Wednesday, August 12, 2015

የቀድሞው ጠ/ሚ መለሥ ዜናዊ 3ኛ ሙት ዓመት በሰሯቸው ታላቅ ሥራዎች በማስታዎሥ ታሥቦ ዋለ



የቀድሞው ጠ/ሚ መለሰ ዜናዊ 3ኛ ሙት ዓመት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና እራይ አሥፈጻሚው ጠ/ሚ  ሀይለማሪያም  ደሳለኝና ቀዳማዊ እመቤት አዜብ  መሥፍን ጭምር በተገኙበት በሥልጣን ዘመናቸው የሰሯቸውን በርካታ  ሥራውች በውሳት በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል.በርካታ የህዋት(TPLF) ባለሥጣናት ቀዳማዊ አዜብ መሥፍንን  ጨምሮ  የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ እራይ በማሥፈጸም ከሳቸው ጋር ለመቀላቀል ቃል ገቡ
መለስ ዜናዊ ለኢትዮጲያ ምንም አልሰራም የምትሉ ተቃዋሚዎች ሁሉ ሳነብ ካገኘሗቸው የርሱ ትልልቅ ስኬቶች ውስጥ ጥቂቶቹን ላካፍላችሁ!1ኛ...ይች ሀገር ከ80 በላይ ብሄር ቤሄረሰቦች ያሉዋት ሲሆን  አቶ መለስ የመጡበት ትግራይ ግን ወርቅ ዘር ናት ብለው ማመናቸውምና መናገራቸውም
2ኛ...አፄ ሐይለስላሴ በከፍተኛ ዓለም አቀፍ ተጋድሎ ወደ እናት ሀገሩዋ የቀላቀሉዋትን ኤርትራን
ማስገንጠላቸው...
3ኛ.....ከኤርትራ ጋር በተደረገና T ድረስ ምክንያቱ ባልታወቀ ጦርነት 70,000 ወጣቶችን እንዲያልቁ በማድረጋቸው
5ኛ....በዘመናት የታሪክ ሂደት ከስም ያልዘለለ ጥቅም አግኝቶ የማያውቀን የአምሀራን ህዝብ እንደ ጨቁዋኝና ገዥ አድርጎ በማስጠላት በበደኖ በአርባጉጉ በነቀምት በጉራፈርዳ የዘር
ፍጅት እንዲደረግበትና እንዲሰደድ
በማድረጋቸው
6ኛ.... የኦሮሞ ፖለቲከኞችን ኦነግ በሚል ስም በመግደልና እስር ቤቱን በኦሮምኛ ተናጋሪ በመሙላታቸው
7ኛ....የሀገሪቱን የትምህርት ፖሊሲ በሀገሪቱ የዘመናዊ ትምህርት ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የማይረባና ትውልድን ገዳይ የሆነ የትምህርት ፖሊሲ እነዲሆን
በማድረጋቸው
8ኛ....ኢትዮጵያውያንን በታሪካቸው
አይተውት የማያውቁትን ለአረብ አገልጋይ ወይም ገረድ እንዲሆኑ በማድረጋቸው
9ኛ.....የሀገሪቱን የመከላለከያ ሰራዊት በተለይም በከፍተኛ ማዕረግ ቦታዎች ላይ ከአምስተኛ ክፍል ያቁዋረጡ ሰዎችን ጀኔራል በማድረጋቸው
10ኛ....በኦርቶዶክስ ቤተክርቲያን ታሪክ
ሽጉጥ የሚይዙ እንዲሁም ጠባብና ዘረኛ የሆኑ ፓትርያርክ በመሾማቸው
11ኛ.....እስልምናን ለማጥፋት አህባሽ የሚባል አስተምህሮ በማምጣታቸው
12ኛ. ዜጎች በሀገራቸው መሬታቸው
እየተነጠቀ ለባዕድ እንዲሰጥ በማድረግ
የወጣቶች ተስፋ ስደት ብቻ እንዲሆን
ያደረጉ በመሆናቸው
ብቻ የርሳቸው ስኬት እንዲህ በቀላሉ ተዘርዝሮ አያልቅምና በዚህ ዬብቃኝ፡፡
መታሰቢያነቷ ለራሱ 3ኛ ሙት አመት ትሁንልኝማ! ደግሞ ዛሬም ጀግና አይሞትም በሉን!

No comments:

Post a Comment