመሳሳይ አድናቆት በውስጤ ያጭራሉ።
በደቡብአፍሪካ ውስጥ በጥቁሮችና  በነጮች ህይወት መካከል ያለውን አስደንጋጭ ልዩነት ዘረዘረኩ። በትምህርት፤ በጤና፤ በገቢ፤ በየፈርጁ ጥቁሮች በህይወት ለመቆየት ብቻ  በሚያስችል ደረጃ ሲኖሩ፤ ነጮች በአለም ያለውን ከፍተኛ ደረጃ  ይኖራሉ። እናም ህይወት በዚሁ መልኩ እንድትቀጥል የማድረግ ዓላማ አለ። “ነጮች” አልኩ። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ያሉት ጥቁሮች በሌላው አፍሪካ ካሉት ጥቁሮች የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ብለው ያስባሉ። የኛ እሮሮ አልኩ፤ ከሌላው የአፍሪካ ህዝብ ጋር ስንነጻጸር ድሆች ነን አይደለም። በሀገራችን ውስጥ ካሉት ነጮች ጋር ስንነጻጸር ድሆች ነን ነው። ይህንን የተዛባ ሁኔታ እንዳናርም እንዳናስተካክል በህግ ተከልክለናል ነው።
አፍሪካውያን በሀገራቸው ክብር ያጡበት ሁኔታ ነጮችን የበላይ የማድረጉ ፖሊሲ ቀጥተኛ ውጤት ነው። የነጮች የበላይ መሆን የጥቁሮችን የበታችነት ያስከትላል። የነጩን የበላይነት ለመጠበቅ የሚወጣው ህግ ይህን እምነት ስር እንዲሰድ ያደርገዋል። በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ማናቸውም ዝቅተኛ ስራ  በጥቁሮች ነው የሚሰራው። አንድ ነገር መነሳት ወይም መጽዳት ካለበት  ያን ስራ እንዲሰራለት ነጩ ጥቁሩን ገልመጥ ገልመጥ ብሎ ይፈልገዋል። አፍሪካዊው የርሱ ተቀጣሪ ሆነም አልሆነም።
ድህነትና የቤተሰብ መፍረስ የሚያስከትሉት ነገር አለ። የሚሄዱበት ትምህርት ቤት ስለሌላቸው፤ ወይም ትምህርት   ቤት እንዲውሉ የሚያስችል ገንዘብ  ወላጆቻቸው ስለሌላቸው፤ ህጻናት በየጎዳናው ሲንከራተቱ ይውላሉ። እቤት ውስጥም ተገኝተው ልጆቻቸው የት እንደሚውሉ ሊያዩ የሚችሉ ወላጆች የሉም። እናትም አባትም ያውም ሁለቱም ካሉ ቤተሰቡን በህይወት ለማቆየት ስራ  ብለው ውጭ መዋል አለባቸው። ይህ የወደቀ የሞራል ደረጃን ያስከትላል። በፖለቲካ  ብቻ ሳይሆን  በየአቅጣጫው ህገወጥነት፤አመጽና ሁከት እንዲንሰራፋ ያደርጋል።
አፍሪካውያን   በመላዪቱ ደቡብ አፍሪካ እኩል ድርሻ እንዲኖራቸው ይሻሉ። በህብረተሰቡ ውስጥ የደህነነት ዋስትናና ድርሻ እንዲኖራቸው ይሻሉ። ከሁሉም በላይ እኩል የፖለቲካ መብት እንዲኖረን እንሻለን። ያለዚህ መብት ስንኩልነታችን ዘለአለማዊ ነው የሚሆነው። በዚህች ሀገር ውስጥ ላሉት ነጮች ይህ አብዮታዊነት እንደሚመስላቸው አውቃለሁ። ምክንያቱም ብዙሀኑ መራጭ የሚሆነው ጥቁሩ አፍሪካዊ ስለሚሆን ነው ነጩ ዲሞክራሲን እንዲፈራ የሚያደርገው።
ይህ ኤ ኤን ሲ የሚዋጋለት ጉዳይ ነው። ትግላቸውም እውነተኛ ብሄራዊነት ነው። ባፍሪካውያን በራሳቸው ተሞክሮና በደረሰባቸው ስቃይ የተቀሰቀሰ የአፍሪካ ህዝቦች ትግል ነው። በህይወት የመኖር መብት ትግል ነው።
ንግግሬን አነበብኩ። እዚህች ነጥብ ላይ እንደደረስኩ ወረቀቶቼን ተከላካይ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጥኩና ፊቴን ወደ ዳኛው መለስኩ። ችሎቱ ፍጹም ጸጥ እረጭ አለ። የመጨረሻዋን ንግግር ከትውስታዬ ስናገር ፊቴን ከዳኛ ዴዊት ላይ ዘወር አላደረኩም ነበር።
በህይወት ዘመኔ ለዚህ የአፍሪካ ህዝብ ትግል ህይወቴን አሳልፌ ሰጥቻለሁ። የነጮችን የበላይነት እየተዋጋሁ ነው። የጥቁሮችን የበላይነት እየተዋጋሁ ነው። ሁሉም ሰው ተዋህዶ፤ ሰምሮና አብሮ እኩል እድል እየተጋራ አንድ ላይ መኖር አለበት የሚል አስተሳስብ አለኝ። የምኖርለትና እንደግብም ልለቀዳጀው ተስፋ የማደርግበት አስተሳሰብ  ነው። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም ለመሞት የተዘጋጀሁለት አስተሳሰብ ነው።
አሁን  በችሎቱ ፍጹም ጸጥታ ሆነ። የመጨረሻዋን ከተናገርኩ  በኋላ ቁጭ አልኩ። በችሎቱ ውስጥ የነበሩ ታዛቢዎች ሁሉ አይናቸው እኔ ላይ ያረፈ መሆኑ  ቢሰማኝም ቤቱ ውስጥ ወዳለው ህዝብ ዘወር ብየ አላየሁም። ጸጥታው ለበርካታ ደቂቃዎች የዘለቀ  ቢመስልም ግን ምናልባትም ከሰላሳ ሲኮንድ በላይ አልቆየም ነበር። በረጅሙ የሚተነፍስ፤ ቁናቁና የሚተነፍስ፤ የሕብር ጉምጉምታ፤ የሴቶች ለቅሶ ተከትሎ በፍርድ ቤቱ ውስጥ ይሰማ ጀመር….
“LONG WALK TO FREEDOM” NELSON MANDELA (PAGE 432-438)
lkebede10@gmail.com

Monday, May 27, 2013

TPLF Devised of its Political Manifesto in 1976 to Commit Genocide against Amhara, by Gudu Kassa


Gudu Kassa

The  Tigrayan People's  Liberation Front(TPLF), fascist group had begun to realize their   anti  _ Amhara people labeling them as ethnic group    since 1976  and devised  their   manefesto in 1976  which they pressed "The TPLF manifesto_1968 ". The present Tigrayan Republic   demarcated based on "the 1968  TPLF manifesto" included Welqayitstegedy  and,Seatu Humera of Gondar and Raya ina Qubo of Wollo  .   They (TPLFs) have been working objectively to subjugate  the Amhara people  since 1976. Since then the master mind of TPLF proceeded their devised political agenda segregate Amhara people from the rest of Ethiopians .By devising such political ploy began   committing    genocide and/or ethnic cleansing  against the Amara people most of which are systematic  genocide against the Amhara people. It is imperative  to provide the following documented  credential  evidences about the TPLF committed genocide  against Amhara people since its history at  different time and place : Ever since TPLF took power and in the history of Ethiopia ,they have been targeting people of Amhara origin TPLF after they took power in 1991, they targeted  people of  Amhara and Amhara  origin all over Ethiopia  in their campaign of ethnic cleansing. Still at this movement, they have displacing, torturing  and brutally killing  Amharas any way they can and continuing to do so.The most notable tragic genocide committed by TPLF was  the Bedeno genocide ,where they threw men,women,and children of Amhara ethnic group down a shallow hole while alive. In Arusia, Arbagugu genocide committed in the same fashion they did in Bedeno in 1992,following this  as reported by DW radio ,the TPLF regime forcefully displaced over 20,000 Amharas from a place in Southern Ethiopia called Bench maji zone.
 A census in 2007 found major discrepancy in its reports,showed out of all ethnic groups  in Ethiopia ,the  Amhara ethnic group population revealed an anomaly. According to the census carried out by the TPLF,2.4 millions  Amharas disappeared. Nevertheless, Amhara ethnic group population anomaly  had been remained unjustified  by  the Central Statistics Authority(CSA). The Central Statistics Authority(CSA) official justification explained  in   probability of   the highest infant mortality rate  and  HIVAIDS death in the respective region(Amhara) can be the most likely reasons to the 2007 census discrepancy in the Amhara region.  The justification  to the census anomaly on Amhara ethnic group population confirm the TPLF systematic and targeted genocide  against  Amhara people.The North Gondarian  Amhara people displacement  and/ or replacement by Tigrayan (especially from an areas: Armacheh , Wolket tegeday and Seatetu Humera ( since Humara Sesame seed  variety is well known in the world  market). Such  calculated , targeted and forced  displacement and/or replacement of the Amhara people  from  their birth place and farm land so as  to benefit   Tigrayan  minority ethnic group . In  2012,as reported by Ethiopian Satellite Television (ESAT) and other medias outlets approximately more than   70,000 Amhara ethnic group forced displacement from  Gura ferda in SNNR  can be the most calculated and targeted against Amhara ethnic group to accomplish the 1976 TPLF manifesto of  ethnic cleansing.  There fore, we are too late to take counter action we have to be able to defined ourselves together with other victim  citizen of Ethiopians. TPLF ruled Ethiopia with hunger ,conflict and genocide as a means of repression and deception. Ethiopia as a result of TPLF come to power become landlocked  and paid millions of dollar for the port rent. The tyranny ethnio fascist TPLF junta   had also given away  land from Ethiopia which accounts 88,000km square( 1,600 km  length boarder length with 60 kms radius(distance to  inside) from south western Sudan boarder  to Sudan government   in lack of accountability to Ethiopian people. TPLF, Tigrayians minority recently in 2013 forced evacuation of 20,000 Amhara people from Benshangule Gumeze is out of the most notable  ethnic cleansing and genocide crime against the same ethnic group identified in its 1976 manifesto   . Finally I concluded that the TPLF junta used any  means under the sun to retain their power  and continuing ehinic cleansing and  genocide crime against Amhara people in particular and the the rest of Ethiopians ingeneral regardless the prevailing situation..
Ref.http://tassew.files.wordpress.com/2011/07/tplf_manifesto_-_1968_e-c.pdf




ብአዴን ‹‹ሰለሞናዊ›› ስርወ መንግስት!? – (ሊያነቡት የሚገባ የአደባባይ ምስጢር)

Seyum Berket _Addisu

በአንድ ወቅት ዜጋ መጽሔት ላይ ታትሞ የነበረና ለግንዛቤዎ ይጠቅምዎታል ብለን እንደገና ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች አቅርበናል።  በአንዳንድ የአገዛዝ ሥርዓቶች በሀብት፣ በመደብ፣ ወይም ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ አልያም በዘር የተዋቀረ ሥርዓት ይኖራል… ለምሳሌ በአፄ ኃይለ ስላሴ ጊዜ የነበረው የስልጣን ፍልስፍና ከሰለሞን ስርዎ መንግስት የሚመዘዝ የዘር ሀረግ ባለቤት መሆንን ይጠይቅ እንደነበረ ሁላችንም የምናስታውሰው ነው፡፡ ከሰለሞን ስርዎ (Solomon Daynasty) መንግስት ውጭ ላሉና በዚያ የስልጣን ዘር ሀረግ ውስጥ ያሉ ሆነው በጉልበትም ይሁን በብልሃት ስልጣን ላጡት ስልጣን የሚሰጣቸው በጋብቻ ትስስር እንደነበረ ለማስታወስ የአፄ ኃይለስላሴ ልጆች ከማንና የት ተጋብተው እንደነበረ ማስታወሱ በቂ ምሳሌ ነው፡፡

 

የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ ከፍ ብዬ የጠቀስኩትን የታሪክና የንድፈ ሀሳብ ማነፃፀሪያ ይዘን የኢህአዴግ አባል ድርጅት ስለሆነው ብአዴን የስልጣን ድልድልና ከሕወሓት በሚሰጣቸው መመሪያ ድርጅቱን በሞኖፖል አንቀው የያዙትን ግለሰቦች የጋብቻ ትስስር፣ በትጥቅ ትግል ዘመን ጊዜ የነበራቸው ተሳትፎን እንዲሁም ዛሬ ያሉበትን ሁኔታ እንደሚከተለው ላቀርብ ተከታተሉ፡–
በክልል ሶስት በዋግ ህምራ ዞን ብርሃኔ አበራ ስለሚባሉ ባልቴት ታጋይ ነው የማወጋችሁ፡፡ ለስሙ የዋግህምራ ዞን ኃላፊ (ሊቀመንበር) ልጃለም ወልዴ ሆኑ እንጅ የዞኑ ህቡዕ መሪ ብርሃኔ አበራ ናቸው፡፡ ይታሰር ያሉት ይታሰራል፤ ይፈታ ያሉት ይፈታል፤ ይባረር ያሉት ሁሉ ከስልጣን ላይ ይባረራል፡፡
ወይዘሮ ብርሃኔ አበራ ለመሆኑ ይኀን ሁሉ ገበሬ ኩሉ ስልጣን ከየት አገኙት? የስልጣን ምንጫቸውን የጨበጡት ከዚህ ቀጥሎ ዝርዝራቸውን በማቀርባቸው ‹‹ታጋይ›› ልጆቻቸው፣ እህቶቻቸውና አማቾቻቸው ወዘተ ነው፡፡ የብርሃኔ አበራ ልጆች1. መዝሙር ፈንቴ የብአዴን ማ/ኮ አባል የነበረ አሁን የተባረረ፤
2. አሰፋ ፈንቴ፡- የበረከት ስምኦን ሚስት/ሲቭል ሰርቪስ ኮሌጅ የምትማር፤
3. ገነት ፈንቴ፡- አንድ የሕወሓት የደህንነት ባለስልጣን ያገባች፤
4. የሺሀረግ ፈንቴ
5. አሸናፊ ፈንቴ
6. መላኩ ፈንቴ
7. አበባ ፈንቴ፡- የሟቹ ሙሉአለም አበበ ሚስት የነበረች፤ በአገር ውስጥ ጉዳይ የኢሚግሬሽን ቪዛ ኃላፊ የነበረች፤ (የብርሃኔ አበራ እንጀራ ልጅ)
8. አለሚቱ ፈንቴ፡- በክልል ሶስት የምክር ቤት አባል የነበረች፤ አሁን እንግሊዝ አገር ያለች (የብርሃኔ አበራ የእንጀራ ልጅ)
9. ኃይሉ ፈንቴ፡- የጢጣ ት/ቤት አስተዳደር
10. አድና ፈንቴ (የተሰዋች) የወይዘሮ ብርሃኔ አበራ ታጋይ እህቶች1. የሺ አበራ የጄኔራል ኃይሌ ጥላሁን ሚስት፣ ጦር ኃይሎች ሆስፒታል በኃላፊነት ቦታ የምትሰራ፤
2. ነጻነት አበራ፡- የታደሰ ጥንቅሹ (ካሳ) ሚስት ክልል ሶስት በፕሮፖጋንዳ ክፍል ውስጥ የምትሰራ፤
የብራሃኔ አበራ ታጋይ የልጅ ልጆች
1. ውዲቱ አጋዡ፤- መከላከያ ውስጥ የነበረች፤
2. ፍሬህይወት አጋዡ፡- የኢህአዴግ ቢሮ ውስጥ ያለች፣ የውዲቱ አጋዡና የፍሬህይወት አጋዡ እናት የብርሃኔ አበራ ታላቋ ልጃቸው ዋርቃ ናት፡፡ የብርሃኔ አበራ የእህት ልጆች1. እንወይ ገብረመድህን የጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር (የአዲሱ ለገሰ ሚስት የነበረች)
2. ቢያድጎ፤
3. የዋግህምራ አቃቢ ህግ ሹም-ወይዘሮ እንወይ ገ/መድህን የአንድ ወንድ ልጅና የሁለት ሴት ልጆች እናት ናቸው፡፡ የወ/ሮ እንወይ ልጆች አባት አቶ ብርሃኑ ነጋሽ ዛሬ ነዋሪነታቸውን አሜሪካ አገር ያደረጉ ሲሆን፣ ከባለቤታቸው ጋር የተለያዩት ወ/ሮ እንወይ ገና ወደትግል ሜዳ ከመግባታቸው በፊት ነበር፡፡ ወ/ሮ እንወይ
የብርሃኔ አበራ ቤተሰብን በጋብቻ የተዛመደው ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ)
የብርሃኔ አበራ ቤተሰብን በጋብቻ የተዛመደው ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ)
ወደ ትግል ከገቡ በኋላ ከአቶ አዲሱ ለገሰ ጋር አንድ ወር ላልበለጠ ጊዜ ጋብቻ መስርተው ነበር፡፡ የአሁኗ የአዲሱ ለገሰ ሚስት የሰቆጣዋ ታምር ተሻለ ነች፡፡ ወ/ሮ እንወይ በአሁን ሰዓት ትዳር የላቸውም፡፡ ወ/ሮ እንወይ ትግሉን ሙሉ በሙሉ የተቀላቀሉት ከ1978 ዓ.ም ወዲህ ነው፡፡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ኢህዴን ወደ ብአዴን ከተለወጠ በኋላ ነው፡፡ ምንም እንኳ በበረሃው ዘመን የነበራቸው የፖለቲካ ንቃት የኢህዴን ማእከላዊ ኮሚቴ አባል ሊያደርጋቸው የሚችል የነበረ ቢሆንም፣ ኢህዴን ከሕወሓት የፖለቲካ ፕሮግራም የገለበጠውን ‹‹ፊውዳሊዝም አስፈጊ ጠላታችን በመሆኑ (Threa-tening enemy) በፕሮግራማችን ውስጥ መስፈር አለበት›› የሚለውን አመለካከት ወ/ሮ እንወይ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያ አብዮትና ደርግ ጠራርገው የጣሉት ስርዓት የሌለ ስለሆነ፣ ስለሌለ ፊውዳሊዝም መሰረታዊ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላት ነው ብሎ ፕሮግራማችን ውስጥ ማስፈር የለብንም›› የሚል አቋም ነበራቸው፡፡ ይህ አቋማቸው እንዲያውም የኢህአፓን ፕሮግራም ተከታይ አስብሏቸው ስለነበረ ነው በጣባው ኮንፍረንስ የኢህዴን ማ/ኮ አባል ሆነው ሳይመረጡ የቀሩት፡፡
4. ሌላኛዋ የብርሃኔ አበራ የአክስት ልጅ፡- የአቶ ታምራት ባለቤት ሁለት ልጆቿን አሜሪካ ይዛ የገባችው ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ ናት፡፡
የዚህ ቤተሰብ የእርስ በእርስ ግንኙነት ሁኔታ
በትጥቅ ትግሉ ዘመን ይህ ቤተሰብ እርስ በራሱ በጣም ይደጋገፍ ነበር፡፡ ከእንወይ ገ/መድህን በስተቀር እስከ 1983 እንወይ ገ/መድህን ከዚህ ቤተሰብ እንዲገለሉ ያደረጋት ታደሰ ጥንቅሹ ነበር፡፡ በ1975 ዓ.ም የኢህዴን የህቡዕ አባላት ተጋልጠው የህይወትና የአካል አደጋ ደርሶባቸው ነበር፡፡ ይህን የህቡዕ አባላት እንቅስቃሴ በጊዜው ይከታተለው የነበረው ታደሰ ጥንቅሹ ነበር፡፡ የእቡዕ አባሎቻችንን ያጋለጠችው እንወይ ነች ብሎ ስላስወራባት ነው እስከ 1983 በመጠኑም ቢሆን ከዚህ ቤተሰብ የተገለሉት፡፡
ሌላኛዋ የዚህ ቤተሰብ አባል ሆና ይኸን ያህል የጎላና እፍ እፍ የቤተሰብ ፍቅር ያልነበራት ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ ነች፡፡ እንዲያውም ወደመጨረሻው አካባቢ የአንድ ቤተሰብ አባል ሆነው በባሎቻቸው የስልጣን ከፍና ዝቅ ማለት፣ በአኗኗርና በአለባበስ በወ/ሮ ሙሉ ግርማይና በሌላው ቤተሰብ አባላት ከፍተኛ አለመግባባት ተከስቷል፡፡
አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ
አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ
ከዚህም በላይ አቶ ታምራት የግንቦት 20 ትምህርት ቤት ይማሩ በነበሩ የዚህ ቤተሰብ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ፈንጠዝያ ተፈጥሮ ነበር፡፡
ዘ-ሐበሻ ድረገጽን ሁልጊዜ ያንብቡ። በየሰዓቱ አዲስ ነገር አያጡም። በትጥቅ ትግሉ ወቅት የዚህ ቤተሰብ ተሳትፎና መስእዋትነትበመግቢያዬ የዘረዘርኳቸው የዚህን ቤተሰብ አባላት ዋና ዋናዎቹን ነው፤ እንጂ ጠቅላላ በብአዴን ውስጥ ያሉትን ኢህዴን ውስጥ የታገሉት በቁጥር 60 ናቸው፡፡ በትጥቅ ትግሉ ውስጥ የነበራቸውን ተሳትፎ በትክክል ማየት እንድንችል ከዚህ ቀጥዬ ስም ዝርዝራቸውን የማቀርብላችሁ በኢህአዴን ውስጥ እንደታጋይ ታቅፈው ጊዜው ይጠይቅ የነበረውን የትጥቅ ትግል ምላሽ ለመስጠት እንዲችሉ የወታደራዊ ስልጠና (ተአለም) ያልወሰዱትን ነው፡፡
1. እንወይ ገ/መድህን
2. ኃይሉ ፈንቴ
3. የሺሀረግ ፈንቴ
4. ገነት ፈንቴ
5. አሸናፊ ፈንቴ
6. አለሚቱ ፈንቴ
7. ብርሃኔ አበራ ከማስታውሳቸው የዚህ ቤተሰብ አባላት ከፊሎቹ ናቸው፡፡
ሁሉም ሰው መገንዘብ እንደሚችለው በአንድ የሽምቅ ውጊያ ስልታዊ ንቅናቄ ውስጥ የሚገኙ የድርጅት አባላት በሙሉ ትግሉ የሚጠይቀውን የወታደራዊ ስልጠና ወስደው ቢያንስ ራሳቸውን መከላከል በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መገኘት አለባቸው፡፡ ሙያና ምንም አይነት የመጀመሪያ ደረጃ የውጊያ እውቀት የሌለው ታጋይ ጠላት ኃይሉን አጠናክሮ ወደ ድርጅቱ ቤዝ አምባ ሊገባ በሚዘጋጅበት ጊዜ ከእቃ ጋር አብሮ መሸሽ ነበር የመጨረሻ እጣ ፈንታው፡፡ ይህ በደፈናው የሚቀርብ የንድፈ ሀሳብ ትንተና ሳይሆን ኢህዴን ውስጥ በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ ይህ ቤተሰብ በትጥቅ ትግሉ ዘመን መሽጎ የኖረው ጠላት ይደርስበታል ተብሎ በማይገመተው የኢህዴን ቤዝ አምባ ውስጥ ነው፡፡ የትጥቅ ትግሉ የሚጠይቀውን የውዴታ ግዴታ ይህ ቤተሰብ ሊፈፅም ባለመቻሉ በተለይ በ1978 አካባቢ በሌላው የድርጅቱ አባላትና ይኸን ቤተሰብ ጉያው ውስጥ በሸጎጠው የኢህዴን ማ/ኮ አባል መካከል ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡
በወቅቱ ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎች ይህ ቤተሰብ ለመስእዋትነት ዝግጁ አይደለም፤ የሌላውን የድሀ ገበሬ ልጅ ላብና ደም እየጋጠ መኖር የሚፈልግ ነው፤ የኢህዴን ማ/ኮ ለዚህ ቤተሰብ (የነማዘር ቤተሰብ) አባላት ልዩ እንክብካቤ ያደርጋል የሚሉ የሰላ ሂሶች ነበሩ፡፡
ከላይ ስለዚህ ቤተሰብ የገለፅኳቸውና ያነታርኩ የነበሩ ጥያቄዎች ምን ያክል ትክክል መሆናቸውን ለማየት ከ60 የቤተሰብ አባላት ውስጥ ስንቶቹ የህይወት፣ ስንቶቹ የአካል መስእዋትነት ከፈሉ የሚለው ጥያቄው በትክክል ይመልሰዋል፡፡ ከዚህ ቤተሰብ ውስጥ የህይወት መስእዋትነት የከፈለችው አድና (ታሪክ) ፈንቴ ብቻ ነች፡፡
በጥይት የቆሰሉ
1.ነፃነት (አምራየ) አበራ በ1977 ዓ.ም ቀስታ ውስጥ ልዩ ስሙ አቡነይ ጋራ በተባለ ቦታ በተካሄደ ውጊያ ዳሌዋ ላይ መጠነኛ የመቁሰል አደጋ የገጠማት ሲሆን በሌላ ውጊያ በጌምድር ክፍለ ሀገር ደጎማ ከተማ በተካሄደ ውጊያ ቀኝ እጇን በብርቱ ቆስላለች፡፡
2.መዝሙር ፈንቴ በ1977 ዓ.ም ዋግ አውራጃ ልዩ ስሙ ተላቁዝቁዛ ይገኝ ከነበረው የኢህዴን ቤዝ አምባ ከራሱ ከመዝሙር ፈንቴ ቤተሰብ ጥይት እግሩ ላይ የመቁሰል አደጋ ገጥሞታል፡፡ ሲጠቃለል ከስድስት ግለሰቦች ውጪ በዚህ ቤተሰብ ላይ የደረሰበት የአካልም ይሁን የህይወት መስእዋትነት የለም፡፡ ስለዚህ የኢህዴን አባላት ለዚህ ቤተሰብ መስእዋትነት ከፈሉ እንጂ ይህ ቤተሰብ ለኢህዴን የከፈለው መስእዋትነት ኢምነት ነው፡፡ እንዲያውም በደም ጎጆ በተገነባ ቤት ውስጥ ተንደላቀው ኖሩ እንጂ ስለነ ‹‹ማዘር›› (ብርሃኔ አበራ) ቤተሰብ ሲነሳ እኔም ጆሮ ዳባ ልበስ ብዬ የማሳልፈው ሀቅ አለ፡፡ የዚህ ቤተሰብ አንድ የእህል ወፍጮ ከቤተሰቡ በላይ እንዳገለገለ መርሳት እኔም የበላሁትን ቂጣ መካድ ይሆንብኛል፡፡
(ከዘ-ሐበሻ የተወሰደ )
maleda times | May 27, 2013 at 9:20 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1U6
Comment   See all comments