Sunday, February 23, 2014

ለ አብራሪው ( በ ይግዛው እያሱ)



ቢመረው ቢከፋው ግፍ አላይም ብሎ 
ጨርቄን ማቄን ሳይል ካገር ወጣ ጥሎ።
ለሙያው ሊታመን ምሎ ቢቀጠርም
ስራን በነጻነት ሊያገኘው አልቻለም።
የህዝብ ብሶት መከራ በሱ ተመስሎ
ላይመለስ ሸኘው ድምጽ አሰማ ብሎ።
ይህ የህዝብ ድምጽ ነው የአንድ አገር ዜጋ
በግፍ የሚገረፍ በወያኔ አለንጋ።
22 ዓመት ህዝብ ከህዝብ ከፋፍለው
አንዱን ባንዱ አዝምቶ አንገት የሚያስደፋው
የወያኔን መንግስት የግፍ አገዛዙን
ለዓለም ሊያሳውቅ ነው በመጥላት እራሱን።
በጣም በተሻለ መኖር እየቻለ
ለሆዱ ሳያድር ነጻነቴን ያለ
የቁርጥ ቀን ጀግና እንደ ሀይሌም የለ። (ሀይለመድህን)
የዓለም መንግስታት ይህን ይወቁልን
ለሀይለመድህን አበራ ጥሩ ፍርድ ይስጡልን።
ወያኔ እንደሚለው አሸባሪ አይደለም
ወያኔ እንደሚለው አገሩን አልከዳም
ወያኔን ግን ከድቷል ህዝብን አስቀድሞ
ራሱን ሻማ አርጎ የወገን ድምጽ ሆኖ።
ቢሞትም አይቆጭም ቢያስሩትም ይፈታል
ያጎነበሰን ህዝብ አንገት ቀና አድርጓል።
ለተበደለው ህዝብ ድምጹን አሰምቷል።
ሞት አዲስ አይደለም በኢትዮጵያ ምድር
ሁሉ ሚከፍለው ነው ለወያኔ ግብር።
የሱም ተራ ደርሶ ለእርድ ሳይዘጋጅ
በሰማይ እያለ እግዚአብሔር እረድቶት
እራሱ አመቻችቶ ዘዴ ፈጠረለት
ህዝብን አድን አለው ሂድና ጩህለት።
ቃሉን ተቀብሎ ለራስ ሳያዳላ
ጄኔቭ ገባ ሀይሌ ለመፈለግ መላ።
መላ ባንተ ይገኛል ድካምህ አይቀርም
የዓለም መንግስታት ይህን ዝም አይልም።
በቅርብ ታየዋለህ ካንተ ፍርድ ጀምሮ
የኢትዮጵያ አምላክ አይጥልህም ጥሎ።

maleda times | February 21, 2014 at 8:16 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-3DX

No comments:

Post a Comment