Tuesday, March 26, 2013

አቶ ሃይለማርያም ያላቸውን ሃይል ተጠቅመው የወሳኝነት ሚና እንዲጫወቱ ግፊት እየተደረገ ነው/ወያኔዎች ተደናግጠዋል!!

                  
Image

 BY 

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በተከፈተው በር ሰተት ብለው መግባት አለባቸው:: በወያኔ ውስጥ የተደረገውን የስልጣን ሽግሽግ ተከትሎ አዳዲስ ለውጦች እየታዩ ሲሆን የአቶ ሃይለማርያም የበላይነት ጎልቶ ለመውጣት እያቆበቆበ መሆኑን ከ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አከባቢ የተገኙ መረጃዎች ሲጠቁሙ ከአከባቢው የህወሃት አክራሪዎች መወገድ እና የአቶ ደብረጺሆን የግለኝነት አትኩሮት ለአቶ ሃይለማርያም እድሉን ገርበብ አድርጎ የከፈተላቸው ሲሆን የአቶ ደብረጺሆን ግለኝነት በሙስና ስም ሊደፈቅ እንደሚችል ያከባቢው ገማቾች ሲናገሩ ወታደራዊው አካል ራሱን ለማዳን ሲል በተጠንቀቅ ከሃይለማሪያም አዲስ ካበበው ቡድን ጋር እንደሚሰለፍ አንዳንድ ፍንጮች ታይተዋል:: አቶ ሃይለማርያም በሙሉ መንፈስ ባይሆኑም ድፍረት እንዳገኙ ከደቡብ ጉባዬ በሁዋላ እየታየ ሲሆን የደቡብ ባለስልጣናት አንድነት ወያኔን አስደንግጦታል::
የሕወሓት የቀድሞ ታጋዮች የአሁን ባለስልጣናት በአቶ ሃይለማርያም ዙሪያ ጥያቄ በማንሳት ላይ ቢሆኑን በባህር ዳር በተደረገው ጉባዬ ላይ ያላቸውን የበላይነት እንዲያሳዩ ከፓርቲያቸው ግፊት እንደተደረገባቸው ምንጮች ጠቁመዋል::የደቡብ ባለስልጣናት አብዛኛዎቹ በግል አቶ ሃይለማርያምን በደቡቡ ጉባዬ ወቅን አግኝተው ያናገሯቸው ሲሆን በአንድነት ራሳቸውን ችለው እንዲወጡ እና ከሕወሓት የበላይነት እንዲላቀቁ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው መክረዋል::ለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚረዳቸው ከወቅታዊ ጉዳዮች ጋር አስታከው ተወያይተውል::
በህወሓት ውስጥ ያለው ፍትጊያ በአባይ ወልዱ የበላይነት ያበቃ ነው ብለን መደምደም እንደማንችል እና መሃል ሰፋሪ ሆነው ወዳሸናፊው ለማዘንበል የግለኝነት ሚና እየተጫወቱ ያሉት ደብረጺሆን ደቡቦችን አመቻችቶ መያዝ አስፈላጊ እንደሆን ስለተረዱት በሃይለማርያም ድፍረት ጀርባ ሆነው ጨዋታውን ማጋጋል ተይይዘውታል::
ምንጮቹ በአከባቢያቸው ያለውን ሁኔታ በማየት እንዳሉት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በሃይለቃል ጭምር የሚደፋፈራቸው የደህንነት አማካሪው አለቃ ጸጋይ ከፓርቲው መነሳቱን ተከትሎ በደብረጺሆን ተዘዋዋሪ ቁጥጥር ስር መሆኑን ከጠ/ሚ ቢሮ የተገኙ መረጃዎች ሲጠቁሙ እንደት ከስልጣን እንደሚባረር ታቅዶለታል::
በስበሃት ነጋ የሚመራው ቡድን የቀድሞ ታጋይ የነበሩት እና በአሁን ሰአት በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች በማሰባሰብ በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ላይ ጥያቄዎችን እንዲያነሱ እና ከሕወሓት ሰው ጠፍቶ ነው ወይ ከደቡብ ለትግሉ አስታውጾ ያላበረከቱ ሰዎች የሚመሩን ነገ ስጋት ሆኖብናል የሚሉ ታጋዮች ይህን ፕሮፓጋንዳ ይዘው በአቶ ስበሃት በኩል መሰለፋቸው በዚህ ሰሞን እንደገና ተረጋግቷል የተባለውን የወያኔ ክፍፍል እንደ አዲስ አግሎታል::
የሃይለማርያም ስልጣን መያዝ ያልጣማቸው አክራሪ ሕወሓቶች ከባህር ዳር መልስ አዲስ አበባ ውስጥ በስበሃት ነጋ ሰብሳቢነት  አርከበ እቁባይ ;ብርሃነ ገብረክርስቶስ ;አዲሳለም ባሌማ;አባዲ ዘሙ ;አለቃ ጸጋይ በርሄ; ቅዱሳን ነጋ; ሃይለኪሮስ እና ሌሎችም ተሰባሰበው በህወሃት ውስጥ ስለለው ሁኔታ እና ራሳችን በፈጠርናቸው ደቡቦች ልንዋጥ ነው የሚል እደምታ ያለው ውይይት አካሂደው ነበር:;
በአንድ ወገን ሆነው በአባይ ወልዱ መሪነት ብኣዴንን አስከትለው የስብሃትን ቡድን እየተዋጉ የሚገኙት አዜብ መስፍን እና ሌሎች..ሳሞራ የኑስን እንደመከታ አድርገው ቢተሙም ሳሞራ ሁኔታዎችን ከመከታተል ዉች ተሳትፎው የተልፈሰፈሰ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል::
የደቡብ ባለስልጣናት ወይም በስበሃት አጠራር የከተማ ጮሌዎች ወደ ከፍተኛ የስልጣን እርከን መምጣታቸው እያንገበገባቸው ሲሆን መለስ ዜናዊ ላልሰለጠኑ አናሳ ብሄሮች ሸጠን በማለት በሟቹ ላይ ከንፈር ነክሰው እየሞገቱ ሲሆን ይህም አልበቃ ብሎ ከድርጅታችንን መመሪያ እና ደንብ ዉጭ በተለያየ ቦታ የመለስን ምስል ማየት ሰለቸን በሚል ምስሉ እንዲነሳ ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል ምናልባት ሁኔታዎችን ያረግብ ይሆናል በሚል አቶ አዲሱ ምስሉ እንዲነሳ ቢናገሩም አቶ በረከት ጠላት እና ወዳጅን አጥርቶ ለመለየት በሚል እንዲቆይ አድርገዋል..
የስበሃት ቡድን ዉስጥ ውስጡን በትግራይ ለሚገኙ የሕወሓት የበታች አመራሮች እንዲሁም በሰራዊቱ ውስጥ ለሚገኙ የህወሓት መኮንኖች በሚያሰራጩት ፕሮፓጋንዳ በበረሃ ወንድም እና እህት ታጋዮችን ሰውተን ደማችንን አፍሠን የልጅነት ወዛችንን ጨርሰን ለዚህ የደረስነው ለደቡብ  ሰዎች እና ለከተማ ጮሌዎች ስልጣን ለመስጠት አይደለም አብረውን የታገሉ ኦሆዴዶች እንኳን ያላገኙትን ስልጣን ነው ያገኙት በማለት እና ለነገ የፖለቲካ ኪሳራ ያመጡብናል የሚያዘነብሉት ወደ ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ነው ለኛ አደጋ ስለሆኑ ከአሁኑ ልናሶግዳቸው ይገባል   በማለታቸው የወያኔ የውስጥ ቀውስ ግሎ ይገኛል::
በአሁን ሰኣት የደህንነት መዋቅሩን እና የጦር ሰራዊቱ ባለስልጣናት አጣብቂኝ ውስጥ ለማስገባት እየሰሩ የሚገኙት ደብረጺሆን አቶ ሃይለማርያም ያላቸውን ሃይል ተጠቅመው የወሳኝነት ሚና እንዲጫወቱ እያደፋፈሯቸው ሲሆን ከጎናቸው እንደሚሆኑ እና ምንም እንደማይመጣ እየመከሯቸው ሲሆን ለሁለት አመት ነው ያስቀመጥንህ የሚለውን የአለቃ ጸጋይ ዛቻ ከአሁን በኋላ ሰሚ የሌለው ጩሀት እንደሆነ መናገራቸውን ምንጮቹ አስቀምጠዋል::
የደቡብ ባለስልጣናት ማሰብ/ድፍረት መጀመር; የህወሃት ክፍፍል መጋል; የኦህዲድ አህያዊ ሞኝነት; የብኣዴን በዝምታ ነገሮችን መከታተል; የኢሕኣዴግ ባልተጠበቀ መልኩ ቀውስ ውስጥ መግባት እና ሌሎች ተደማምረው የወያኔን ውድቀት የሚያመላክቱ ሲሆን በሃገሪቷ ላይ የፖለቲካ ለውጥ እንዲኖር ለማየት የሚጓጓውን ህዝብ ስል ነቀል ለውጥ እንዲያደርግ መስራት ደሞ የእያንዳንዳችን ሃላፊነት ነው::
staff reporter | March 26, 2013 at 2:31 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1D0
Comment   See 

                       

Friday, March 22, 2013

World Bank told to investigate links to Ethiopia ‘villagisation’ project

Grass roofed house for the forced displaced

  


William Lloyd George in Addis Ababa, guardian.co.uk

An independent panel has called for an investigation into a World Bank-funded project in Ethiopia following accusations from refugees that the bank is funding a programme that forced people off their land.

In a report, seen by the Guardian, the inspection panel – the World Bank’s independent accountability mechanism – calls for an investigation into complaints made by refugees from the Anuak indigenous group from Gambella, western Ethiopia, in relation to the bank’s policies and procedures.

The refugees claim the Protection of Basic Services (PBS) programme funded by the bank and the UK Department for International Development (DfID), is contributing directly to the Ethiopian government’s “villagisation” programme, introduced in 2010. The programme seeks to move people to new villages, but residents say this is done with little consultation or compensation, and that these sites lack adequate facilities.

In a letter sent to the panel in September, the refugees say some people have been forcibly relocated from their land, which is now being leased to foreign investors.

“These mass evictions have been carried out under the pretext of providing better services and improving the livelihoods of the communities,” says the letter. “However, once they moved to the new sites, they found not only infertile land, but also no schools, clinics, wells or other basic services.”

It says the government forced them to abandon their crops just before harvest, and they were not given any food assistance during the move. “Those farmers who refused to implement the programme … have been targeted with arrest, beating, torture and killing,” the letter says.

The refugees say they “have all been severely harmed by the World Bank-financed [project], which is contributing directly to the Ethiopian government’s villagisation programme in Gambella region”.

The letter says Ethiopian government workers, whose salaries are paid for through the PBS programme, have been forced to implement villagisation.

DfID has been criticised for failing to address abuse allegations in the South Omo region of Ethiopia, where residents told DfID and USAid officials of their experiences.

DfID is also embroiled in a legal action over its links to the villagisation programme. An Ethiopian farmer claims he was forcibly evicted from his farm. His lawyers, Leigh Day & Co, say DfID money is linked to these abuses through PBS funding in Gambella. DfID has said it is responding to the legal concerns and reviewing the allegations of rights abuses in Ethiopia.

In its report, the panel says that although the World Bank management denies links between villagisation and the PBS programme, the two are attempting to achieve the same things. “[Villagisation] is a programme that aims at fundamentally restructuring settlement patterns, service infrastructure and livelihoods, including farming systems, in the Gambella region, and as such constitutes a significant context in which PBS operates. In this sense from a development perspective, the two programmes depend on each other, and may mutually influence the results of the other,” says the panel report.

The panel says there are “conflicting assertions and differing views” on links between PBS and villagisation, the complaints by the refugees and the bank’s adherence to its policies and procedures, which could adequately be addressed through an investigation.

In a response to the refugees’ letter, the World Bank denied all links between the PBS and villagisation. It said it had not encountered any evidence of human rights abuses. It did admit the new sites “were not desirable”, but said the Ethiopian government had asked for assistance to improve them.

According to David Pred, founder of Inclusive Development Internationalwho helped the Anuak file their complaint, the PBS is funding the majority of government departments responsible for implementing the villagisation programme. “It provides both the means and the justification for villagisation,” said Pred.

The World Bank has been supporting the PBS programme since May 2006 with a commitment of more than $2bn. The bank’s board was scheduled to meet on Tuesday to discuss the panel’s report, but the meeting was postponed.

Human Rights Watch says many of the communities affected by villagisation have not been properly consulted about resettlement. It has interviewed several refugees from the region who reported that government officials have responded with violence and arbitrary detention when people have not agreed to relocate.

“The World Bank’s president and board need to let the inspection panel do its job and answer the critical questions that have been raised by Ethiopians affected by this project,” said Jessica Evans, senior international financial institutions advocate at Human Rights Watch. “If the World Bank doesn’t support this investigation, its Ethiopia programme will continue to be shadowed by controversy.”

The chairman of the UK parliament’s international development committee, Sir Malcolm Bruce, said the allegations against villagisation are unsubstantiated. Bruce, who visited Ethiopia last week, said the UK programme “is delivering a very good result”.

• This article was amended on 20 March 2013. Gambella is in western Ethiopia, not eastern as we originally said

ከጠቅላይ ፍ/ቤት እስከ ሚንስትሮች ም/ቤት

                  
Gudu  Kassa
መጋቢት 18/2005 ዓ.ም የእነ እስክንድር ነጋ ይግባኝ ለመጨረሻ ጊዜ ተብሎ ተቀጥሯል፡፡ በዚህ መዝገብ የተከሰሱት የህሊና እስረኞች ይግባኝ ከጠየቁ አምስት ወር አልፏቸዋል፡፡ 
ለምን? …በአዲስ መስመር እንነጋገርበት፡፡
የይግባኙን ውሳኔ ያዘገየው የፖለቲካ ተንታኝ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የተከሰሰው በሀሰት ስለሆነ ነው፡፡ በእርግጥ ይህንን ያልኩት እኔ አይደለሁም፤ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የመሀል ዳኛ የሆነው አቶ አማረ አሞኘ ነው፡፡ ባለፈው ወር ዳኛው አቃቢ ህጎቹን ሰበሰበና እንዲህ አላቸው፡-
‹‹ይህን ሰው አሻባሪ ነው ብላችሁ ስትከሱት ያቀረባችሁት ማሰረጃ በተለያየ ጊዜ የፃፈውን ፅሆፎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና በአንድ የፖለቲካ ፓርቲ መድርክ ላይ ተናገረው ያላችሁትን ብቻ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ ፅሁፉና ንግግሩ ያስከተለው አደጋ አልተገለፀም፤ ወይም ምንም አይነት አደጋ አላስከተለም ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተከሳሹ ላይ ቅጣት ለመጣል አያስችልም፡፡ ስለዚህም ሌላ ጥፋተኝነቱን የሚያረጋግጥ ማሰራጃ ካላችሁ አቅርቡ? አሊያም በሚቀጥለው ቀጠሮ ሲቀርብ በነፃ እለቀዋለሁ፡፡››
አቃቢ ህጎቹ ምንም ማስረጃ አልነበራቸውምና በደፈናው ‹‹ሰውየው አሸባሪ ስለሆነ ዝም ብለህ፤ ይግባኙን ውድቅ አድርግና የከፍተኛው ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አፅናበት›› የሚል ይዘት ያለው ተመሳሳይ አቋም አንፀባረቁ፡፡ ዳኛው ምን አይነት መንፈሳዊ ኃይል ተጭኖበት እንደ ሆነ እንጃ! ‹‹በፍፁም ከህግ ውጪ አልሰራም፤ ህሊና አለኝ›› ብሎ ፍንክች ያባ ቢለዋ ልጅ ይላል፡፡
ይህን ጊዜም ነገሩ ቦግ ያደረገው አንድ አቃቢ ህግ
‹‹አንተ እስክንድርን እለቃለሁ የምትለው ያገርህ ልጅ ጎንደሬ ስለሆነ ነው!››
ይለዋል ቁጣ በተቀላቀለበት ድምፅ፡፡ ዳኛ አማረም ይበልጥ ተናዶ
‹‹እኔ እሰከ ዛሬ ድረስ ያገለገልኩት ሀገሬን ኢትዮጵያ እንጂ የትውልድ መንደሬን አይደለለም፡፡ ደግሞም ዘረኝነት የለብኝም›› ሲል መለሰለት፡፡
በእንዲህ አይነት ሁኔቴ መዋዘገቡ በመካረሩ መግባባት አልቻሉምና ጉዳዩ ሚንስትሮች ምክር ቤት ደረሰ፡፡ በሚንስትሮች ም/ቤትም ስብሰባውን የመራው ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ደመቀ መኮንን ሲሆን፣ ዳኛውም አብሮ ቀርቧል፡፡ አቶ ደመቀ መጀመሪያ ዳኛው ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠየቀ፡፡ ዳኛውም ስለክሱ አጠር አድርጎ ካብራራ በኋላ እንዲህ ሲል ደመደመ፡-
‹‹እስክንድር ነጋን ‹አሸባሪ› ብሎ ለመፍረድ የሚያስችል በቂ ማስረጃ ስላልቀረበ በሚቀጥለው ቀጠሮ በነፃ አሰናብተዋለሁ፤ እንዲህ ማድረግ አትችልም የምትሉኝ ከሆነ ግን ክቡራን ሚንስትሮች በዕለቱ በችሎት ለመሰየም ፍቃደኛ አለመሆኔን በትህትና ትረዱኛላችሁ ብዬ አስባለሁ!››
ከዚህ በኋላ ሚኒስትሮቹ መወያየት ጀመሩ፡፡ ተከራከሩ፤ በመጨረሻም አቶ ደመቀ እንዲህ አለ፡-
‹‹እኔም ከአቶ አማረ ጋር እስማማለሁ፡፡ ምክንያቱም በዚህ ሰውዬ /እስክንድር/ የተነሳ ከፍተኛ አለም አቀፍ ጫና እየደረሰብን ነው፡፡ ስለዚህም ብንፈታው ተጠቃሚዎቹ እኛው ነን ብዬ አስባለሁ፡፡››
አንድ ሚኒስትር ቀጠለ፡-
‹‹በመሰረተ ሃሳቡ ላይ እስማማለሁ፡፡ ነገር ግን እስከዛሬ አስረነው ‹ነፃ ነህ› ብለን ብንለቀው የፖለቲካ ኪሳራ ስልሚያስከትልብን፣ ከፍርዱ ላይ ቅንስናሽ አድርገን ይቅርታ ጠይቆ እንዲወጣ ብናደርግ የተሻለ ነው፡፡››
ሌላ ሚኒስትር ቀጠለ፡-
‹‹እስክንድርን እኔ አውቀዋለሁ፤ የአሜሪካን ሀገር መኖሪያ ፍቃድ እና ብዙ ሀብት እያለው እዚህ ነገር ውስጥ የገባ ሰው ነው፡፡ እናም በፍፁም ይቅርታ ለመጠየቅ ፍቃደኛ አይሆንም››
ሌላኛው ሚንስትር ቀጠለ፡-
‹‹ኧረ ለመሆኑ መለስ አለም አቀፍ ጫና እንደሚያስከትል እያወቀ ለፓርቲያችን ጥቅም ብሎ የገባበትን ጉዳይ፣ ዛሬ እርሱ አልፏል ብለን ጫና ይምንፈራበት ምክንያት ከየት የመጣ ነው? በቃ! መለስ አደገኛ ሰው ነው ብሎ አስሮቷል፡፡ አለቃ! እዛው ይበስብስ!››
የሚንስትሮች ምክር ቤትም ቢዚህ ጉዳይ ላይ መስማማት ሳይችል በመቅረቱ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዘዳንት አቶ ተገኔ ቀርቦ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ቀጠሮ ይዘው ተለያዩ፡፡
…በእርግጥ ከአቶ ተገኔ ማብራሪያ በኋላ የሚኒስትሮች ም/ቤት ምን አይነት አቋም ላይ እንደደረሰ ለማወቅ ያደረኩት ጥረት ሊሳካ አልቻለም፡፡ መረጃውንም እስከ ዛሬ ያቆየሁት ለዚህ ነበር፡፡ አሁን ግን የቀጠሮ ቀን ሰለደረሰ ልነግራችሁ ተገደድኩ፡፡
እናም የፊታችን ረዕቡ ከጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሚከተሉት አራት ነገሮች አንዱን እናያለን ብዬ አስባለሁ፡፡
1. የሚንስትሮች ም/ቤት ጫናው ስለከበደው በነፃ ይለቀዋል፣
2. መለስ እያወቀ የገባበትን ጫና አንፈራም! (ራዕዩ እናስቀጥላለን እንደማለት ነው) በማለት የከፍተኛውን ፍርድ ቤት ውሳኔ ያፀናሉ፣
3. ከተፈረደበት 18 ዓመት ላይ ቅንስናሽ አድርገው፣ ይቅርታ እንዲጠይቅ ወደ ማግባባቱ ይሄዳሉ፣
4. ዳኛው አሞኘ እንደፎከረው ከችሎቱ ይቀርና አሁንም ‹‹የመጨረሻ›› ቀጠሮ ይሰጣል፡፡
የሆነ ሆኖ እንዲህ የሚል አንድ እውነት ‹‹በመሪዎቻችን›› ግንባር ላይ ተቸክችኳል፡፡ ‹‹ሲቪሉ ጀግና እስክንድር ነጋ እያርበደበደው ነው!››
አዎ! እኔም እላለሁ፣ የእስክንድር እና መሰሎቹ የግፍ እስር አርብድብዶ ብቻ አይተዋችሁም!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ! ውድቀት ለአምባገነኖች!!
staff reporter | March 22, 2013 at 3:16 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1Bu
Comment   See

                         

Thursday, March 21, 2013

የወያኔ ኢህአዴግ አባል ድርጅቶች አዲስ የመረጧቸው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስም ዝርዝር ይዘናል ይመልከቱ

 
                   

ባሳለፍነው ሳምንት በምርጫ ተወጥሮ የነበረው ወያኔ ዛሬ ቁርጡ ታውቆ የመረጣቸውን አመራር አባላቶች አሳውቆል  ከሑሉም ኣጛር ድርጅቶች የተውጣጡ ኣባላጦጭኝ ያቀረበ ሲሆን፡ከህወሃት ከኦህዴድ ብአዴን እና ደቡብ ህዝቦች የተመረጡት አጠቃላይ ስምዝርዝራቸውን ማለዳ ታይምስ ይዞት የቀረበ ሲሆን አዘብ መስፍን በሶስተኛ ደረጃ ላይ የኢሃዴግ ተመራጭ በመሆን የፍራቻዋን መንፈስ አለምልማለች አጠቃላይ ለስም ዝርዝራቸው ከስር ይመልከቱ መልካም ቆይታ ።ከማለዳ ታይምስ ጋር


የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/ህወሓት/ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነው የተመረጡ
1. ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል
2. አቶ አባይ ወልዱ
3. ወ/ሮ አዜብ መስፍን
4. አቶ አባይ ፅሃየ
5. ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም
6. ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር
7. አቶ በየነ መክሩ
8. አቶ ኪሮስ ቢተው
9. አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ
10. አቶ ሚኬኤለ አብርሃ
11. ወ/ሮ ሮማን ገብረስላሴ
12. ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ
13. አቶ አለም ገብረዋህድ
14. አቶ ጎበዛይ ወልደአረጋይ
15. ወ/ሮ አረጋሽ በየነ
16. ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
17. አቶ ጌታቸው አስፋ
18. አቶ ቴድሮስ ሀጎስ
19. አቶ ሀጎስ ጎደፋይ
20 አቶ ዳንኤል አሰፋ
21. አቶ ኢሳያስ ወልደጊወርጊስ
22. አቶ አባዲ ዘሙ
23. አቶ ገብረመስቀል ታረቀ
24. አቶ ተክለወይኒ አሰፋ
25. አቶ ነጋ በርሀ
26. ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማርያም
27. ወ/ሮ ቅዱሳን ነጋ
28. አቶ ሓዲሽ ዘነበ
29. አቶ ተስፋአለም ይህደጎ
30. አቶ ተወልደ ገብረፃዲቅ
31. አቶ ይትባረክ አምሃ
32. አቶ እያሱ ተስፋይ
33. አቶ ብርሃነ ኪዳነማርያም
34. አቶ ፀጋይ በርሃ
35. ወ/ሮ ያለም ፀጋይ
36. ዶ/ር ክንደያ ገብርሂወት
37. አቶ ጥላሁን ታረቀኝ
38. አቶ ተወልደ በርሀ
39. አቶ ብርሃነ ፅጋብ
40. አቶ ሃይለ አስፋሃ
41. ወ/ሮ ኪይሪያ ኢብርሃም
42. አቶ ጎይቶአም ይብርሃ
43. አቶ ሀፍቱ ሀዱሽ
44. አቶ ተወልደብርሃን ተስፋአለም
45. ዶ/ር ገብርሂወት ገብረእግዚአብሄር
 
የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆነው የተመረጡ ስም ዝርዝር
 
1.አቶ አዲሱ ለገሰ
2.አቶ በረከት ስምኦን
3.አቶ አያሌው ጎበዜ
4.አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
5.አቶ ደመቀ መኮንን
6.አቶ አለምነው መኮንን
7.አቶ ካሳ ተክለብርሃን
8.አቶ ህላዊ ዮሴፍ
9.አቶ ተፈራ ደርበው
10.አቶ ታደሰ ካሳ
11.አቶ ብናልፍ አንዷለም
12.አቶ መላኩ ፈንታ
13.አቶ ከበደ ጫኔ
14.ወይዘሮ ዘነቡ ታደሰ
15.ዶክተር አምባቸው መኮንን
16.አቶ ፈንታ ደጀን
17.አቶ ጌታቸው አምባየ
18.ዶክተር ምስራቅ መኮንን
19.ዶክተር ይናገር ደሴ
20.አቶ ለገሰ ቱሉ
21.ወይዘሮ ዝማም አሰፋ
22.ወይዘሮ ብስራት ጋሻው ጠና
23.ወይዘሮ ሽታየ ምናለ
24.ወይዘሮ ወለላ መብራቴ
25.አቶ ፀጋ አራጌ
26.ዶክተር ስንታየሁ ወልደሚካኤል
27.አቶ ዮሴፍ ረታ
28.ዶክተር አምላኩ አስረስ
29.አቶ መለሰ ጥላሁን
30.አቶ መኮንን የለውምወሰን
31. አቶ ገለታ ስዩም
32. ወይዘሮ ፍሬህይወት አያሌው
33. ዶክተር ፋንታሁን መንግስቴ
34. አቶ እሸቴ አስፋው
35. ወይዘሮ ገነት ገብረእግዚአብሄር
36. አቶ ፍስሃ ወልደሰንበት
37. አቶ ግዛት አብዩ
38. አቶ ምግባሩ ከበደ
39. አቶ ጌታቸው ጀምበር
40. አቶ መሃመድ አብዱ
41. አቶ ባዘዘው ጫኔ
42. አቶ እዘዝ ዋሴ
43. አቶ አየነው በላይ
44. አቶ ብርሃን ሃይሉ
45. ወይዘሮ ምስራቅ ማሞ
46. ወይዘሮ አበራሽ ታደሰ
47. ወይዘሮ ወርቅሰው ማሞ
48. አቶ አህመድ አብተው
49. አቶ ደሳለኝ አምባው
50. አቶ አለባቸው የሱፍ
51. አቶ ተስፋየ ጌታቸው
52. ወይዘሮ ነጻነት አበራ
53. ወይዘሮ አበባ የሱፍ
54. አቶ ንጉሱ ጥላሁን
55. አቶ ይልማ ወርቁ
56. አቶ ዘለቀ ንጉሱ
57. አቶ ያለው አባተ
58. አቶ አባተ ስጦታው
59. አቶ ደሳለኝ ወዳጀ
60. አቶ ጌታቸው ሃይለማርያም
61. አቶ ከበደ ይማም
62. ወይዘሮ ውባለም እሰከዚያ
63. አቶ ደስታ ተስፋው
64. አቶ ስዩም መኮንን
65 አቶ ጌታቸው መንግስቴ
 
 
የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/
 
1/ አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ
2/ አቶ ሙክታር ከድር
3/ ሀብታሙ ሀይለሚካኤል
4/ አቶ በዙ ዋቅቤካ
5/ ወ/ሮ አስቴር ማሞ
6/ አቶ አብዱልቃድር ሁሴን
7/ አቶ ሲሳይ ሁሪሳ
8/ አቶ ኑሬ ቀመር
9/ አቶ ሰለሞን ቁጩ
10/ አቶ ተፈሪ ጢያሮ
11/ አቶ ጌታቸው ባልቻ
12/ አቶ ኩማ ደመቅሳ
13/ አቶ ለቺሳ አዩ
14/ አቶ ጆስፔ ሲማ
15/ አቶ አበራ አየለ
16/ አቶ አባዱላ ገመዳ
17/ አቶ ወርቅነህ ገበየሁ
18/ አቶ አልዬ ዑመር
19 / አቶ ተስፋዬ ቱሉ
20/ አቶ ዑመር ሁሴን
21/ አቶ ሻፊ ዑመር
22/ አቶ አብይ አህመድ
23/ አቶ ፈይሳ አሰፋ
24/ አቶ ሙስጠፋ ከድር
25/ አቶ ነጋ ሞሮዳ
26/ አቶ ሞቱማ መቃሳ
27/ አቶ ሰለሞን አበበ
28/ አምባሳደር ግርማ ብሩ
29/ አቶ ኢብራሂም ሃጂ
30/ አቶ ዳባ ደበሌ
31/ አቶ ረጋሳ ከፍአለ
32/ አቶ ሱፊያን አህመድ
33/ አቶ ድሪባ ኩማ
34./ ወ/ሮ ደሚቱ ሃምቢሳ
35/ አቶ ዘላለም ጀማነህ
36/ አቶ ደዋኖ ከድር
37/ አቶ ዘውዴ ቀፀላ
38/ አቶ አብዱልአዚዝ መሀመድ
39/ አቶ ሰማን አባጎጃም
40/ አቶ ሞሾ ኦላና
41/ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ
42/ ወ/ሮ ራብያ ኢሳ
43/ ወ/ሮ ፎዚያ አማን
44/ ወ/ሮ ሮዛ ዑመር
45/ ወ/ሮ ሎሚ በዶ
46/ አቶ ጌቱ ወየሳ
47/ አቶ እሸቱ ደሴ
48/ አቶ ፈቃዱ ተሰማ
49/ አቶ ገዳ ሮቤ
50/ አቶ ታምራት ጥበቡ
51/ አቶ ሞገስ ኤዴኤ
52/ አቶ ፈይሰል አልዬ
53/ አቶ ደምሴ ሽቶ
54/ አቶ ለማ  መገርሳ
55/ ወ/ሮ ሰዓዳ ከድር
56/ አቶ በከር ሻሌ
57/ አቶ አህመድ ቱሳ
58/ አቶ አበራ ሀይሉ
59/ አቶ አህመድ ሙሀመድ
60/ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው
61/ ዶ/ር ካባ ኦርጌሳ
62/ አቶ ስለሺ ጌታሁን
62/ ዶ/ር ምትኩ ቴሶ
63/ አቶ ሻሎ ዳባ
64/ አቶ አብረሃም አዱላ
65/ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ
66/ አቶ ሽፈራው ጃርሶ
67/ አቶ አሊ ሲራጅ
68/ አምባሳደር ጊፍቲ አባሲያ
69/ አቶ ጫላ ሆርዶፋ
70/ አምባሳደር ደግፌ ቡላ
71/ አቶ ኤቢሳ ዲንቃ
72/ አቶ ኢተፋ ቶላ
73/ አቶ ጌታቸው በዳኔ
74/ አቶ ቶሎሳ ገደፋ
75/ ፕሮፌሰር ፈቃዱ በየነ
76/ አቶ ከፍያለው አያና
77/ ዶክተር ግርማ አመንቴ
78/ አቶ መሀመድ ጅሎ
79/ ወይዘሮ ብሌን አስራት
80/ ዶክተር መሀመድ ሀሰን
 
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ስም ዝርዝር
 
1. አቶ አለማየሁ አሰፋ
2. አቶ ሙደር ሰማ
3. አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ
4. አቶ ሽፈራው ሽጉጤ
5. አቶ ሃይለብርሃን ዜና
6. አቶ ሬድዋን ዜና
7. አቶ መኩሪያ ሃይሌ
8. ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል
9. አቶ ሳኒ ረዲ
10. አቶ ታገሰ ጫፎ
11. አቶ ተስፋየ በልጅጌ
12. አቶ መለሰ አለሙ
13. አቶ ሲራጅ ፈጌሳ
14. ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ
15. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
16. ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም
17. አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ
18. አቶ ምትኩ በድሩ
19. አቶ ካይዳኪ ገዛኸኝ
20. አቶ ደበበ አበራ
21. አቶ ደሴ ዳልኬ
22. አቶ ክፍሌ ገብረማርያም
23. አቶ አስፋው ዲንጋሞ
24. አቶ ተክለወልድ አጥናፉ
25. አቶ ኑረዲን ሃሰን
26. አቶ ማቲዎስ አኒዮ
27. አቶ ጥላሁን ከበደ
28. ወይዘሮ ብዙነሽ መሰረት
29. አቶ ኢዮብ ዋኬ
30. ወይዘሮ አልማዝ በየሮ
31. አቶ ሁሴን ኑረዲን
32. አቶ ያዕቆብ ያላ
33. ዶክተር መብራቱ ገብረማርያም
34. አቶ ይገለጡ አብዛ
35. አቶ አባስ መሃመድ
36. አቶ ሞሎካ ውብነህ
37. አቶ ዮናስ ዮሴፍ
38. አቶ ዴላሞ ኦቶሮ
39. ወይዘሮ አበባየሁ ታደሰ
40. አቶ ታገሰ ኤሮሞ
41. አቶ ተመስገን ጥላሁን
42. አምባሳደር ተሾመ ቶጋ
43. አቶ ቃሬ ጫዊቻ
44. ወይዘሮ አስቴር ዳዊት
45. ወይዘሮ መሰረት መስቀሌ
46. አቶ ሞገስ ባልቻ
47. አቶ መሃመድ አህመድ
48. አቶ ተስፋየ ይገዙ
49. ዶክተር ዘሪሁን ከበደ
50.አቶ ገሌቦ ጎልቶሞ
51. አቶ አማኑኤል አብርሃም
52. አቶ ሰማን ሽፋ
53. አቶ ሰለሞን ተስፋየ
54. አቶ ወዶ አዶ
55. አቶ ደረጀ ዳኬጉቾ
56. አቶ አሰፋ አብዮ
57. ወይዘሮ ህይዎት ሃይሉ
58. አቶ ወንድሙ ገዛኸኝ
59. አቶ ዘሪሁን ዘውዴ
60. አቶ አድማሱ አንጎ
61.ወይዘሮ ከፈለች ደንቦባ
62. አምባሳደር ለኢላ አለም
63. አቶ ገብረመስቀል ጫላ
64. አቶ ዳመነ ዳሮታ
65. ዶክተር ካሱ ኢላላ
 
staff reporter | March 21, 2013 at 9:14 am | Categories: AFRICA WIRE | URL: http://wp.me/p2gxmh-1AT
Comment   See

                      

Tuesday, March 19, 2013

ነብዩ ኤልያስ በአራት ኪሎ”በ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከ አዲስ ጉዳይ መጽሔት


ተዋናይት ጀማነሽ ሰለሞን የካቲት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ለአዲስ ጉዳይ መጽሔትና ለሌሎች ሚዲያዎች በበተነችው ጥሪ “የኢትዮጵያ ትንሳኤ ሊያረጋግጥ ኃያል ባለስልጣን ቅዱስ ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቷል”ብላለች፡፡ ጀማነሽ “ይህንን እጅግ ታላቅ አስፈሪና ጥልቅ ሃይማኖታዊ ምስጥር በተመለከተ ትንታኔና ትምህርት የሚሰጥበት ጉባኤ ከጽዋ ማኅበሬ ጋር በመሆን አዘጋጅቻለሁና በኢግዚቢሽን ማዕከል ተገኝታችሁ ተካፈሉልኝ” በማለት ነው ግብዣውን የላችው፡፡ በግዕዝ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ በተጻፈውና ማኅበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ .. ብሎ የሚጀምረው  የጽዋ ማኅበሯ አማካኝነት በበተነችው ጥሪዋ “በጉባኤው የኢትዮጵያ ትንሳኤ ይታወጃል” ብላለች፡፡ የተለያዩ አርቲስቶችና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች እየተሳተፉበት መሆኑ የሚነገረው በዚህ ጉባኤ ላይ  የተለያዩ ወገኖች ጥያቄ በማንሳት ላይ ይገኛሉ፡፡በብዙዎች ዘንድ ይህ እንቅስቃሴ ከዚህ ቀደም ተሐድሶ በሚል ስያሜ እንደተካሄደው ዓይነት በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ጥላ ስር አዲስ ሃይማኖት ፤ አዲስ አስተምህሮ የመመስረት አላማ ያለው ነው የሚል አስተያየት እየተሰነዘረበት ነው፡፡ ለመሆኑ ይህ “ተዋሕዶ” የሚል ስያሜ በመካሄድ ላይ ያለው እንቅስቃሴ ከኦርቶዶክስ እምነት አንጻር ምን ያህል ተቀባይነት አለው? የነብዩ ኤልያስ ወደ ኢትዮጵያ መምጣትስ ምን ያህል ተዓማኒ ነው? የዚህ እንቅስቃሴ መሰረታዊ ባህርያት ምን ምን ናቸው? እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎች እንዲመልስን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን  የእምነት መሰረቶችና ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ጋር የተያያዙ በርካታ መጽሀፍት ደራሲ የሆነው ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ጋብዘናል፡፡
ዲ/ን ዳንኤል ከላይ ያነሳናቸውን ጥያቄዎች ተንተርሶ በላከልን ጽሁፍ በርካታ ጉዳዮችን ይዳስሳል፡፡ “ነብዩ ኤልያስ ወደ ኢትዮጵያ መጥቷል የሚለው” ጉዳይን በመሰረቱ በመፈተሸ ሃይማኖታዊ ትንታኔ ሰጥቶበታል፡፡
ሰሞኑን በከተማችን አዲስ አበባ “ነብዩ ኤልያስ መጥቷል ፤ የአለም ፍጻሜ ቀርቧል”  የሚሉ አካላት ተነስተዋል፡፡ እነሱ እንደሚሉት ነብዩ ኤልያስ መጥቶ አዲስ አበባ ይገኛል፡፡ ቤተመንግሥቱንና ቤተክህነቱን ለማጥራት ተዘጋጅቷል ፡፡ ከሚያጠራቸው የቤተክህነት ጉዳዮችም ሦስቱ ትኩረት አግኝተዋል ይላሉ፡፡ “የመጀመሪያው ኦርቶዶክስ የሚለው ስም ስህተት ነው  ፤ ስማችን ተዋህዶ ነው ፤ መለበስ ያለበት ልብስ ነጭ ብቻ ነው ፤  እሱም ቢሆን ጥለቱ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ መሆን መቻል አለበት ፤ አሁን ያሰርነውን ክር በመበጠስ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ክር ማሰር አለብን” የሚል ነው፡፡ በየአጋጣሚው ቤተክህነቱንና ቤተ መንግሥትን በመንቀፍ አሁን የሚታዩትን ችግሮች መሰረት አድርጎ ህዝቡ መጥቷል የተባለው ኤልያስን መከተል እንጂ ወደ ቤተክርስቲያን መሄዱ ጥቅም እንደሌለው እየተነገረ ነው፡፡ የሚከናወኑ ማናቸውም የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችም የኤልያስን መምጣት የሚያመላቱ እንጂ ምዕመና ሊሳተፍባቸው የሚገቡ አለመሆናቸው ይነገራል ፡፡ እስኪ እነዚህ ነገሮችን በዝርዝር እንመልከታቸው፡፡
ኤልያስ ማነው?
ኤልያስ ማለት “እግዚአብሔር አምላክ ነው” ማለት ነው፡፡ከክርስቶስ ልደት በፊት በስምንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ ከእስራኤል የተነሳ ነብይ ነው፡፡ኤልያስ የሚታወቀው በሶስት ሃይማኖታዊ ተግባሮች ነው፡፡የመጀመሪያው በእስራኤል ተንሰራፍቶ የነበረውን የባአድ አምልኮ ያጠፋና አምልኮተ እግዚአብሔርን ያጸና መሆኑ ሲሆን ፤ ሁለተኛው ደግሞ ንጉስ አክአብ አሕዛባዊት ኤልዛቤልን አግብቶ ይፈጽም የነበረውን ግፍና ጥፋት ሳይፈራና ሳያፍር ፊት ለፊት የገሰጸና ለእውነት ብቻ የቆመ ነብይ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ አቋሙ ምክንያት በሰሜን እስራኤል በሚገኙ ሰንሰለታዊ ተራሮች ፈፋ ለፈፋ ሲንከራተት ኖሯል፡፡ መጀመሪያ ቁራዎች ሲመግቡት ቆይተው ከዚያ በሰራፕታ የምትገኝ አንዲት መበልት አገልግለዋለች፡፡
ይህ ቆራጥነቱና ለአምልኮተ እግዚአብሔር ቋሚ መሆኑ በእግዚአብሔር ዘንድ ባስገኝለት ሞገስ የተነሳ ኤልያስ ከኄኖክ ቀጥሎ ሳይሞት ወደ ብሔረ ሕያዋን በመወሰዱ ይታወቃል፡፡ ዮርዳኖስን ወንዝ ከደቀ መዝሙሩ ከኤልሳዕ ጋር ከተሻገረ በኋላ የእሳት ሰረገላ መጥቶ ኤልያስን ወስዶታል፡፡ ይህ ኤልያስ የሚታወቅበት ሦስኛው ነገር ነው፡፡
ኤልያስ ይመጣል ?
ከ470 እስከ 440 በኢየሩሳሌም ትንቢት የተናገረው ነብዩ ሚልኪያስ “የእግዚአብሔር ቀን ነብዩ ኤልያስን እልክላችኋለሁ” ብሎ ትንቢት ተናግሮ ነበር፡፡ (ሚል 4፤5) ይህንንም በመያዝ አይሁድ በፋሶች ፤ በግሪኮች ፤ በሶሪያውያንና በሮማውያን መከራ በተፈራረቁባቸው 400 ዓመታት ውስጥ ነብዩ ኤልያስን ሲጠባበቁት ነበር፡፡ በየምኩራባቸውም የኤልያስ መንበር የተባለ ከፍ ብሎ የተሰራ ባለ መከዳ ወንበር ያስቀምጡ ነበር፡፡ ከክርስቶስ ልደት 6 ወራት ቀድሞ ተወለደውና  ከበረሀ የመጣው መጥምቁ ዮሐንስ በብዙ መልኩ ኤልያስን ይመስለው ስለነበረ የተወሰኑት የአይሁድ ክፍሎችና በኋላም ክርስቲያች ይመጣል የተባለው ነብዩ ኤልያስ እርሱ ነው ብለው ተቀብለውታል፡፡
ዮሐንስ መጥምቅ እንደ ኤልያስ ሁሉ በርኽኛ ባህታዊ ነው፡፡ እንደ ኤልያስ ሁሉ ጸጉር የለበሰ ነው ፤ እንደ ኤልያስ ሁሉ እስራኤል ተስፋ የቆረጠችበት ዘመን የመጣ ነው ፤ እንደ ኤልያስ ሁሉ ሄሮድስን ሳያፍርና ሳይፈራ የገሰጸ ነው ፡፡ በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያቶች መጥምቁ ዮሐንስ ኤልያስን ይመስለው ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ይመጣል የተባለው ኤልያስ መጥምቁ ዮሐንስ መሆኑን መስክሮለታል፡፡(ማቴ 11፤14 17፤10-13 ፤ ሉቃ 1፤17)
ስለ ኤልያስ መምጣት የሚነግረን ሌላው መጽሀፍ የዮሐንስ ራዕይ ነው፡፡ ዮሐንስ ራዕይ በምዕራፍ 11 ላይ ዓለምን የሚያጠፋው ሀሳዊ መሲህ  ከመጣ በኋላ ዙፋኑን አደላድሎ የዓለምን ክርስቲያኖች ሲጨርስና ምስክር ሲጠፋ ሁለት ምስክሮች መጥተው 1260 ቀናት ምስክርነት እንደሚሰጡና በመጨረሻም በሐሳዌ  መሲህ እንደሚገደሉ ይገልጣል፡፡ ከሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ የተነሱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እነዚህን ሁለት ምስክሮች ኄኖክና ኤልያስ መሆናቸውን ተርጉመዋል፡፡
ሐሳዊ መሲሕ ሲነሳና ሁሉንም እንደ ሰም አቅልጦ እንደ ገል ቀጥቅጦ ሲያጠፋ ፤ ለእውነት የሚመሰክርም ሲጠፋ ፤ ምዕመናንም በሚደርሰው መከራ ምክንያት የሚከተሉት የእምነት መንገድ  “ስህተት ይሆን…” ብለው ሲጠራጠሩ እነዚህ ሁለቱ ሳይሞቱ ወደ ብሔረ ሕያዋን ያረጉ ነብያት መጥተው እውነትን በመመስከርና የሐሳዌ መሲሕን ነገር በማጋለጥ ምስክርነታቸውን በደም እንደሚያጸኑ የሊቃውንቱ ትርጓሜ ያብራራል፡፡
ዮሐንስ አፈወርቅ ፤ አቡሊዲስ ዘሮምና ቪክቶሪያንስ እንደሚገልጡት ኤልያስና ኄኖክ በኢየሩሳሌም ያስተምራሉ ፤ በኢየሩሳሌም ተዓምራት ያደርጋሉ ፤ በኢየሩሳሌም ይገደላሉ ፤ በኢየሩሳሌም ይነሳሉ ፤  በኢየሩሳሌም ያርጋሉ ፡፡ ይህም ለጌታችን መምጣት የመጨረሻው ምልክት ነው፡፡ ከኤልያስና ኄኖክ  መምጣት በኋላ የሚጠበቀው የክርስቶስ ለፍርድ መምጣት ነው፡፡
ነብዩ ኤልያስ  በአራት ኪሎ
በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ነብዩ ኤልያስ መጥቷል ይባላል፡፡ የሚኖረው አራት ኪሎ ነው፡፡ አንዳንድ ታዋቂ የሆኑ ሰዎች  በተለይም አርቲስቶች ተከታዮች ሆነናል ይላሉ፡፡ ይህንን ሁኔታ ከቅዱሳት መጻህፍትና ከሊቃውንት ትምህርት ጋር ስናነጻጽረው ትክክል ሆኖ አናገኝውም፡፡
መጀመሪያ ነገር ኤልያስ ብቻውን አይመጣም፡፡ በነብዩ ሚልኪያስ ለብቻው እንደሚመጣ  የተነገረለት  ኤልያስ መጥምቁ ዮሐንስ መሆኑን ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ስለ መሰከረ ሌላ ምስክር ማምጣት አያስፈልግም፡፡  በሌላ በኩልም አሁን መጥቷል ተባለው  በመጨረሻው ዘመን የሚመጣው ኤልያስ  ከሆነ ደግሞ እንደ ሊቃውንቱ ትምህርት ብቻውን አይመጣም ፤ አብሮት ኄኖክም ይመጣል፡፡ አሁን ግን  ኤልያስ ከኄኖክ ተነጥሎ ነው መጣ የተባለው፡፡
ይህ ብቻ አይደለም፡፡ ነብዩ ኤልያስ የሚመጣበት ጊዜ በራዕይ ዮሐንስ ላይ ምዕራፍ 11 ተገልጧል፡፡  አስቀድሞ ሐሳዊ መሲህ ይመጣል፡፡ ዙፋኑንም በተቀደሰችው ከተማ በኢየሩሳሌም ይዘረጋል፡፡ ምዕመናንም(በተለይም የስድስት ስድሳ ስድስትን አምልኮ ያልተቀበሉትን) በግፍ ይገድላቸዋል፡፡ በዚህም ጊዜ እውነት ትቀጥንና ምስክር ታጣለች ፤ ኤልያስና ኄኖክ የሚመጡትም እውነትን በአደባባይ ለመመስከር ነው፡
ይህ ከሆነና በአዲስ አበባ እየተባለ እንዳለው ኤልያስ ከመጣ ሐሳዊ መሲህ መጥቷል ማለት ነው፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ምዕመናን በግፍ ተገድለዋል ፤ በዓለምም ላይ አማኞች በአብዛኛው አልቀዋል ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሲፈጸም አላየነውም፡፡ በኢየሩሳሌምም ሐሳዊ መሲህ ገና አልነገሰም፡፡
ሌላም ሦስተኛ ነገር መነሳት አለበት፡፡ ሐሳዊ መሲሕ የሚነግሠው ፤ ኄኖክና ኤልያስም የሚገለጡት ‹በተቀደሰችው ከተማ” በኢየሩሳሌም ነው፡፡ የሚሠውትም  እዚያ መሆኑን “እርስዋም  በመንፈሳዊ ምሳሌ ሶዶምና ግብጽ የተባለችው  ደግሞ ጌታችን የተሰቀለባት ናት› ብሎ ኢየሩሳሌም መሆኗን  ነግሮናል(ራዕይ 11፤8) ፡፡ አሁን ግን ኤልያስ ተገለጠ የተባለው ያለው አዲስ አበባ አራት ኪሎ ላይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ተልዕኮውም ከመጽሀፍት ጋር የሚጣረስ ነው፡፡ ጌታ የተሰቀለው አራት ኪሎ ነው ካላልን በቀር፡፡
ራዕይ ዮሐንስ እንደሚነግረን ኄኖክና ኤልያስ ምስክርነት የሚሰጡት ለ1260 ቀናት ወይም ለ42 ወራት ወይም ለሦስት ዓመት ከስድስት ወራት ነው፡፡ አሁን ግን አዲስ አበባ መጣ የተባለው ኤልያስ መጣ ከተባለ አራት ዓመት ሊያልፈው ነው፡፡
ምጽአትና መሲሕን መናፈቅ
በዓለም ሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የምጽአትን ቀን የመናፈቅና የምጽአትን ምልክቶች ደርሰዋል ብሎ የመጨነቅ አዝማሚያ የሚከሰትባቸው ምክንያቶች አሉ፡፡ እነዚህም ኢኮኖሚያዊ ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውሶች ሲከሰቱና ሕዝብ ተስፋ ሲቆርጥ ነው፡፡
እስራኤራዊያን ከፋርሶችና ከግሪኮች ወረራ በኋላ ሀገራቸው ስትመሰቃቀል ፤ መንፈሳዊነት ሲጎድልና መንግሥታቸው ፈርሶ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሲመጡ “መሲሕ እየመጣ ነው ፤ ኤልያስ እየደረሰ ነው” የሚል አስተምህሮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ2ኛው መቶ ክፍተ ዘመን ጀምረው ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ አንዳንድ ሰዎች ይመጣል የተባለው መሲሕና ኤልያስ እኛ ነን እያሉ አጋጣሚውን ሊጠቀሙበት ሞክረው ነበር፡፡ ከእነዚህ መካከል ከክርስቶስ ልደት በፊት በ2ኛውና አንደኛው መ.ክ.ዘ ላይ የተነሱ ቴዎዳስና ይሁዳ ይጠቀሳሉ፡፡ ቴዎዳስ አራት መቶ ሰዎችን አስከትሎ ነበር ፡፡ በኋላ ግን ሐሰተኛ መሆኑ ሲታወቅ ሕዝቡ ተወው ፡፡ ይሁዳም ሕዝቡን አስነስቶ እስከ ማሸፈት ደርሶ ነበር፡፡ መጨረሻው ግን አላማረም(የሐዋ 5፤37-39)
በቅርብ ጊዜ በኡጋንዳ ኢኮኖሚ ሰደቅና የእርስ በርስ ጦርነት ሲባባስ ይህም የሕዝቡ ማኅበራዊ ሕይወት ሲያቃውሰው “እኔ ክርስቶስ ነኝ” የሚል ሰው ተነስቶ በአንድ አዳራሽ ውስጥ  የነበሩ ተከታዮች መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ሲሉ በእሳት ተቃጥለው እንዲያልቁ አድርጓቸው ነበር፡፡ በአሜሪካ የደረሰው ኢኮኖሚ ድቀት ካስከተላቸው መዘዞች አንዱ በየአካባቢ “እኔ መሲሕ ነኝ” የሚሉ እና  ሕዝቡ ችግሩን  ከማሸነፍ ይልቅ ችግሩን እንዲረሳው የሚያደርጉ ሰዎች  መከሰታቸው ነው፡፡ በ2012 የተደረሰ አንድ ጥናት ባለፉት 3 ዓመታት በአሜሪካ ውስጥ 132 ሰዎች መሲሕ ነን ብለው ተነስተው ወደ 4.5 ሚሊየን የሚደርስ ሕዝብ አስከትለዋል፡፡
በሀገራችን ታሪክ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በተከሰተው የግራኝ ጦርነት በኋላ ሕዝቡ መንፈሳዊ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተስፋ መቁረጥ ደረጃ ደርሶ ነበር፡፡ አብያተ ክርስያናቱ ተቃጠሉ ፤ ኢኮኖሚው ወደመ ፤ መንግስት ተዳከመ ፤ ትዳና መስተጋብር የመሰሉ ማኅበራዊ ተቋማት ፈረሱ፡፡ ብዙ ሰዎች ሞቱ ፡፡ ይህ ሕዝቡ ላይ ባስከተለው ተስፋ መቁረጥ የተነሳ ከዚህ መከራ እና ስቃይ የሚያወጣውን አንዳች ሰማያዊ ኃይል ይጠብቅ ነበር፡፡
በሀገራችን ላይ የበልጥ ራዕይ ዮሐንስ የታወቀውና በገልባጮች እጅ በብዛት የተገለበጠው በዚህ ጊዜ ነው፡፡ በሚሰሩት አብያተ ክርስቲያናትም የሐሳዊ መሲህ ፤ የኤልያና የኄኖክ ፤ የአዲሲቱ ሰማይና ምድር ስዕሎች በብዛት ተሳሉ፡፡
ከግራኝ ጦርነት በኋላ በአጼ ሰርጸ ድንግል ወራሾች መካከል በተፈጠረው የርስ በርስ ውጊያ ሀገሪቱ ስትታመስና ሕዝቡ በተደጋጋሚ ጦርነትና የሕዝብ ፍልሰት ሲታወክ እኔ ክርስቶስ ነኝ ፤ ሕዝቡንም ከችግር ላወጣውና መንግሥተ ሰማያት ላወርሰው መጥቻለሁ የሚል ሐሳዊ መሲሕ በአማራ ሳይንት አካባቢ ተነስቶ ነበር ፡፡ አስራ ሁለት ሐዋርያት ፤ 72 አርእድትንና 36 ቅዱሳት አንስትንም መርጦ ነበር፡፡ ብዙውም ሕዝብ በተስፋ መቁረጥ ላይ ስለነበረ ተከትሎት ነበር፡፡ በኋላ ግን በሞት መቀጣቱን አቡነ ጎርጎርዮስ በኢትዮጰያ ቤተክርስቲያን ታሪክ መጽሐፋቸው ጠቅሰውታል፡፡
በቅርቡ በሀገራችን ታሪክ ዐጼ ምኒሊክ አርፈው ሞታቸው በተደበቀበት ጊዜ ፤ በታህሳስ ግርግር ጊዜ ፤ በአብዮቱ ዋዜማና ማግስት ፤ እንዲሁም ኢሕአዴግ አዲስ አበባ በገባበት ጊዜ አያሌ “ባሕታውያን” ተነስተው ነበር፡፡ ይህ ነገር መጣ ፤ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ስለ ንግሥት ዘውዲቱ  ዘመን በጻፉት የትዝታ መጽሀፋቸውም ይህንን ገልጠውታል፡ ይህም ያም ነገር ታየ ፤ ተገለጠ የሚለው ብሂልም  ነባርና የሀገር አለመረጋጋትና በኑሮ ተስፋ መቁረጥ ተገን አድርገው የሚመጡ ናቸው፡፡
የኤልያሳውያን ሁለት አስተምህሮዎች
አሁን በዘመናችን የተከሰቱ ኤልያሳውያን ሁለት ነገሮች ላይ አተኩረው እየሰሩ ነው፡፡ የመጀመሪያው “ኦርቶዶክስ” ትክክለኛ ስም አይደለም የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሰንደቅ አላማን ከጽድቅና ከኩነኔ ጋር ማያያዛቸው ነው፡፡
ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል የግሪክ ሲሆን “ኦርቶ” ርቱዕ “ዶክስ” ደግሞ እምነት ፤ መንገድ ፤ ጠባይ ፤ ባህል ማለት ነው፡፡ ይህንን ስም የክርስቲያን አብያ ክርስያናት መጠቀም የጀመሩት በ325 ዓ.ም በተደረገው ጉባኤ በኋላ ነው፡፡ ከጉባኤ ኬልቄዶን የ451 ዓ.ም ጉባኤ በኋላ ደግሞ የምዕራብ አብያተክርስቲያናት ካቶሊክ ሲባሉ ምስራቆቹ “ኦርቶዶክስ”  የሚለውን ስም ይዘው ቀሩ ፡፡ በምስራቆቹ መካከል  የጉባኤ ኬልቄዶንን  ውሳኔ በመቀበልና ባለመቀበል መካከል ልዩነት ስላለ የግሪክ መሰል አብያተክርስቲያናት የምስራቅ ኦርቶዶክስ ሲባሉ  ፤ አርመን ፤ ግብጽ ፤ ሕንድ ፤ ሶሪያና ኢትዮጵያ ደግሞ “ኦሪየንታል ኦርቶዶክስ” ተባሉ፡፡
ኦርቶዶክስ ፤ ኦርዶክሳዊ የሚለው ስም በሀገራችን ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በሁለት መንገድ ተገልጠዋል፡፡ በአንድ በኩል ጥሬ ቃሉ እንዳለ የተቀመጠ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ወደ ግዕዙ ተተርጉሞ “ርቱዕ ሃይማኖት” እየተባለ ተቀምጧል፡፡ ፍትሐ ነገስት ‹ይኩን ምእመነ ኦርቶዶክሳዌ ይላል› (42፤2) ያዕቆብ ዘእልበረዲም ‹ሃይማኖት ኦርዶክሳዊት› ሲል እምነቱን ይገልጣል፡፡ መጽሐፈ ቄርሎስም ‹ሃይማኖተ ርቱዕ› እያለ ተርጉሞ ይገልጠዋል፡፡
‹ተዋሕዶ› የሚለው ቃል ነጥሮ የወጣው በጉባኤ ኤፌሶን በ431 ዓ.ም ነው፡፡ በጉባኤው ንስጥሮስን ባሕል ለማየት የተሰበሰቡ አበው በእስክንድርያ ቄርሎስ የተሰጠውን ትምህርት በመቀበል ሁለት ባሕርይ የሚለውን አውግዘው መለኮት ከስጋ ተዋህዶ ሥግው ቃል ሆነ የሚለው ርቱዕ እምነት መሆኑን መሰከሩ፡፡ ይህ ቃል የእምነት ዶክትሪን መገለጫ ሆኖ ነው የኖረው ፡፡ በኬልቄዶን ጉባኤ በኋላም ይህ ስያሜ የኦርቶዶክሶቹ ዋና መጠሪያ እየሆነ መጣ፡፡ በኢትዮጵያ ጥንታዊ መጻሕፍት ላይ ተዋህዶ እምነት ሆኖ እንጂ የቤተክርስቲያ መጠሪያ ሆኖ አናገኝውም ‹ኦርቶዶክሳዊ› የሚለው ቃል የምናገኝውን ያህል  ‹ተዋህዶ› የሚል መገለጫ አናገኝም ተዋሕዶ የሚለው ቃል በነገረ ሥጋዌ ትምህርት ላይ በሀገር ውስጥ የተነሳ የተለየ አስተያየት ስላልነበረ መጠሪያነቱ አልጎላም፡፡
በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከአውሮፓ በመጡ ካቶሊካውያን ምክንያት የተፈጠረውን የእምነት ክፍፍል ተከትሎ ይህ የእምት መጠሪያ የአማያንና የወገን መጠሪያ እየሆነ መጣ፡፡ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቅባትና ጸጋ የሚባሉ ባሕሎች መጥተው ነበር፡፡ እነዚህን ባሕሎች የሚቃወሙትና ኢየሱስ ክርስስ መለኮት ከስጋ በተዋሕዶ ሥግው ቃል እንጂ እንደ ነገስታትና ነቢያት በመቀባት አይደለም ያሉት ደግሞ መጠሪያቸው ከእምነታቸው ተወስዶ “ተዋሕዶዎች” ተባሉ፡፡ ከቦሩ ሜዳ ጉባኤ በኋላም የቤተክርስቲያኒቱ ሕጋዊ ስም ‹‹ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ›› የሚለው ጎላ፡፡
ኦርቶዶክስ የሚለው ስም  ቤተክርስቲያኒቱ በዓለም የምትታወቅበት የወገን ስሟ ነው፡፡ ሌሎችም ‹የግብጽ ኦርቶዶክስ› ፤ ‹ የሕንድ ኦርቶዶክስ› ብለው ይጠሩ እና ከአካባቢያቸው ራሳቸውን ለመለየት ደግሞ ‹የግብጽ ኮፕት ኦርቶዶክስ› ፤ ‹የሶርያ ያዕቆባዊት ኦርቶዶክስ› እያሉ ይጠራሉ፡፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንም  ‹ኦርዶክስ ተዋሕዶ› ትባላለች ፡፡
አንዳንድ ሰዎች በዘመናውያን መዛግብት ቃላት ስለ ‹ኦርቶዶክስ› የተሰጡ ፍቺዎችን ይዘው ይሞግታሉ፡፡ ኦርቶዶክስን ‹ከአክራሪነትና ከለውጥ አለመቀበል› ጋር እያዛመዱ ይፈቱታል፡፡ በዚህ ምክንያት ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል ለኮንሰርቫቲቭ ፓርቲዎችና ለአይሁድ ሲሰጡት ይታያሉ፡፡ ይህ ግን ኦርቶዶክስ የሚለው ስም ከመነጨበት ጠባይ በእጅጉ የራቀ ነው፡፡
አሁን ወደ ሁለተኛ ነጥብ እንመለስና ሰንደቅ አላማን እንመልከት፡፡ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የኢትዮጵያውያን መለያ ናት፡፡ ለዚች ሰንደቅ አላማ  ብዙዎች ውድ ሕይወታቸውን  ከፍለዋል፡፡ ከእነዚህ ውድ ሕይወታቸውን ከከፈሉ መካከልም የቤተክርስቲያኒቱ አባቶችና ልጆች ይገኙበታል፡፡ ቤተክርስቲያኒቱ ታሪክን ከማቆየት ፤ ባሕልን ከማሻገርና ኢትዮጵያዊነትን ከማስረጽ ሚናዋ አንጻር ሰንደቅ አላማንም  በማስከበርና ለትውልድ በማስተላለፍ የበኩሏን ድርሻ ተወጥታለች፡፡
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ  ሰንደቅ አላማ ከሀገራዊ እሴትነቱ ፤ መስዕዋትነትና ነጻነት ከማንጸባረቁም ፤ ለኢትዮጵያውያን ከደማቸው ጋር የተዋህዶ ልዩ ምልክት ከመሆን አልፎ ግን ጽድቅና ኩነኔ ውስጥ የሚገባ ፤ እርሱን ያልተቀበለ እና ያላደረገ ሰማያዊ ዋጋ የሚቀርበት ፤ ከእርሱ ውጪ ቀለም ያለው ነገር የለበሰና ማህተብ ያሰረ ሃጥያት እንደሰራ ተቆጥሮ ንስሃ የሚገባበት ግን አይደለም፡፡ ከኢትዮጵያ ውጪ ያለ ዜጋ የቤተክርስቲያኒቱ አባል ለመሆን የቤተክርስቲያቱን ዶግማ እና ቀኖና መቀበልን እንጂ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራን መቀበል ግዴታው አይደለም፡፡ በኡጋንዳ ባንዲራ ፤ በአሜሪካ ባንዲራ ፤ በሶማሊያ ባንዲራ አሸብርቆም ቢሆን የኦርዶክስ ተዋሕዶ ልጅ መሆን ይችላል፡፡ አስከ አሁን በቀኖና በሚደነገጉ መጻህፍቶች ውስጥ ሰንደቅ አላማን የተመለከተ ቀኖና የለንም፡፡
በመሆኑም ሰንደቅ አላማችን ከኢትዮጵያዊነታችን ጋር እንጂ ከኦርቶዶክስ  እምነታችን ጋር  የታሪክ እንጂ የድኅነት ተዛምዶ የለውም፡፡
እንደዚህ አይነት አመለካከቶች የሚያይሉት እንዲሁ አይደለም፡፡ በሕዝቡ ዘንድ ኢትዮጵያዊ ስሜት  ደብዝዟል ፤ ለሰንደቅ አላማና ለሀገራ እሴቶች የሚሰጠው ዋጋ ቀንሷል ተብሎ ሲታሰብ ሰንደቅ አላማን የመሰሉ ሀገራዊ እሴቶች ጉልበት ያገኙ ዘንድ ተጨማሪ ሃይማኖታዊ ኃይል ይሰጣቸዋል፡፡ ቤተክርስቲያቱ የሰንደቅ አላማን ክብርና ትርጉም ማስተማርዋ እና በትውልድ ውስጥ ማስረጿ ባልከፋ ፡፡ አስተምህሮ ግን ከሀገራዊ ግዴታ የሚመጣ እንጂ ከሃይማኖታዊ ግዴታ የሚመጣ መሆን የለበትም፡፡ ከሕዝብ እሴቶች እንደ አንዱ ሆኖ እንጂ ከጽድቅና ኩነኔ ጋር መሆን ለበትም፡፡
ምን ይደረግ ?
የሃይማኖት ትምህርት በሚገባ መሰጠት ሲያቆምና ሰዎችም በተደላደለው እምነት መንገድ ላይ በእውቀትና በእምነት እየተመሩ መጓዝ ሳይችሉ ሲቀሩ ‹ባለ ተስፋዎች ይሆናሉ› ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በላከው መልዕክቱ መጀመሪያ ላይ ‹በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን ፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ባሉት ምዕመናን›  በማለት የገለጠው አባባል ታላቅ ነገር አለው፡፡ ምእመናኑ በሁለት ዓለም መኖራቸውን እንዳይረሱ ለማድረግ ነው፡፡ ‹በክርስቶስና በኤፌሶን› ክርስቲያችም ምድራዊነታቸውንም ሰማያዊነታቸውንም  መርሳት የለባቸውም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን ምድራዊ ጎዳና ሲያቅተንና ፈተና ሲበዛበት ፤ የኢኮኖሚ የፖለቲካ ሁኔታ አልቃና ሲል ፤ የምናየው የምንሰማው ተስፋ ሲያሳጣን ፤ ምድር ላይ መሆናችንን ፈጽመን ረስተን ኅሊናችን ወደሚፈጥረው ልዩ አለም እንገባለን፡፡ ያንንም እጅግ ከመመኝታችን የተነሳ የደረስንበት ይመስለናል፡፡
በዚህ ጊዜ የሚሰጡ ትምህርቶች ለሰዎች ቀላል የሆኑ ፤ ንባብና ትምህርትን የማይጠይቁ ፤ በቀላሉ የሚተገበሩ ፤ የሚነኩና የሚዳሰሱ ይሆናሉ፡፡ ቡና መጠጣት አለመጠጣት ፤ አረንጓዴ ቢጫ ክር ማሰር አለማሰር ፤ በባዶ እግር መሄድ አለመሄድ ፤ ጸጉርን ማስረዘም አለማስረዘም ፤ መቁጠሪያ አለስርዓቱ ማሰር አለማሰር ፤ ከመምህራን ቃል ይልቅ የሰይጣንን ቃል መቀበልና ማመን እየሰለጡ ይመጣሉ፡፡
ለዚህ ትልቁ መፍትሔው የእምነት ተቋማት የራሳቸውን ሥራ (ወንጌል ማስተማር) ትተው በሰዎች ስራ ውስጥ መግባታቸው ነው፡፡ ስለዚህ ተቋማቱ መጀመሪያ ራሳቸውን ወደ ተልዕኳው መልሰው ፤ የማይጨበጥ ተስፋ የሚዋልለውን ሕዝብንም ወደ ትክክለኛ ኑሮ እና ተስፋ መመለስ አለባቸው፡፡  እዚህ ኤልያስ ነኝ ፤ እዚያ ድንግል ማርያም ነኝ ፤ እዚያ አቡዬ ነኝ የሚሉ በተነሱ ቁጥር ሕዝቡ ስራና ትዳር ፈትቶ ተንከራቶ አይዘልቀውም፡፡ ይህ አዲስ እንቅስቃሴ ለምእመናኑ የተለየ ፋይዳ ይዞ አልመጣም፡፡

staff reporter | March 18, 2013 at 10:32 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1zD
Comment   See

                       

Sunday, March 17, 2013

ICC Indictee Set to Travel to Ethiopia

 
Recent local media reports indicate that the current governor of South Kordofan, Ahmed Haroun, may head Sudan's delegation to the upcoming negotiations with rebels from Sudan People Liberation Movement North (SPLM-N). News of a governor of an important province heading a delegation would not normally be a headline, however, the governor is an alleged war criminal in this case.
Ahmed Haroun, also known as "The Butcher of Nuba", is subject to an arrest warrant by the International Criminal Court (ICC) for serious charges, including war crimes and crimes against humanity. He has served in senior official capacities in the Sudan for more than a decade.
Haroun, a lawyer by training, joined politics at a young age. He was the youngest Minister of State in the government. From 2003-2005, he was a state minister for the Interior and allegedly in charge of the management of the "Darfur Security Desk", thereby coordinating the different government bodies involved in the counter-insurgency. It is highly likely that he must have been aware of the situation in Darfur during that difficult period. Later on, he was appointed Minister of State for Humanitarian Affairs, following his stint at the Ministry of the Interior.
Currently, he is the governor of South Kordofan, the province that lies to the west of Darfur and to the north of South Sudan, encompassing key border regions like Abyei whose status remains unresolved. Over these same regions, Haroun has allegedly recruited tribal militias to try ensure -through violent means- that Abyei and its oil-rich fields remain part of the Sudan and do not effectively exercise a referendum under the Comprehensive Peace Agreement (CPA), which could result in it joining South Sudan. Alleged human rights violations occur in South Kordofan on a daily basis with total impunity for the perpetrators. Victims in the Nuba Mountains in South Kordofan remember Haroun all too well from the 1990s, when he was more commonly known as the "Butcher of the Nuba."
In 2007, the ICC judges issued an arrest warrant for Haroun for 42 counts for war crimes and crimes against humanity. Since that period, he openly defied the ICC and its former Chief Prosecutor Moreno Ocampo, firing off false accusations at both the institution and the former Prosecutor.
Despite the charges leveled against him, he has not -- until this moment -- set foot outside of the Sudan, allegedly fearing he could be apprehended. If he travels to Ethiopia to participate in talks at the AU summit, it would be his first known trip outside the country since the issuance of an arrest warrant against him.
Although Ethiopia is not a state party to the Rome Statute, it is a member state to the United Nations. Therefore, it has the obligation to comply with Resolution 1593/2005 since this was a Chapter VII resolution, which is considered legally binding upon all member states. This resolution "advised all states and concerned regional & international organizations to cooperate fully with the court and prosecutor. "
As noted in her latest presentation at the UN Security Council, the ICC Prosecutor Ms. Fatou Bensouda recalled that the Council referred the situation to the Court because of the firm belief "that the justice process is an essential component of any strategy aiming at truly stopping ongoing crimes and achieving peace in Darfur."
This statement could not be more timely: How many more have to be killed in order to have Ethiopia and other members states of the UN comply with the UNSC 1593? Cooperation is needed at all fronts, first and foremost at the UN, especially when we are talking about massive human rights violations that affected the lives of more than 2.5 million people.
The UN needs to take tougher action on member states that deliberately disrespect their obligations. This will hopefully deter other suspects from Darfur, Sudan from visiting other member states of the UN.


Article co-authored with Stephen A. Lamony, Senior Advisor of the Coalition for the International Criminal Court (CICC).