Sunday, February 23, 2014

ለ አብራሪው ( በ ይግዛው እያሱ)



ቢመረው ቢከፋው ግፍ አላይም ብሎ 
ጨርቄን ማቄን ሳይል ካገር ወጣ ጥሎ።
ለሙያው ሊታመን ምሎ ቢቀጠርም
ስራን በነጻነት ሊያገኘው አልቻለም።
የህዝብ ብሶት መከራ በሱ ተመስሎ
ላይመለስ ሸኘው ድምጽ አሰማ ብሎ።
ይህ የህዝብ ድምጽ ነው የአንድ አገር ዜጋ
በግፍ የሚገረፍ በወያኔ አለንጋ።
22 ዓመት ህዝብ ከህዝብ ከፋፍለው
አንዱን ባንዱ አዝምቶ አንገት የሚያስደፋው
የወያኔን መንግስት የግፍ አገዛዙን
ለዓለም ሊያሳውቅ ነው በመጥላት እራሱን።
በጣም በተሻለ መኖር እየቻለ
ለሆዱ ሳያድር ነጻነቴን ያለ
የቁርጥ ቀን ጀግና እንደ ሀይሌም የለ። (ሀይለመድህን)
የዓለም መንግስታት ይህን ይወቁልን
ለሀይለመድህን አበራ ጥሩ ፍርድ ይስጡልን።
ወያኔ እንደሚለው አሸባሪ አይደለም
ወያኔ እንደሚለው አገሩን አልከዳም
ወያኔን ግን ከድቷል ህዝብን አስቀድሞ
ራሱን ሻማ አርጎ የወገን ድምጽ ሆኖ።
ቢሞትም አይቆጭም ቢያስሩትም ይፈታል
ያጎነበሰን ህዝብ አንገት ቀና አድርጓል።
ለተበደለው ህዝብ ድምጹን አሰምቷል።
ሞት አዲስ አይደለም በኢትዮጵያ ምድር
ሁሉ ሚከፍለው ነው ለወያኔ ግብር።
የሱም ተራ ደርሶ ለእርድ ሳይዘጋጅ
በሰማይ እያለ እግዚአብሔር እረድቶት
እራሱ አመቻችቶ ዘዴ ፈጠረለት
ህዝብን አድን አለው ሂድና ጩህለት።
ቃሉን ተቀብሎ ለራስ ሳያዳላ
ጄኔቭ ገባ ሀይሌ ለመፈለግ መላ።
መላ ባንተ ይገኛል ድካምህ አይቀርም
የዓለም መንግስታት ይህን ዝም አይልም።
በቅርብ ታየዋለህ ካንተ ፍርድ ጀምሮ
የኢትዮጵያ አምላክ አይጥልህም ጥሎ።

maleda times | February 21, 2014 at 8:16 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-3DX

Monday, February 3, 2014

9.34 kilos of cocaine in stomach; tummy-ache leads police to 5


Nigerians caught with 441 cocaine capsules in transit lounge of Abu Dhabi AirportBy Mohammed El Sadafy
maleda times | February 3, 2014 at 9:10 am | URL: http://wp.me/p2gxmh-3kH


The give people arrested at Abu Dhabi Airport for drug trafficking and the capsules of cocaine found in the stomachs and intestines.
Five Nigerians have been arrested at Abu Dhabi International Airport during the past 12 days for trying to smuggle 441 capsules weighing a total of 9.34kg of cocaine in their stomachs.
Police said the five men were seen very tired and confused in the transit lounge of the airport.  One of them was suffering from stomach pain.
Colonel Dr Rashid Mohammad Bu Rasheed, Director of Criminal Investigation, said the arrested people had arrived in Abu Dhabi from Sao Paulo in Brazil and Lagos, Kano and Abuja in Nigeria. They tried to change their flight to mislead the police, he added.
He also said the drug traffickers intended to leave the pills in their stomach for more than 24 hours. Their lives could have been at risk even if just of the capsules burst inside their bodies, he added.
Comment   See all comments

በሀገራችን የሉዓላዊነት ጉዳይ እንኳን እሥራት ሞትም ይምጣ(ጌታቸው ዘብ-ጎ )


አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንደሚባለው አበዋዊ የአነጋገር ዘይቤ ሰሞኑን የሰላማዊ ፓርቲ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ያለው ሥርዓት ገዥ ኃይል(ህወሃት) የኢትዮጵያ ሀብት የሆነውን ለሙንና ውሃ ገቡን በአጭር ጊዜ ምርት አምርቶ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ችግር ሊቀርፍ የሚችለውን በርካታ የማሽላ አይነቶች፤ሰሊጥና ኑግ፤ጥጥና የሙጫ ዛፍ በብዛት የሚገኝበትን ለሀገር ውስጥ ፍጆታም ምሰሶ የሆነውን ሕዝብ እንደ መተንፈሻ ሳንባው የሚተማመነውንና እንደ ዐይኑ ብሌን የሚመለከተውን ሰፊውን የምዕራብ ኢትዮጵያ ክቡር ግዛት ለሱዳን ለመስጠት ከሕዝቡ በስተጀርባ በድብቅ ድንበር ማካለል ፊርማ በመፈራረሙ ምሥጢሩን ለህዝብ እናጋልጣለን በማለት የሰላማዊ ፓርቲ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይደናቀፍ በመስጋት ስከታተል ነበር። ትዕይንተ ሕዝቡን ለማካሄድ የሚደረገውን ቅስቀሳ በማዎክ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ላይ ይህ ነው የማይባል ወከባ እሥራት ተፈጸመ። ሕዝብ በዚህማ አትምጡብን አይቀሬ ነው ብሎ ከወጣ በኋላ መንገዶችን ከመስቀል አደባባይ ወደ አራዳ ፤ከመስቀል አደባባይ ወደ ብልኮ ፤ ከመስቀል አደባባይ ወደ ቼቸላ በትራፊክ በመዝጋት ሕዝብ ታግቶ እንደዋለ ከዘ-ሐበሻ ዘገባ ለመረዳት ችያለሁ። ዘ- ሐበሻ ትልቅ ታሪክ ሰርታለች ሁላችንም እናመስግናት። እናም ሰሞኑን ርቄ የምገኝ ብሆንም ከዚህ የተፈረደበት ሕዝብ አብራክ የተፈጠርኩ በመሆኔ ወላጆቼ ጥሬ ቆርጥመው አስከብረው ያቆዩዋትን ሀገሬን የበሉበትን መሶብ የሚደፉ ሰብአዊነትና ርህራሄ የበማይሰማቸው እምብርት የለሽ ሆዳሞች የተፈጸመው ተግባር እጅግ አሳዝኖኛል። በመሠረቱ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲወጣ የተደረገው በደሙና በጥንቱ አስከብሮት የኖረው መሬቱ ታሪካዊ ጠላት ለሆነችው ሱዳን በድብቅ ሊሰጥ በመሆኑ እንጅ ድንጋይ ለመወርወርና ጥይት ለመተኮስ ቢሆንማ መንገዱ ይህ አልነበረም። ያን ህወሃቶች ከዚህ አሳፋሪ ተግባራቸው የማይመለሱ ከሆነ ወደፊት የምናየው ይሆናል።
በህዝብ ላይ ለተፈጸመው ድርጊት ኃላፊነቱን የሚወስዱት እነማን እንደሆኑ ጠንቅቄ ስለማውቃቸው ጊዜውን ይጠብቅ በማለት የቀድሞ የደርግ ፖሊስ የነበሩ ደርግ ከወደቀ በኋላ አዲሶቹ ገዥዎቻችን ቦታውን ሲሸፍኑ ፖሊስ ከጨዋታ ውጭ ሆኖ ነበር። የኦሊሶችና የቤተሰቦቻቸው ሁኔታ ታይቶ በሕዝብ ላይ ግፍ ያልፈጸሙትን እየተገመገሙ እንዲመለሱ ሲደረግ ከክልል አንድ ሰው ጋር በመሆን የደርግ ፖሊስ የነበሩትን በጎንደር ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲመለሱና የድሮ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ካደረጉት አንዱ ስለነበርኩ ፖሊሶች ሕዝቡን መተባበር ሲገባቸው አግቶ ማዋልና የህዝቡ ስሜት እንዲታፈን ማድረግ ከትናንትናው አለመማር ይሆናል። እንኳን ይህ ውስጡ የነቀዘ ምስጥ እንደበላው አገዳ ባዶውን የቀረ ቅጥረኛ ገዥ ቡድን ማንም ቢሆን የህዝቡን ስሜት በኃይል አፍኖ በመያዝ የሥልጣን ዘመኑን ማራዘም አይችልም።!! «ለዚያውም ህወሃት ህወሃት እኮ እንኳን ዘንቦብሽ እንዲያውም የተባለ ነው።»ከዚህ ላይ አንድ የሚያሳዝነኝ ነገር ቢኖር የጎንደር ሕዝብ ሩህሩ ፤ትዕግስተኛ ፤ አርቆ አሳቢ ፤ለጋስና ተካፍሎ የሚያድር ሕዝብ ነው። ለምሳሌ ዛሬ ተመልሰው መጥተው ሊሰፍሩ ኤርትራውያን ውጡ በተባለበት ወቅት ሁሉም ኤርትራዊ ታፍሶ ፖሊስ መምሪያ ግቢ ውስጥ ነበር። ጎንደሬዎች ኤርትራዊ ወገኖቻቸውን ወደ አዲሲቱ አገር ለመሸኘት የመጡት ድንጋይ ይዘው አልነበረም። እንጀራ በመሶብ፤ወጥ በትልቅ መገፈጅ፤ ጠላ በመንቀልና በገንቦ ተሸክመውና አሸክመው እያለቀሱ ነበር ኤርትራዊ ወገኖቻቸውንና አብሮ አደጎቻቸውን የሸኙዋቸው። ታሪክ ለመተረክ ፈልጌ ሳይሆን በአይኔ ያየሁትና በቦታውም ስለነበርኩ ነው። በአጋጣሚ አንድ የአክስቴ ልጅ የተባበሩት መንግሥታት ውስጥ የሚሰራ ሌረፍት መጥቶ እዛው ፖሊስ መምሪያ ፊት ለፊት አብረን ቆመን የተመለከትነው ሁኔታ ነበር።
አለመታደል ሆኖ የትኛውም ገዥ ኃይል ሲመጣ ለዚህች ታሪካዊ ክ/ሀገር የሚሾሙ ባለሥልጣናት ቀዳሚ ተግባራቸው ዘረፋ ነው። ክፍሌ ዳዲ ይጠቀሳል።መላኩ ተፈራ የጎንደር ተወላጅ ሆኖ የፈጀው የጎንደርን ወጣት ነው። የዛሬዎቹ የህወሃት ነጭ ለባሾችና እንባ ጠባቂዎችም ይህን ሕዝብ የሚመለከቱት በጠላትነት ፈርጀው ነው። በረከት ስሞኦን ( መበርኻቱ ገበረእግዚአብሔር) ወላጆቹ እነማን እንደሆኑ ቢታወቅም ተወልዶ ያደገው ጎንደር ነው። በረከት ግን «ጎንደሬዎች ወሬ እንጅ ሥራ አያውቁም » ብሎ መተቸቱን ከአንድ ለገዥው ቡድን ቅርብ የሆነ ሰው አጫውቶኛል። አቶ በረከት የትኛውን የሥራ እድል ፈጥሮ ነው ጎንደሬዎች ሥራ እንደማናውቅ የከሰሰን? ሥራ ለመያዝ የድርጅት አባል መሆን መመዘኛ ሆኖ በሚሰራበት እንዴት ብሎ?ለማን ሲባል ምን ለማትረፍ? ሰሞኑን የአማራ ክልል ካድሬዎችን ሰብስቦ ስለ አማራው ሥነ-አእምሮና አመለካከት ገለፃ ያደረገው አለምነው መኮንን የተናገረውን በኢሳት ቀርቦ ተደምጧል። ለማረጋገጥ እንደቻልኩት ሁሉም ሰምቶታል። ይህ አሳዛኝ ፍጡር የሰደበው ራሱን ሲሆን የሚገርመው ደግሞ የዚህ የሚንቀው ሕዝብ ክልል ምክትል ሊቀመንበር ሆኖ ነው። አይ ! ነገን መርሳት ሆዳም! ይሏል ይህ ነው። የታደሰ ካሳ(ታደስ ጥንቅሹ)እና የሕላዊ ዮሴፍ፤ የተፈራ ዋልዋ ኮፒ እነሱ አዘውትረው የሚናገሩት ይህን ነበር። ታደስ አንድ ቀን እኔን ለማናደድ የአማራ ደም ቢመረመር ውጤቱ ትምክህትን እናገኛለን ነበር ያለው። እንግዲህ የአማራው ክልል እንደዚህ በመሰሉ ገፈፎች ነው የሚተዳደረው። በቅርቡ አንድ ከዚህ ጋር የሚያያዝ ሰፋ ያለ ጹሑፍ ለማቅረብ እየሰራሁ ስለሆነ ዛሬ የጎንደሩ ሰላማዊ ሰልፉ እንደ 1969ኙና በአባአምሃ ኢዮሱስ ወቅት የፈሰሰው ደም አይነት አለመፍሰሱ ተመስገን ለማለትና ስለተሰማኝ ሁኔታ ለመግለጽ ነው አመሰግናለሁ።
በቀጣይ እስከምንገናኝ በደህና ያሰንብተን።
የኢትዮጵያ ዳርድንበር ላለማስደፈር አንድ እንሁን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘልዓለም በክብር ትኑር!!
maleda times | February 2, 2014 at 8:57 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-3kb
Comment   See all comments