Friday, July 31, 2015

ኦባማ መጣ ኦባማ ሄደ ምን ፈየደ ? ህወሃት መሩ መንግስት ተጋለጠ::መጭው አኬል ዳማ ተበሰረ።

adanom

ህወሃት መሩ መንግስት ልዩ በዓል፤ልዩ ድምቀት፤ልዩ ምልክት፤ታሪዊ ንግርት ሌላም ጨመር አርጎ የፕሬዜዳንት ኦባማን ጉብኝት ቢያስወራውም አለቀ:: የተረፈ ምንም የለም። የተለወጠም ምንም የለም።ከታፈገው እስር ቤት በጣት የሚቆጠሩ ተፈተዋል። ህወሃት በዚህ አይመሰገንም።ህዝብም ዓለምም የታፈገውን እስር ነው የሚመለከተው። ይልቅስ የወያኔ መሃይም መንጋ ያደረገው የፕሮቶሎል ስተተት ሲያስቅ ሰነበተ።
ምን ደስ አለህ ብባል ፕሬዜዳንት ኦባማ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህንን አንስተው፤የሰው ልጅ መገኛ እያለ አክብሮት፤ ፍቅሩን እምቅ ስሜቱን ለናት አገሩ ስለገለጠላት ባለቅኔ መናገራቸው ነው።ጥቁር አማሪካውያን የባርነት ውርደትን አንቀበልም ሲሉ ኮከባቸው ኢትዮጵያ ነበረችና ገጣሚ ፖል ዱንባርን፡”ለኢትዮጵያ ከልብ” (Ode to Ethiopia) ብሎ የተቀኘውና ላግስተ ኁስ  ኢትዮጵያ በፋሽስ መንጋጋ ስትገባ “የኢትዮጵያ ጥሪ” ብሎ የገጠመውን ሌላ አኩሪ ገጣሚ ማንሳታቸው አልረሳም (Call of Ethiopia)። በተለይ በዘረኞች፤ በቂመኞች በከዳተኞ እጅ ባለችው አገር፡ይህ መሆኑ ይገርማል።ወይታሪክ? ያሰኛል።
ፕሬዜዳንት ኦባማ ወያኔን ሊያወድሱ ነው ወደ ኢትዮጵያ የተጔዙት የሚለው ጅሉ ቴድሮስ አዳኖም ነው።ፕሬዜዳንቱ ዓይናቸው ሽብርተኞች ላይ ነው።አልሸባብን ለመውጋት ከሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች ቢያገኙ ኖሮ ህወሃትን አይፈልጉም ነበር። ሰራዊቱን ለማቅረብ ሽርጉድ ደግሞ መለስ የጀመረው ነው። የተለወጠ ነገር የለም።የጥንቱ ኢትዮጵያ ጦር ድንበር አስከበረ።ጠበቀ።ይሄው ነበር።ለሰላም ጥበቃ ቢሰለፍ በተባበሩት መንግስታት ነበር።ሌላ አዛዥ አልነበረም።አዳኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ምንድነው ቢባል የህወሃት በስልጣን መቆየት ነው የሚል ነው።ለዚህ ደግሞ ማንስ ቢያዘው አይጨንቀውም።
ጅሉ ቴድሮስ አዳኖም ፕሬዜዳንት ኦባማ “መንግስታችን በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ነው ብለውልናል” አለ ባደባባይ።ኦባማ ምን አገባቸው? አማሪካስ ? ባለቤቱ መስካሪው የኢትዮጵያ ህዝብ እያለ ? ፕሬዜዳንቱ ዛሬ ያለውን የመንግስታቸው አቌም ነው የሚንጸባርቁት።እንዴት የውጭ ጉዳይ ሆኖ ይህን አይረዳም? ጅሉ ቴድሮስ አዳኖም ይህ ሊገባው አይችልም። ባድር ባይነት ላገኘው ሹመት የሚበቃ አይደለምና።ሱዛን ራይስ ለምን ሳቅ አፈናት ? በዲሞክራሲያዊ መንገድ ነው ወይ የተመረጡት ስትባል? የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን አይከታተልም? እስቲ ይችን እመቤት ክሰሳት ? እስቲ ውቀሳት ?የት አባክ ትገባለህ? ቪኦኤ እድሉን ሰጥቶህ ነበር። ሱዚ አርባክንድ ምላስ ነው ያላት! ከፈለግህ አሁንም ሞክር።
ሌላው ነገር ፕሬዜዳንት ኦባማ አፍሪካ የሙስና ነቀርሳ አለባት ብለዋል።የሙስና ሙከራ ጣቢያ ሆና ቆይታ ዛሬ የሙስና ማዕከል የሆነችው አዲሳባ መጥተው ይህን ማለታቸው ለወያኔም ለሁሉም የአፍሪካ ሞሽላቆች ነው።የሚሰረቀው መጠን፤ የት እንደተደበቀ፤በማን? ሁሉን ከስለላ ድርጅታቸው ያገኙታል።ሟቹ ሞሽላቃው መለስ ዜናዊ የዘነጠላቸው ቢሊዮኖች ምስጢር አይደሉም። በነገራችን ላይ የናጄሪያ አዲሱ መሪ አገሬን ግጠው የበሏት ባለስልጣናት የዘረፉትን ለማስመለስ እርዱኝ ለማለት ነው ወደ አሜሪካ የመጡት፡የቦኮ ሃራምም ጉዳይ ቢቀድምም።ውጭ ጉዳይ የሚያናግሩህ ፋይልህን በጃቸው አርገው ነው።ዳሩ ምን ይገባሃል?
ፕሬዜዳንት ኦባማ የደቡብ ሱዳንን፡የኬንያን ጸጥታ ጉዳይ አንስተዋል።ኢራቅ፤ሶሪያ፤አፍጋኒስታን ያለው ሁኔታ የበለጠ የሚሳስባቸው ይሆናል።ስለፓርቲያቸው የመጭው የምርጫ ውድድር ከማሰባቸው አንጻር የአፍሪካ ጉዳይ ቅድሚያ አይዝም ማለት ያስችላል።ንግዱም ከቻይናው አፈሰማይ ይተርፈኛል ማለት ያውም ይህን ያህል ጌዜ ተተኝቶ የሚያዋጣ አይደለም።በኔ አስተያየት ፕሬዜዳንት ኦባማ ለጉዞ ያነሳሳቸው እንዲው በስልጣን ዘመኔ ያባቴን አገርና ዘመዶቸን ልጠይቅ ማለት ነው ማለት ይቻላል።
ይህ የፕሬዜዳንት ኦባማ ጉብኝት ህወሃት መሩን መንግስት በጣም ያጋለጠ ነው።ከጉብኝቱ ትንሽ ቀደም ብሎ በአበኞች ግንቦት7 ተኩስ ቢከፈት መላው የወያኔ መንጋ ተርበተበተ።ወፋፍራሞቹ የህወሃት ድመቶች ግራ ተጋቡ።ጄኔራሎቹ መወቃቀስ ጀመሩ።ሚስጥር ይሾልክ ጀመር።ጨዋታው ባጭር ጊዜ መቀየሩ ግራ አጋባቸው።አጭበርባሪው መለስ እያለ በተማሪ እንቅስቃሴ ከተማራት ተንኮል መነጋገሪያ የምትሆን አንድ ነገር ጣል ያደርግ ነበር።የድል አጥቢያ አርበኛው ቴድሮስ አዳኖም፤የውሸት መዝገብ የሆነው በረከት፤ሰካራሙ ሽማግሌ፤ ሹላፉ አባይ ጸሃዬ አንዳቸው ብልሃት የላቸውም።በተለይ ቴድሮስ አዳኖም የት ?ምን ሲያደርግ ነበር ባለፉት ቅድም ወያኔ ዓመታት ? በሜዳው ትግል ምን ድርሻ ነበረው ? ያለው ዋና ሰርተፊኬት የመለስ ተላላኪነት ነው። በቪኦኤ ራዲዮም ያስረገጠው ይህንኑ ነው።ዛሬመ “ታላቁ መሪያችን ይላል” ይህ ሰው መሳቂያ ነው።
ልክ ጌታው ያሰለጠነው ውሻ አይነት ነበር የጅሉ ቴድሮስ አዳኖም ቃለመጠይቅ በቪኦኤ ራዲዮ። ያልተፈቱት ጋዜጠኞችስ ሲባል “የፍርድ ቤት ውሳኔ “ እያለ ቀላመደ።ልክ እንደ ጌታው እንደ መለስ።ስለ መቶ በመቶ ማቸነፍም ሲጠየቅ ራሱን ለትዝብት ዳረገ።ከዚህ ሰው ዲግሪ የቆስጤ በርሄ የተሻለ ነው ወይ ያሰኛል። ጌታው ያሰለጠነው ውሻ የሚያሰኘው አዳኖም ሲናገር ብርሃኑ ነጋ ወደ ትግል ሜዳ መሄዱን አስመልክቶ ልክ እንደሟቹ ድውይ “መንገዱን ጨርቅ ያርግለት” ማለቱ ነው።ብርሃኑ ነጋ ወደ ኤረትራ አልሄደም። እደግመዋለሁ።ወደ ኤርትራ አልሄደም። ብርሃኑ ነጋ የሄደው የትግል እቶቹንና ወንድሞቹን ሊቀላቀል ወደ ትግል ሜዳ ነው የሄደው።በኤርትራ በኩል ? አዎን። በኤርትራ በኩል:: ደህና ካምፒንግ እንኳን ወጥቶ የማያቅ የወሬ ቋት ቴድሮስ አዳኖም : “ጨርቅ ያርግለት” ማለቱ አስቂኝ ነው። ራሳቸው ህውሃቶች(መኮንኖቹ)የሚስቁበት ይመስለኛል።
የጅሉ ቴድሮስ አዳኖም በዳያስፖራ ያለው ሁሉ የደርግ አባል የነበረ ይመስለዋል።እሱ እንጀራ በወጡን ሲዝቅ ደርግን ይታገል የነበረና ዛሬ በስደት ያለው ብዛቱ እንደሚያይል፤ህወሃትም አላስቀምጥ ብሎት የተሰደደ እጅግ ብዙ እንዳለ አያውቅም።አሁን እሱ ድፍን አፍሪካን አስሶ፤ የአፍሪካ አንድነት አርኪቴክት ከነበረው ክቡር አቶ ከተማ ይፍሩ ወንበር ላይ ይቀመጥ? አይ ኢትዮጵያ ? ቴድሮስ አዳኖም ታሪክ ይወቅስሃል የሚባል አይደለም።ትልቅ አፍ ያለው ትንሽ እንሰሳ በመሆኑ።ታሪክ ደግሞ እንዲህ ላለው አይጨነቅም።
ቴድሮስ አዳኖም “በዘዴ” በቪኦኤ ቃለ መጠይቁ ላይ አንዳርጋቸው ጽጌን አንስቷል።ይህ የሚያመለክተው ምንያህል ወያኔ ስለ አርበኞች ግንቦት 7 ሲጨነቅ እንደሚያድር ነው።አንዳርጋቸውን ህጋዊ ባልሆነ መንገድ  ከመሰል የየመን ወሮበላ አረብ አብራችሁ ከያዛችሁ በኋላ ያሻችሁን አርጋችሁታል።ሁኔታውን የብሪጣኒያው አምባሳዶር ግልጥ አርጎታል።ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ከምትጠቀሙበት መጀመሪያ ከቤተሰቡ ታገናኙት ነበር። ከሰብእና ጎዳና ሳይሆን እናንተ ያላችሁት ከተንኮልና በቀል ጎዳና ነው።ውጭ ጉዳይ ቴድሮስ አዳኖም ለቀንደኛው ቂመኛ ለበረከት ስሞን ይህን ንገረው። የላከህም እሱ ነው። አንዳርጋቸው ጻፈ ያልክው መጽሃፍ ተነባቢነትም ታማኒነትም የሚያገኘው አቶ አንዳርጋቸው ተፈቶ፤ቤቱ ሎንዶን ተመልሶ ቢያሳትመው ብቻ ነው።ከዚህ የተረፈው ያው አኬልዳማችሁ ነው።መለስ ሲሞት መንደራችሁ ለጥቆ የጅል ሆነ።የሚታዘብ ያለ አይመስላችሁም።
ባጭሩ የፕሬዜዳንት ኦባማ ጉብኝት ለወያኔ የፈየደው ምንም የለም ከመጋለጥ፤መሳቂያ ከመሆን ሌላ።የእሳቸው ጉብኝት የምስራቅ አፍሪካን የሰላም ሁኔታ ያሻሽለዋል ማለት አይቻልም።በትንሹ የደቡብ ሱዳንን ሁኔታ ብቻ ቢያዩ የት ነበሩ ብሎ ያስጠይቃቸዋል። ግራ ቀኙ ፋይዳ ቢስ ነው።የህወሃት መሩ መንግስት ስንብት አዲስ ምእራፍ መክፈት መቻሉን “መንገዱን ጨርቅ ያርግላችሁ” የተባሉት እነ ብርሃኑ ነጋ ቀድመው አውቀውታል።መንገዱ ግን ጨርቅ አይደለም።ለወሬኛ ይመስለዋል እንጂ። እድሜ ይስጠን የኢትዮጵያ አምላክ።

ኢትዮጵያ በነጻነት በአንድነት ለዘላለም ትኑር!
ሽብርተኛ ድርሽ የማይልባት፡የተረጋጋች፡የበለጸገች አገር በህብረት እንገነባለን!
በግፍ የታሰሩ የስልምና ሀይማኖት ተከታይ ወንድሞቻችን ይፈቱ!
አርበኞች ግንቦት 7 ከሌሎች ታጋይ ሃይሎች ጎን ለጎን ወደፊት ይራመዳል!
በአገራችን ውስጥና በውጭ ያላችሁ አገር ወዳዶች ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ጋር ተባበሩ!

Did President Obama tell the truth about Democracy in Ethiopia?

Did President Obama tell the truthCongressman Joe Wilson called President Obama a liar during his address to Congress. I was infuriated, as well as many Americans, because it was rate to utter such a word in such venue or any venue to a sitting president.


Now the question is, Did President Obama tell the truth or he is being mislead about democracy in Ethiopia. All the evidence about Ethiopia from the State Department Report on Human Rights, Amnesty International, Human Rights Watch and the U.N all indicate egregious human rights abuses, but President Obama on July 27, during a joint press conference with PM. Hailemariam Deslalegn told the press that Ethiopia is a democracy and the Ethiopian regime was “democratically elected”. The regime won 100% of votes according its government appointed election commission. The only opposition representative was barred from running.Ethiopia & president-obama
What is going with President Obama. I wonder what happens with African-Americans when they go to Africa, they fall in love with dictators and they completely ignore the reality or the masses who are toiling and completely oppressed and suppressed. Ethiopia has more journalist and religious leaders in jail than any African country. In his book Out of America: A Black Man Confronts Africa, journalist Keith Richburg criticizes some African-Americans for being too willing to work with African dictators who increase the suffering of their own people. Obama is no exception to this curse.
In 2005 at the behest of the United States, Ethiopia invaded Somalia and succeeded in ousting a government that brought stability and for the first time after the fall of dictator Siad Barre. All Somalia and tribal chiefs were under its control. The consequence of that invasion was the rise of Al Shabab. Now, Obama sowing the seeds of rebellion by taking all hopes of any democratic change in Ethiopia. He has closed all the doors for peaceful change or any U.S. pressure for democratic opening in Ethiopia by endorsing the current system. The Ethiopian regime spends huge sums of money lobbying U.S. officials with the help of DLP Piper, a global lobbying agency and that may be paying off, but at the expense of the 100 million lives in Ethiopia.
What a legacy for a man who won the Nobel Peace Prize to endorse one of the most rotten and corrupt regime in the world. What a contradiction for a president who often talked about openness and democracy to reverse a course and wine and dine in country where there is no freedom of the press or freedom of religion or where the Internet and most of the means of production are controlled by a one party dictatorship.
It is a sad day for Ethiopia, a sad day for Obama and a sad day for U.S.A because Obama represents U.S.A.

Tuesday, July 28, 2015

The Greatest Truth Never Told



When oil becomes thicker than blood,
 the results are always wars, famine of Biblical proportions, poverty, lack of educational institutions, political and economic backwardness, low IQ and shocking level of moral illiteracy.... etc...

The content of the letter is posted below in text format for a better reading....

Image

    Image
    SINCLAIR OIL CORPORATION
    630 FIFTH AVENUE
    NEW YORK, N.Y.


    September 27, 1945


    The honorable James F. Byrnes
    Secretary of state
    Washington D.C.

    Dear Mr. Secretary:

    My company has only recently completed an agreement with the Imperial Ethiopian government for the development of petroleum in Ethiopia.
    I feel rather certain that you, personally, have been informed with request to this agreement. Unfortunately, the country of Ethiopia is an inland country, with no direct water outlet for export shipping. Should we be successful in discovering oil, we would, of necessity, be required to construct adequate pipe line facilities from Ethiopia to a suitable seaport, as well as an export shipping terminal.
    If we are to proceed with our development program in Ethiopia, it is of vital importance that Eritrea should be recognized as an integral part of Ethiopia, as we would have a suitable seaport outlet.
    Our entire development program will seriously be delayed and affected should Eritrea be under the domination of any other power except Ethiopia. I, therefore, urgently request that your good offices support the demand of Ethiopia with respect to Eritrea.
    For your personal information, I am attaching hereto photostatic copy of the supplemental agreement between my company and the Imperial Ethiopian Government, with respect to construction of pipe lines in outboard outlets, from which you will readily see the importance to this project of the acquisition of Eritrea by Ethiopia.

    Very truly yours
    Signed:
    President.

Image
Image==============

In 1944 Sinclair Petroleum, an American company, signed an agreement with Ethiopia and started petroleum exploration activities in the Ogaden. Until 1951, Sinclair Petroleum drilled 17 exploration wells in the eastern part of the Ogaden basin. The Ogaden sedimentary basin covers 350,000 sq. km. of land. Sinclair Petroleum had noted the existence of oil inflow in one of the exploration wells drilled in Gelladi locality.


==========================================
After the end of World War II, the United Nations conducted a lengthy inquiry regarding the status of Eritrea, with the superpowers each vying for a stake in the state's future. Britain, the last administrator at the time, put forth the suggestion to partition Eritrea between Sudan and Ethiopia, separating Christians and Muslims. The idea was instantly rejected by the Eritrean people— both Christians and Muslims— who wanted total independence and keep their territorial sovereignty intact. The United States point of view was expressed by its then chief foreign policy advisor John Foster Dulles who said:
".... From the point of view of justice, the opinions of the Eritrean people must receive consideration. Nevertheless, the strategic interests of the United States in the Red Sea Basin and considerations of security and world peace make it necessary that the country [Eritrea] be linked with our ally, Ethiopia." —John Foster Dulles, 1952
A UN plebiscite voted 46 to 10 to have Eritrea be federated with Ethiopia which was later stipulated on December 2, 1950 in resolution 390 (V). Eritrea would have its own parliament and administration and would be represented in what had been the Ethiopian parliament and would become the federal parliament. In 1961 the 30-year Eritrean Struggle for Independence began, following the Ethiopian Emperor Haile Selassie's dissolution of the federation and shutting down of Eritrea's parliament. The Emperor declared Eritrea the fourteenth province of Ethiopia in 1962.

===============
Image
Africa Rising
A new spirit of self-reliance is taking root among many Africans as they seize control of their destiny. What are they doing right?
By Johanna Mcgeary and Marguerite Michaels Monday, Mar. 30, 1998 
    ".............By logic, the nation of Eritrea (pop. 3 million) should not exist. The secessionist province's independence fighters ought never to have defeated Ethiopia in their 30-year-long struggle. They were outmanned, outgunned, abandoned or betrayed by every ally; their cause was hopeless. They won by force of character, a unity and determination so steely not all the modern armaments, superpower support or economic superiority of Ethiopia could withstand it. The spirit that saw the Eritreans through 10 years in the trenches of their mountain redoubt at Nakfa has built them a nation from scratch, since independence was finally consummated in 1993................"
    http://content.time.com/time/magazine/a ... -5,00.html

Last edited by Arba_Gorash on 02 Sep 2013, 19:19, edited 1 time in total.

Obama warns on Africa leaders refusing to step down

http://www.bbc.com/news/world-africa-33684721


 
Media caption Barack Obama: "Nobody should be president for life"

US President Barack Obama has ended his visit to Africa by warning the continent will not advance if its leaders refuse to step down when their terms end.
"Nobody should be president for life," Mr Obama said.
He was speaking at the African Union's headquarters in Ethiopia's capital, Addis Ababa, the first time a sitting US president has addressed the body.
Earlier in the trip, Mr Obama visited Kenya, the homeland of his late father.
"I don't understand why people want to stay so long, especially when they have got a lot of money," he told the 54-member AU, an apparent criticism of African leaders who have done just that.
Calling on the AU to ensure leaders respect their constitutions and step down when their term ends, Mr Obama specifically mentioned Burundi, whose president Pierre Nkurunziza has controversially been re-elected for a third term.
"Sometimes you will hear leaders say 'I'm the only person who can hold this nation together.' If that's true, then that leader has failed to truly build their nation."
Mr Obama's address ends his visit to Africa
He said democracy was about more than just holding elections: "When journalists are put behind bars for doing their jobs or activists are threatened as governments crackdown on civil society then you may have democracy in name, but not in substance."
And he joked about his own chances of another term in office, which he is constitutionally barred from seeking.
"I actually think I'm a pretty good president,'' he said. "I think if I ran, I could win. But I can't!"
Grey line
Analysis: Karen Allen, BBC News, Addis Ababa
President Obama reminded me of a steam engine gathering speed as it approached its destination.
He had come to the AU to pay tribute to Africa's huge potential, the vibrancy of its youth and the impressive rates of economic growth in some countries. But he also wanted to deliver another message. Diplomacy was dispensed with and he faced the wind.
He warned that leaders who overstayed their terms in office "were not beyond the law", citing Burundi as an example.
Yet he neutralised the sting with a bit of self-deprecation. Who would want to stay in office for longer? He knows a thing or two about such things.
Some in the audience emerged blinking in disbelief that he had talked with such candour. A university student I chatted to confided that he was afraid of applauding in case anyone was watching him. Such is the level of paranoia and fear of intelligence officials here.
"I was looking around and I was wondering 'should I clap?'" he said. The expression on his face gave it away. It felt good, he said.
Grey line
Mr Obama also called for an end to the "cancer of corruption", saying it was the key to unlocking Africa's economic potential.
The money could be used to create jobs and build schools and hospitals, Mr Obama said.
The rapid economic growth in Africa was changing "old stereotypes" of a continent hit by war and poverty, he said.
But unemployment needed to be urgently tackled on a continent whose one billion people will double in a few decades, Mr Obama said.
"We need only look to the Middle East and North Africa to see that large numbers of young people with no jobs and stifled voices can fuel instability and disorder," he added.
In echoes of his speech in the Kenyan capital Nairobi, Mr Obama condemned the repression of women, saying the "single best indicator of whether a nation will succeed is how it treats its women".
His address to the AU marks the end of his five-day visit to Africa.
The trip has focussed heavily on trade and security, but he also found time in Kenya to meet relatives of his father, including his half-sister Auma.
line
Barack Obama
Obama’s trip to Kenya: 12 things
Savouring Kenya's 'exports'
The scholarship that changed the world
How the US and China compete for Africa

Monday, July 27, 2015

ትንሽ ስለ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋJuly 24, 2015

ትንሽ ስለ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ

/ር ብርሀኑ ነጋ ሰሞኑን የተናገሩትን ስሰማ አስር አመት ወደ ኋላ ተመልሼ አንዳስብ ግድ አለኝ፡፡ ፕ/ሩ ኢትዮጵያም ሆኑ አሜሪካ ወይንም አስመራ ሰላማዊ ተጋይም ሆኑ ሁሉን አቀፍ የትግል ስልት አራማጅ እምነት አስተሳሰባቸው የማይለዋወጥ መሆኑን ለመገንዘብ ቻልኩኝ፡፡

ጊዜው 1997 መጨረሻ ወቅቱ ሕዝብ ይመርጣል ጠመንጃ ያሸንፋል ሆኖ የፖለቲካው አየር የጋመበት ቅንጅትም ወያኔም በየራሳቸው በጭንቅ ውስጥ የነበሩበት ነው፡፡ የወያኔ ጭንቀት ሥልጣኑን ላለማጣት ሲሆን የቅንጅት ጭንቀት ደግሞ ሥልጣን ወይንም ሞት የሚለው ወያኔ ወንበሩን ከሚያጣ ሀገር ቢፈርስ ሕዝብ ቢጨራረስ ደንታ የሌለው በመሆኑ ነገሮች ወደዚህ አንዳያመሩ በማሰብ ነው፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ ሆነው ቅንጅቶች ከመረጣቸው ሕዝብ ጋር ለመወያየት አዲስ አበባ ላይ በየሳምንቱ ቅዳሜና ዕሁድ በየወረዳዎች ስብሰባዎችን ማዘጋጀት ጀመሩ፡፡ ኢ/ር ኃይሉ ሻውል ለተወካዮች ምክር ቤት የያኔው ዶ/ር ብርሀኑ ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ተወዳድረው በተመረጡበት ወረዳ 23 ብስራተ ገብርኤል አካባቢ በተጠራ ስብሰባ ላይ የወረዳው ነዋሪ ባልሆንም ተገኝቻለሁ፡፡ወደ አዳራሹ የመጣ ማንም ኢትዮጵያዊ የነዋሪነት፣ የአባልነት፣ የጎሳም ሆነ የኃይማት ልዩነት ገደብ ሳይደረግበት ስብሰባውን የመሳተፍ ሙሉ መብት ነበረው፡፡
መድረክ ላይ ያሉት ሰዎች ተራ በተራ ንግግር ሲያደርጉ የዶ/ር ብርሀኑ ተራ ደረሰ፡፡ (በወቅቱ በነበራቸው ማዕረግ ነው የምጠራቸው)የዶ/ሩ ንግግር የተሰብሳቢውን ስሜት በመቆጣጠሩ አዳራሹ በጭብጨባ ተናውጧል፡ “ወያኔዎች ያለ ጸብና ቅራኔ መኖር አይችሉም፣እኛ ደግሞ አንጣላቸውም፤የሚጣሉት ሲያጡ ርስ በርሳቸው ይጣላሉ፣… እኛ በምንም መልኩ አነርሱን አንሆንም ፣እነርሱን የሆን እለት ተሸንፈናል ማለት ነው፤” አዳራሹ በጭበጨባ ቀለጠ፡፡ ዶ/ር እየተናገሩ ነው “ ዛሬ እዚህ አዳራሽ የተገኛችሁ ሁሉ ወደየቤታችሁ እንደተመላሳችሁ የተጣላችሁት የኢህአዴግ አባለል ካለ የበደላችሁ እሱ እንኳን ቢሆን እናንተ ይቅርታ እየጠየቃችሁ ታረቁ” ተቃውሞ የለም ድጋፍ ጭብጨባ ብቻ እንደውም አንዳንድ ወጣቶች በድምጽም እሺ ሲሉ ይሰማ ነበር፡፡ እኔ ግን በተመስጦ እያዳመጥኩ በሀሳብ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እየነጎድኩ አእምሮየ እጆቼን ለጭብጨባ ማዘዝ አልተቻለውም፡፡ የዶ/ር ብርሀኑ ንግግር ቀጥሏል፡፡
በየመድረኩ ሆነ በመገናኛ ብዙኃን ከፖለቲከኞቻችን ( በሁሉም ጎራ ካሉት) በአብዛኛው ስንሰማ የኖርነው ልክ ልካቸውን መንገር በሚል አስተሳሰብ የተቃኘ፣ የጠላትነት ስሜት የሚንጸባረቅበት እናሸንፋችኋለን ልክ እናስገባችኋለን ወዘተ በሚል ፉከራ የታጀበ የበቀል ቃና ያለው ወዘተ ንግግር በመሆኑ ነበር የዶ/ር ብርሀኑ ንግግርና አነጋገር በተመስጦ ያነጎደኝ፡፡
የዶ/ር ብርሀኑ ንግግር የቅንጅት አመራር አባል ያውም በምርጫ አሸንፎ ተሸንፈሀል የተባለ ፖለቲከኛ ሳይሆን ከፈጣሪ የተላከ በአንድ እጁ እየሱስ ክርስቶሰ የተሰቀለበትን የፍቅርና የነጻነት መሰቀል በሌላ እጁ ቃሉ የተጻፈበትን ቅዱስ መጽኃፍ ይዞ በፈጣሪ ስም የሚያስተምር የኃይማኖት ሰባኪ ነበር የሚመስለው፡፡
ከሀይማኖት ሰባኪም ስለ ፍቅር ስለ አንድነት ስለ ይቅር ባይነት ለመስበክ ተዘጋጅቶ የመጣ የዚህችን አለም ህይወት አሸንፎ ራሱን የሰጠ መምህር ነበር የሚመስሉት፡፡
ፖለቲካ መጠላላት በሆነበት ሀገር፤ አይደለም በአላማ ተለይቶ የሚታገልን በአመለካከት የተለየን ካላጠፉ አንቅልፍ የማይወስዳቸው በበዙበት ዘመን፤ የፖለቲካው ጨዋታ ጥሎ ማለፍ የሰዎቹ ባህርይ ጥላቻና በቀል የሚንጸባርቅበት በሆነበት ከዚህም በላይ ስሜት ፖለቲካውን በተቆጣጠረበት በዛ ወቅት ከዶ/ር ብርሀኑ አንደበት የተደመጠው ንግግር ቀልብ የሚስብ ብቻ ሳይሆን ሁለንተናን የሚገዛ ነበር፡፡ እናም ፈጣሪ ይህችን ሀገር ሊታረቃት ይሆን! ከመገዳደል አዙሪት ልንወጣና የዴሞክራሲ ቀንዲል ልናይ ይሆን!ወዘተ እያልኩ ራሴን እየጠየኩ ተስፋና ጨለማ በአንድ ላይ እየታዩኘ ነበር በሀሳብ የነጎድኩት፡፡
ግና ተስፋዬ እንደ ጉም ሲበን ወራት አልተቆጠሩም፡ እኚህ ፍቅርን የሰበኩ ይቅር ባይነትን ያስተማሩ የአንድ ሀገር ልጅነት ከፖለቲካ አመለካከት ልዩነት በላይ መሆኑን በተግባር ለማሳየት የጣሩ ሰው ወንጀለኛ ተብለው ከትግል ጓዶቻቸው ጋር ታሰሩ፡፡ ከመታሰራቸው በላይ ዘር ማጥፋት ሀገር ክህደት ህገ መንግሥታዊውን ሥርዓት በኃይል ለመጣል መሞከር ወዘተ በሚል መከሰሳቸው የሀገራችንን መጻኢ እድል ጨለማነት በበግልጽ ያሳየ ነበር፡፡
ዶ/ር ብርሀኑ በቃሊቲ ወህኒ ቤት ሆነው በጻፉት የነጻነት ጎህ ሲቀድ በተሰኘው መጽኃፋቸው የገለጹት ከላይ የገለጽኩትን እምነት አመለካከታቸውን የሚያንጸባርቅ የሰላም ደቀ መዝሙርነታቸውን የሚያሳይ ለመሆኑ ያነበበ ሁሉ የሚያረጋግጠው ይመስለኛል፡፡ ከሁለት አመት የእስር ቆይታ በኋላ አሜሪካ ሄደው ወያኔ በሰላማዊ ትግል ብቻ ስልጣን አንደማይለቅ በተግባር አረጋግጠናል፤ነጻነት ከተመኘን፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ አንባገነን አገዛዝ አንዲላቀቅ የምንፈልግ ከሆነ ትግሉ ሁሉን አቀፍ መሆን አለበት ብለው ግንቦት 7ን ሲመሰርቱም ጡንቻ ወለድ የሆኑ ቃላት አልተሰሙባቸውም፡፡ አሸባሪ ተብለው በሌሉበት ተከሰው ሞት ቢፈርድባቸውም የጥላቻና የበቀል ስሜት አልተንጸባረቀባቸውም፡፡
እነሆ ልክ ከላይ የገለጽኩትን ቃል በተናገሩ አስር አመት (በምርጫ ማግስት መሆኑም ያመሳስለዋል) የጠመንጃውን ትግል ለመምራት ወደ አስመራ ሲያመሩ፤ ..ደም መፋሰስ ውስጥ ሳንገባ የሀገራችንን ችግር ቁጭ ብለን በመነጋገር ብንፈታ እንወድ ነበር.ይህ ጦርነት ወደንና ፈቅደን ሳይሆን በወያኔ እብሪት ተገደን የገባንበት በመሆኑ ገደልን እያልን የምንፎክርበት አይደለም፡፡ ከሁለታችንም የሚሞተው ወገን በመሆኑ እናዝናለን፤ አሁን ቢሆን ወያኔዎች ለድርደር ፈቃደኛ ከሆኑ እኛ ጦርነት ምርጫችን አይደለም፤ወዘተ ማለታቸውን ሰማን፡፡ (ቃል በቃል አልጠቀስኩ ይሆናል) ይህም ዶ/ር ብርሀኑ የሚናገሩት በወቅታዊ ትኩሳት እየተገፉ፣ምን ብናገር አድማጭ ጆሮ አገኛለሁ በሚል ስልት ሳይሆን የሚያምኑበትን ለመሆኑ ይህ በትንሹ በአስር ዓመታ ውስጥ ከነገሮች መለዋወጥ ጋር ያልተለወጠው ንግግራቸው በቂ ማረጋገጫ ይመስለኛል፡፡
በዚህ ሁሉ ሂደትና አመታት ያልተለወጠ አላማና እምነት ከዚህ በኋላ ይለወጣል ተብሎ ባይሰጋም በእምነት ዓላማቸው እንደጸኑ ለድል እንዲበቁና በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ከፋች እንዲሆኑ ፈጣሪ ይርዳቸው፡፡
ነጻነቴን የምንል፤ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊት ሀገር ሆና ለማየት፣ (ለእኛ ባትደርስ ለልጆቻችን) የምንመኝ ዜጎችም በምኞትና በፍላጎት ብቻ የሚገኝ አይደለምና የዶ/ር ብርሀኑን ባታደልም በያለንበት በምንችለው ድጋፍ መስጠት ይገባናል፡፡ካልሆነም አደናቃፊ ከመሆን መቆጠብ፡፡

ህወሓት ለሽብር ጥቃት ተዘጋጅቷል፤ እንጠንቀቅ!አርበኞች ግንቦት 7

 Ginbot 7

ህወሓት ለሽብር ጥቃት ተዘጋጅቷል፤ እንጠንቀቅ!

July 24, ,2015
ዘረኛውና ፋሽስቱ የህወሓት አገዛዝ፣ በሕዝባዊ ኃይሎች ላይ ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ተቀባይነት እንዲያገኝለት የሽብር ተግባር ፈጽሞ በአርበኞች ግንቦት 7 ላይ ለማላከክ ወስኗል። እንዲህ ዓይነቱ እኩይ ተግባር ህወሓት ስልጣን ከመያዙ በፊትም በኋላም ሲያደርገው የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ህወሓት እንዲህ ዓይነቱ  ኢሰብዓዊና ዘግናኝ ተግባር ለመፈፀም የሚያስችሉ እኩይ ስለልቦና እና ልምድ አለው።
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ በቅርቡ የጀመረው የነፃነት ትግል የፈጠረበት መደናገጥ ለመሸፈንና ንቅናቄውን በኢትዮጵያ ሕዝብና በዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብ ለማስወገዝ ያግዘኛል ብሎ ያመነበት ይህን ዘግናኝ ሴራ ከሳምንት በፊት ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጁቱን አጠናቆ የነበረ ቢሆንም በወቅቱ የነፃ ሚዲያ አባላት ደርሰውበት ለሕዝብ ይፋ በማድረጋቸው እንዲዘገይ ተደርጎ ነበር። አሁን በደረሰን መረጃ ደግሞ ሴራው ከበፊቱ በባሰ እና ይበልጥ አውዳሚ በሆነ መጠን ተግባራዊ ለማድረግ የህወሓት “ስውር” መንግሥት ወስኗል። በዚህም ምክንያት ይህ የማስጠንቀቂያ መግለጫ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በማያሻማ ሁኔታ እንዲገነዘብ የምንፈልገው ሀቅ የሚከተለው ነው። አርበኞች ግንቦት 7  በደረሰው መረጃ  መሠረት ህወሓት በሰላማዊ ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ወስኗል። የእቅዱ ዓላማ ዘግናኝ እርምጃ በንፁሃን ዜጎችና ሕፃናት ላይ በማድረስ “የሽብር ጥቃቶች ሰለባ” ነኝ በማለት የኢትዮጵያ እና የዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብ አዘኔታ ማግኘት ነው። የዩ. ኤስ. አሜሪካ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን የሚጎበኙ መሆኑ ደግሞ ይህንን እቅድ ተግባራዊ የማድረግ ጉጉቱ እንዲጨምር አድርጓል። ስለሆነም ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ በህወሓት የሽብር አደጋ ውስጥ ነች። የቦሌ ዓለም ዓቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ እና ወደዚያ የሚያደርሰው መንገድ፣ የአፍሪቃ ኅብረት ጽ/ቤት እና የአሜሪካ ኤምባሲ ህወሓት በሽብር ጥቃት ዒላማነት ከመዘገባቸው ውስጥ ቀዳሚዎቹ ናቸው።
አርበኞች ግንቦት 7 በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚቃጡ የሽብር ጥቃቶችን መቃወም ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ተባብሮ ያመክናል። ይህ በህወሓት የተደገሰልንን የሽብር ጥቃት ማምከን ይኖርብናል። እኩይ እቅድን አስቀድሞ አውቆ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ አንድ ዓይነተኛ የሽብር መከላከያ ዘዴ ነው። በዚህ ረገድ በአገዛዙ ውስጥ ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ባለውለታዎች ናችሁ።
የእያንዳንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሕይወት መለኪያ በሌለው መጠን ውድና ክቡር ነው። በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ዜጋ የህወሓትን እኩይ ሴራ ተገንዝቦ ራሱን፣ ቤተሰቡንና አካባቢውን ከጥቃት እንዲጠብቅ አርበኞች ግንቦት 7 በጥብቅ ያሳስባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

TPLF Security Forces Terrorist Plot in Addis Ababa Leaked

 pg7-header-4

TPLF Security Forces Terrorist Plot in Addis Ababa Leaked

July 24, 2015
Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy has received credible reports that the fascist regime in Ethiopia has made intricate plans to detonate explosives and blame Patriotic Ginbot 7 for its own terrorist acts.
While we had received the leaked information of the sinister plans being hatched by the TPLF politburo members a few weeks ago, the pending visit of the U.S. President to Ethiopia have made it imperative for the TPLF regime to carry out the heinous crimes in the next few days.
We would like to inform the Ethiopian people and the international community that TPLF has finalized plans to carry on terrorist acts at Bole International Airport, along the major highway leading to the airport, at the headquarters of the African Union and the U.S. Embassy.
The TPLF minority regime is, of course, no stranger to planting bombs in Ethiopia’s capital Addis Ababa in a bid to frame its real and perceived political enemies and brutally murder innocent Ethiopians.
Massive leaks of secret files by WikiLeaks has exposed the late Prime Minister Meles Zenawi as the terrorist-in-chief. In a report from 2006 marked “Secret; Subject: Ethiopia: Recent Bombings Blamed on Oromos Possibly the Work of Government of Ethiopia” “Classified By: Charge [d’Affairs] Vicki Huddleston”, “An embassy source, as well as clandestine reporting, suggests that the bombing may have in fact been the work of the Government of Ethiopia security forces.” (Cable referenceid:#06ADDISABABA2708.)
Patriotic Ginbot 7 strongly condemns the senseless brutality and the unconscionable use of terror by the rogue regime in Ethiopia to garner international support. Its utter disregard for the sanctity of human life and the Ethiopian people’s well known reputation as a peaceful and cultured people who abhor violence is truly horrifying.
The very fact that this dying regime is willing to kill, maim and cause mayhem in Addis Ababa to maintain power  at any cost and in the face of a shrinking political base is a clear indication that it has lost any legitimacy to rule Ethiopia.
pg7-header-4
Patriotic Ginbot 7 would like to remind the deeply traumatized people of Ethiopia who are knowledgeable of the sinister motives of the fascist regime to be ever so vigilant and take every precaution for their individual and collective safety.
It is also time for the United States and the international community to realize that a terrorist regime willing to use violence to cling to power will never be a credible partner in the “war against terror.”
 

Friday, July 24, 2015

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበ

July 19, 2015
/ ብርሃኑ ነጋ ከቃሊቲ እስር ተፈተው ቀደም ሲል ይኖሩበት ወደነበረው አሜሪካን ሀገር ከተጓዙ በኋላ አፍታም ሳይቆዩ ነበር የሁለገብ ትግልን አስፈላጊነት መናገር የጀመሩት። / ብርሃኑ ወዲያውም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ ከሌሎች ሃሳባቸውን ከሚጋሩ ስመጥር ፖለቲከኞች እና የለውጥ አራማጅ ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄን መሰረቱ፣ በወቅቱ / ብርሃኑ የእርሳቸውን እና በግንቦት 7 ዙሪያ የተሰባሰቡ ጓዶቻቸውን ቁርጠኛነት ሲያስገነዝቡዘረኛውን የወያኔ አምባገነን አገዛዝ ከህዝብ ጫንቃ ላይ ለማውረድ የማንፈነቅለው ድንጋይ አይኖርምነበር ያሉት።



https://www.youtube.com/watch?t=16&v=b-upNBStOVM

ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ 7 ጠንካራግንቦት የተዋጊ ሃይል ማቋቋም የቻለ ሲሆን ለጥቆም ቀደም ሲል ጀምሮ ወያኔን ማስወገድ የሚቻለው በሃይል ብቻ ነው በማለት መስዋዕትነት በመክፈል ላይ ከነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጋር በመዋሃድ የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄን መፍጠር ተቻለ።
ዛሬ በወያኔ እጅ ወድቆ የሚገኘው በሳሉና ቆራጡ ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እስካሁን ግንቦት 7 በተጓዘባቸው የስኬት ጎዳናዎች ሁሉ አሻራው እንዳለበት በቅርብ አብረውት ሲታገሉ የነበሩ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ይመሰክራሉ።
በወጣት አርበኞች የተገነባውና እራሱን ለውጊያ ብቃት ሲያደራጅ የሰነበተው አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ ክንዱን ማሳረፍ በጀመረ ማግስት ነው እንግዲህ የንቅናቄው መሪ / ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም አመራሮች በአካል የትግሉን ጎራ ለመቀላቀል ወደ ሜዳ የወረዱት።
የዶ/ ብርሃኑ ነጋንና የሌሎች አመራሮችን የትግሉን ጎራ በአካል መቀላቀል አስመልክቶ ንቅናቄው ባሰራጨው አጭር መልዕክት እንደገለጸው፣
የተቀደሰ አላማን ያነገብን እርኩስ አላማን በሚያራምዱት ላይ ድልን እንቀናጃለን፣ / ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም የንቅናቄው አመራሮች የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ነጻነት፣ የፍትህ እና የዴሞክራሲ ጎዳና እንደሚመሩት ጥርጥር የለንምብሏል።
አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ቀጥሎ ባለበት ሁኔታ የዶ/ ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም የንቅናቄው አመራሮች በአካል ከአርበኞቹ ጎን መገኘት ከፍተኛ ሞራል እና መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአለም አቀፍ ህብረተሰብ ዘንድ ከፍተኛ ተደማጨነት ያላቸው የሰላምና የዴሞክራሲ ግንባር ቀደም ታጋይ ናቸው። ይህን ችሎታቸውም ኢትዮጵያን ወደ ነጻነት ለመውሰድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Monday, July 20, 2015

Junk Journalism: Zehabesha or Ay-Habesha? July 20, 2015.by Teshome Debalke

The tragedy of the State of Media and journalism in Ethiopia is known as TPLFs propaganda mill factory that transmits in multiple languages in the wishes of TPLF warlords. The self-proclaimed Tigray people representative led Apartheid regime of the Federal ethnic Nation and Nationality of Ethiopia is feeding our people lookalike news, political entertainment and propaganda drama — too busy trying to rewrite everything, including history to prolong the Apartheid system where its very survival depends on. Without it; TPLF is nothing but gangs of ethnic warlords feasting on the expense of and riding on the back of the people of Ethiopia as design by their enablers.

Far away from the Apartheid regime controlled territory of Ethiopia in the free world where the real battle is fought to win the hearts-and-minds of the people of Ethiopia that run away from tyranny. One would think; the free world is where the good, the bad and the ugly Medias (junk verses real journalism) would be sorted out; not by how much cut-and-paste news they provide from other sources or cook up their own imagination but, engage in critical investigative reporting that matters to the people they claim to serve but, It wasn’t meant to be. An average Media in Diaspora today is nothing more than Coffee Shop chitchat (Tela BetWore) pasted on the unfortunate cyberspace that was invented to revolutionize information transmission.
Sadly to say Ze Hbesha joined the rank and file of the sorry State of Media to force us asks Ze Habisha or Ay Habisha. Its latest press coverage of the lone ranger Ethiopian Review editor and journalist wannabe Elias Kifle apologizing ‘Ethiopians’ for his past association with Shabia where unidentified individuals clapping their hands on the background. It reminded me of TPLF’ that is known to fabricate drama and make it look like real.
When two ‘Medias’ editors collude for one-and-only thing and make it look like another it is called junk journalism. But, when they insult the intelligence of the people they want to reach it is crime of reducing the public to their level. I noticed many Medias, political parties and civic organization doing the same.
The 1st Media (ER) editor giving a press statement and the second Media (ZH) editor making a video with clapping hands heard on the background without identifying ZH reporter nor showing the people clapping their hands and without asking the ER editor and the supposedly audience hard question it is gorilla journalism at best. What did TPLF’s junk journalist do different than the two clown journalist wannabes doing?
Looking at it positively, it reminds me of what the British playwright and screenwriter Sir Tom Stoppard said;
“Junk journalism is the evidence of a society that has got at least one thing right, that there should be nobody with the power to dictate where responsible journalism begins”
Therefore, junk journalism is a good thing but, what is missing in our society is sorting out junk journalism from real journalism. Understandably, it is a monumental task when the government is a factory of junk journalist and spending substantial resources to make sure no real journalism see the day.
As they say ‘you get what you put in’; like junk food that fills your stomach and start working in your vain pumping its chemical residue in your body to make you fat and ugly, junk journalism does the same to your brain pumping its fairytale residue to make you irrational enough to believe you are a journalist for cutting-and-pasting anything.
The legendary Ethiopian artist Telahun Gesese said; ‘አቅምን አውቆ መኖር ታላቅ ችሎታ ነው’ or as our people say ‘አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል’ if only we could listen.
A bit of an advice is in order to those who think they are journalists-Medias
The British newspaper and publishing magnate Lord Northcliff put it this way “News is something someone wants suppressed. Everything else is just advertising”
In that note, all Medias should be mindful; Ethiopians are sick and tired of junk journalism (advertisement) that infested the Woyane occupied nation of Ethiopia and migrated to the free world to feed us junk information.
That said; gone are the days of claiming you’re journalists — pasting advertisement. The staged ER editor empty apology was directed to undermine Ginbot 7. ZeHabesha gorilla coverage was advertisement was directed to TPLF’s apologists nothing to do with the people of Ethiopia, nada. They both proved to qualify for junk journalism and for that we have Woyane; we don’t need more junk journalism. Either you do it right or don’t do it at all. Advertising is a good thing as long as we know who the advertisers are or not presented as journalism.
What we need is real journalism. The question is what is real journalism?
The early 20th century American Journalist Walter Lippmann once said“There can be no higher law in journalism than to tell the truth and to shame the devil.”
Ethiopians don’t need advertisement of wishes we need journalism to follow the higher law of ‘telling the truth and shaming the devil’.
There two ways junk journalism develops; to give comfort to the devil or to piggyback on the devil to advertise something else. I am not sure which one the two clowns represent. But, what I am sure is they are practicing junk journalism.
But, there is hope to graduate from junk journalism to the real deal. First respect to the truth, yourself and the profession goes a long way. Second, breaking the back of the ‘devil’ requires digging to the roots of the truth not skirting it.
Wanted man: Biniam Tewolde
Wanted man: Biniam Tewolde
For example, the recent revelation the Woyane Information Network Security Agency (INSA) hacking team led by ‘Biniam Tewolde’ (pictured) from Defence Engineering College, Berhanu Girmay Desta from “University of electronic and technology of China (UESTC), Seblewoin Tsegaye Demessie Hunan University- Computer Science and Technology and Godif Nigus Tesfau with unknown background was the breaking news that should have been followed to their networks of agents in diaspora.https://wikileaks.org/hackingteam/email … archresult
This high priority news that required follow up and deep investigation to find out the agents of Woyane from Asia to North America would have gotten the devil its due to run. But, diversion to something else is what we see on most Medias including ER and EthioMedia. ZeHabisha is going in the same direction too.
Running out of diversion to face the truth; on July 20 EthioMedia featured;Berhanu Nega gives up life in America to lead uprising against tyranny in Ethiopia (Ethiomedia). When you open the link it reads
Reading the title I am not sure what EM editor that spends most of his adult life as ‘journalist trying to communicate to the public. The first one appears he is trying to say the good Dr. gave up in life all together and the declared armed struggle is also reported as uprising. On the second title it is not life he gave up but ‘comfy’ and not uprising but insurrection. It appears he is constipating to come up with the right word to communicate what he wanted to say.
Then came the led paragraph;
SEATTLE – Berhanu Nega, leader of Patriotic Ginbot 7, on Saturday bid farewell to his career as an economics professor here in America to lead a struggle in Africa against the despotic regime in Addis Ababa, Ethiopia.
Here is junk journalism at its best– stating with the title. Dr. Berhanu is not new for the struggle or ‘giving up ‘comfy’ before. He also led the arm struggle or what EM Abrha Belai referred as ‘insurrection’ from the day G7 was formed. In fact, Dr. Berhanu and his compatriots formed G7 specifically to wage war on TPLF and are the only group that tried both peaceful and armed struggle against TPLF led Apartheid regime of Ethiopia.
A few weeks ago, EM refused to source ESAT’s news regarding Patriotic G7 military attack on Woyane troops. Instead it put out diversion news titled ‘Eritrean and Ethiopia; war again?’ (It no longer is posted on front page) with a video link of the Woyane puppet PM warning Shaibia to undermine the movement anyway possible.
A year ago EM sourcing Elias of Ethiopia Review reported Patriotic- Ginbot 7 leaders Andargachew’s kidnaping was the work of Shaibia with no success. A year later when the struggle intensifies and bullets start flying, EM and ER couldn’t swallow the truth to come up with yet with another bizarre reports.
No one knows if Dr. Berhanu told EM editors that he is leaving his ‘comfy’ life for good or not. There is no way of knowing whether Birhanu told EM of Bilai he is going permanently or EM editor made it up to fit his imaginations or wishes either. It is not also clear Dr. Berhanu discussed his career goal with EM editor or if EM editor understands what a career in academia means. I am not sure of what was all the fuss about whether Dr. Berhanu is economics professor or not or in America or Timbuktu to lead an armed struggle in Africa or Ethiopia either. He reminded me TPLF’s apologists referring Ethiopia as East Africa or Horn of Africa for reason I believe is to confuse Ethiopians.
What is giving contemporary journalists constipation to behave like junk journalists?
An amateur like me can easily figure out without blinking an eye. Here is my take; they all have agenda other than freeing our people from the ruling Apartheid tyranny and or potential future tyrants.
As they say; you can run but can’t hide. And as I said before ESAT is chocking them from spitting out the truth. If that is not the case I can’t find anything that made our contemporary Medias having seizer when they hear the truth.
Ethiopians are watching whether Medias are with the people of Ethiopia or sucking up for one or other interest groups.
Sooner or later they will shape up or shipped out, I guarantee it.

Sunday, July 19, 2015

A message from Patriotic Ginbot 7: Dr. Berhanu Nega joined his comrades in the ground

 

Dr. Berhanu Nega

A message from Patriotic Ginbot 7: Dr. Berhanu Nega joined his comrades in the ground

July 19, 2015
Dear Ethiopians:

Dr. Berhanu Nega
As you already know, our struggle has reached a crucial milestone in which our comrades have begun paying the ultimate sacrifice in battling the TPLF-led regime in Ethiopia.
Armed struggle was never a method of struggle of our choice. The TPLF-regime has closed all peaceful avenues and has left us with the choice to become enslaved in our home land or to fight by any means necessary.
Therefore, the man who Ethiopians have once peacefully elected as mayor of the capital of Ethiopia, Addis Ababa, Dr. Berhanu Nega, chairman of Patriotic Ginbot 7, has joined his comrades in arms on the ground where the soldiers of Patriotic Ginbot 7 have begun waging the battle to free Ethiopia.
As we have confidence in the victory of good over evil, we have no doubt that Dr. Berhanu Nega and other leaders of our organization will effectively lead our organization and our beloved people to freedom, justice and democracy!
Victory to the Ethiopian people! Patriotic Ginbot7

Breaking News Dr Berhanu nega arrived in Eritrea

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy Chairman Dr Brhanu nega arrive in Eritrea. according to the movement higher official confirmation  Dr Brhanu is in Eritrea to engage in the arm straggle that the movement embark on since last week .


click here
https://www.youtube.com/watch?t=22&v=P_5E20O05XE

Saturday, July 18, 2015

ኢትዮጵያ የመበታተን አዳጋ ላይ መሆኗን የሚያሥገነዝበው ዶክመንተሪይ ቪድዮ(Documentary video) ይፋ ወጣ ፣2007

ኢትዮጵያ የጥቁር  ህዝብ የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን  በምራብያውያን  አፍሪካን መቀራመት(scramble of Africa) ሴራ ሥምምነት  በጀግኖች አባቶቻችን ፍጹም የአርበኝነት  ተጋድሎ አሳፍረው በመመለሳቸው ዛሬ በሀገር በቀል ባንዳ ቅጥረኞች አማካኝነት ይህችን ታላቅ ሀገር  ለማዳከም ኢትዮጵያ  በምራብውያን ጌቶቻቸው የርጅም ጊዜ የኢትዮጵያን  የማህበረሰብና ሥነልቦና ጥናት ውጤት መሰረት አምሀራ ብሄረሰብና የኦርቶደክስ ተዎህዶ እምነት ማጥፋት ወይም ማዳከም መሰረተ ሀሳብ የጥናት ውጤት መሰረት   የትግራይ ነጻ አውጭ(TPLF)  ከዛሬ 40 ዓመት በፊት የጻፈውን 1968ዓ፣ም ማንፊስቶ፣(TPLF Manifesto.1976G.C)    ዛሬም አራት ኪሎ  ሸምቆ በማሥፈጸም በመፈጸም ላይ ይገኛሉ፥ በመሆኑም ሀገራችን ዛሬ ደረሰቻበት ደረጃ ላይ ደርሳለች ሥለዚህ ታላቋ ሀገራችን ከመፍረስ መታደግ ያአለብን እኛ የእዚህ ትውልድ  ኢትዮጵያውያን  መሆናችንን  ተገንዝበን  የዜግነት ግዴታችንን እንዎጣ 

ይህ ሥራዓት ከቀጠለ ኢትዮጵያ የመበታተን አዳጋ ላይ መሆኖን የማሳየው ዘጋቢ ፊልም ከዚህ በታች የተመከተውን  ቪዶ አድራሻ በመጫን እንዲመለከቱና  እኒዳሰራጩ በአክብሮት ተጋብዘዋል(you arekindly invited to see the documentary video entitled : Documentary:U.S.  policy :Ethiopia a failed state) and share the document for others.


ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

click the link below

https://www.youtube.com/watch?v=ikVl6auH83w