Friday, February 22, 2013

ግልጽ ደብዳቤ ለአቶ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ለአቶ በረከት ስምኦን አ ዘጋጅ በፍቃዱ ዘ ኃይሉ

Gudu  Kassa
ለተከበሩ አቶ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ የኮሙኒኬሽን እና ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር፣
ለተከበሩ አቶ በረከት ስምኦን፤ በሚኒስትር ማዕረግ፣ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ፣
ከ20 ዓመታት በፊት ፓርቲዎቻችሁ - ሕወሓትም ሆነ ብአዴን - ብዙ የኢትዮጵያ ልጆች ሕይወታቸውን የገበሩለትን ጦርነት ያካሔዱት፥ ኢትዮጵያውያን ‹‹ጀርባቸውን ሳይመለከቱ›› በነጻነት አመለካከታቸውን እና ሐሳባቸውን እንዲያንፀባርቁ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ብዙዎች ደማቸውን ያፈሰሱለት፣ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ የተሰየመለት (አንቀጽ 29) ‹‹የአመለካከት እና ሐሳብን በነጻ የመያዝና የመግለጽ መብት›› ከኢትዮጵያውያን እጅ ቀስ በቀስ አፈትልኮ እየወጣ መሆኑ ቢያሳስበኝ ይህንን ግልጽ ደብዳቤ ለመጻፍ ተገደድኩ፡፡
ደብዳቤዬን መስመር ለማስያዝ እንዲመቸኝ ከኔ የተሻለ የምትረዱትን ነገር በማስታወስ ልጀምር፡፡ ኢትዮጵያ ከ80 ሚሊዮን የሚልቁ ሕዝቦች፣ ከ80 የሚልቁ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች፣ በርካታ ሃይማኖቶች፣ እምነቶች እና ባሕሎች ያሏት አገር ናት፡፡ ሁሉም የየራሱ የሆነ ነገሮችን የሚረዳበት መንገድ ያለው ይህ ብዝኃ-ሕዝብ በፓርላማ ውስጥ ባለ አንድ ፓርቲ ሙሉ ድምፅ እና አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል አማራጭ ሐሳብ ብቻ ሊወከል ፈፅሞ አይችልም፤ ስለዚህ ሕዝቦች ሐሳባቸውን በነጻ የሚገልፁበት ሌሎች አማራጮች ያስፈልጓቸዋል፡፡ እነዚህ አማራጮች ጋዜጣና መጽሔቶችን፣ ሬዲዮና ቴሌቪዥኖችን እንዲሁም አዲሱ ብዙኃን መገናኛ (new media) በመባል የሚታወቀውን በበይነመረብ ላይ ባሉ ድረአምባዎች፣ ጦማሮች እና ማኅበራዊ አውታሮች ላይ ዜጎች የሚያሰፍሯቸውን አስተያየቶች እና ሐሳቦች ያካትታል፡፡
በአሁኑ ወቅት በርካታ በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያወሩ መጽሔቶች እና ጥቂት የማይባሉ የስፖርት ጋዜጦች ለሕዝብ የሚደርሱ ቢሆንም፣ ማዕከላዊ ትኩረታቸውን ፖለቲካ አድርገው የሚጽፉ ሳምንታዊ ጋዜጦች ቁጥር ግን እየተመናመነ መጥቶ ከ10 በታች ሆኗል፤ ከነርሱም ውስጥ ገሚሱ ከተመሰረቱ 5 ዓመት የማይሞላቸው ሲሆን እንደሌሎቹ ከዚህ በፊት በተለያዩ ምክንያቶች ከስመው እንደቀሩት እልፍ ጋዜጦች መጥፋታቸው አይቀርም የሚል ስጋት አለኝ፡፡ ይህ እንግዲህ የፕሬስ ነጻነት በአገራችን ከተጀመረበት ጊዜ አንጻር ሲታይ በየቀኑ ሁለት፣ ሦስት ጋዜጦች ከሚወጡበት እና የተለያዩ ሐሳቦች ከሚንሸራሸሩበት፣ በቀን ምንም ነጻ ጋዜጣ ላይወጣ ወደሚችልበት (ሰኞ እና ኀሙስን መጥቀስ ይቻላል) ጊዜ ዝቅ ብለናል ማለት ነው፡፡
ሁለት የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን አንዱ ትኩረቱን ከማኅበራዊ ጉዳዮች ሳያርቅ፣ ብዙዎች እንደሚሉት ‹‹ከመንግሥት ጋር ሳይጋጭ›› ለመዝለቅ እየሞከረ ሲሆን ሌላኛው ሙሉ ለሙሉ የሚያንፀባርቀው የገዢውን ፓርቲ ሐሳብ እና ርዕዮተ ዓለም ብቻ በመሆኑ አማራጭ ድምፅ ብሎ ለመጥራት ከባድ ነው፡፡ በተጨማሪም፤ አንድም የግል ቴሌቪዥን እስካሁን አልተፈቀደም፡፡
ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 29 (5) ላይ ‹‹በመንግሥት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል፡፡›› ብሎ ቢደነግግም በተግባር የሚታየው እውነታ ግን ተቃራኒው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚያሰራጫቸው አራት ቴሌቪዥኖች፣ የኢትዮጵያ ሬዲዮ እና ኤፍ ኤም 97.1 እንዲሁም የኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ የሚያሳትማቸው ጋዜጦች በሙሉ ለገዢው ፓርቲ የሚወግኑ፣ ተቃራኒ ሐሳብ የሚያመነጩ ወገኖችን የሚያፍኑ እና ፍርደገምድል የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ መሆናቸውን ማንም ከሕዝብ የወጣ መንገደኛ አስቁመው ቢጠይቁት ይመሰክራል፡፡
አዲሱ ብዙኃን መገናኛን በመጠቀም የሚቀርቡ ዜናዎች እና መረጃዎች ቀልጣፋ እና በቀላሉ የመሰራጨት አቅም ያላቸው ቢሆኑም፤ መንግሥት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለዘርፉ ትኩረት ባለመስጠቱ በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚጽፉ፣ ራሳቸውን የድረገጽ ዜና እና መረጃ አገልግሎት ለመስጠት በሕጋዊ መንገድ ያስመዘገቡ ያገር ውስጥ የሚዲያ ተቋማት የሉም፡፡ ይሁን እንጂ በውጭ አገር የሚኖሩ ዜጎቻችን የመሠረቷቸው በርካታ ድረገጾች እና አገር ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንም በትርፍ ሰዓት ሊጽፉባቸው የመሠረቷቸው በርካታ ጦማሮች አሉ፡፡ እነዚህ የሕዝብ አስተያየቶች፣ እና አማራጭ ምክረሐሳቦች የሚንጸባረቁባቸው ጦማሮች እንኳንስ መንግሥትጋ ደርሰው ለስህተቶቹ የእርምት እርምጃ እና ለብሶቶቹም ምላሽ ሊሰ’ጥባቸው ቀርቶ ከጸሐፊው በቀር ኢትዮጵያ ውስጥ ላለ አንድም ዜጋ ሳይደርሱ እንዲቀር ድረገጾቹ ከስር፣ ከስር እየታገዱ ይገኛሉ፡፡
ክቡራን ሚኒስትሮች፣
ኢትዮ-ቴሌኮም ‹‹ኢትዮጵያን ከመጪው ዘመን ጋር የማገናኘት›› ሕልሙን የሚፈፅመው በተቀላጠፈ እና ነጻ የመረጃና ተግባቦት አገልግሎት እንጂ በከፊል በተገደበ ተግባር ሊሆን አይችልም፡፡ የብሮድካስት አገልግሎት የገዢው ፓርቲን አቋም ብቻ ለይቶ እያሰራጨ ሕዝቡን በአንድ አስተሳሰብ ብቻ ለመቅረፅ የሚያደርገው ሙከራ ከስነምግባርም ሆነ ስለወደፊቷ ኢትዮጵያ ከሚያስብ ሕሊና አንጻር ተገቢ አይደለም፡፡
መንግሥት የፕሬስ ነጻነቱን የሚያፍንባቸው በርካታ መንገዶች ናቸው፡፡ በብሮድካስት ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት የሕትመት ፈቃድ ለማውጣት የሚሄዱ የድርጅት ወኪሎች በፖለቲካዊ አመለካከታቸው ምክንያት ይከለከላሉ ወይም ተሰላችተው እንዲቀሩ ተከታታይ እና የተራዘሙ ቀጠሮዎች የሚሰጥበት አስተዳደራዊ በደል ይደርስባቸዋል፤ (የቀድሞው ‹አውራምባ ታይምስ› ጋዜጠኞች ተሰብስበው የመሠረቱት አሳታሚ በዚህ መንገድ አዲስ ጋዜጣ ማሳተም ሳይችል ቀርቷል)፡፡ ማተሚያ ቤቶችም ቢሆኑ ፈቃድ የተሰጣቸውን ጋዜጦች ‹‹በበላይ አካላት ትዕዛዝ›› እንዳይታተሙ ያግዳሉ፤ (የፍትሕ ጋዜጣን እግድ መጥቀስ ይቻላል)፡፡ አዲስታይምስ መጽሔትም በብሮድካስቱ ባለሥልጣን ፈቃዱ እንዳይታደስ ተከልክሏል፡፡ በመንግሥት በጀት የሚተዳደረው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሳንሱር የሚከለክለውን የሕገ-መንግሥት አንቀጽ (29/3/ሀ) የሚጋፋ የሥራ ውል ያስፈርማል፤ ሌላኛው የመንግሥት ይዞታ ቦሌ ማተሚያ ቤትም በተመሳሳይ መንገድ አንድ ማኅበራዊ ጉዳይ ላይ እና ሌሎች የስፖርት ጋዜጦችን ብቻ ይዞ የፖለቲካ ጋዜጦችን ‹‹ሥራ ይበዛብኛል›› በሚል ሰበብ እንዳይታተም ያደርጋል፡፡
ጥቂት የማይባሉ የግል ማተሚያ ቤቶች ያሉ ቢሆንም፣ ሁሉም ሊባል በሚቻል መልኩ አንድን ጋዜጣ ለአንዴ ብቻ ካተሙ በኋላ ደግመው አያስተናግዱም፡፡ ይህም የሚሆነው ‹‹በመንግሥት ወይም ባለሥልጣናት ጫና›› እንደሆነ አሳታሚዎቹ በተደጋጋሚ የገለጹት ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህም በላይ፣ ጋዜጠኞች እየታሰሩ ነው፤ ሌሎችም በመንግሥት አካላት ጫና አገራቸውን እየለቀቁ ለመሰደድ ተገደዋል፡፡  ይሄ ደግሞ በቀሪዎቹ ጋዜጠኞች ላይ ራሳቸውን እና ሐሳባቸውን ሳንሱር እንዲያደርጉ፣ ዜጎች በየተገናኙበት ብሶታቸውን ‹ሌላ ሰው ሰማኝ አልሰማኝ› በሚል ድምፃቸውን ዝቅ አድርገው በሹክሹክታ እንዲያወሩ የሚያደርግ ፍርሐት ውስጥ ከትቷቸዋል፡፡
ብዙ ጋዜጦች በታገዱበት እና ቀሪዎቹም ‹‹መንግሥትን የማያስከፉ›› ይዘቶች ላይ በሚያተኩሩበት በዚህ ጊዜ ዜጎች ብሶታቸውን የሚተነፍሱበት እና መረጃዎችን የሚያገኙባቸውን ሌሎች አማራጮች መፈለጋቸው የማይቀር ነው፡፡ ለዚህም ነው በተለያዩ የድረአምባ ጦማሮች እና የማኅበራዊ አውታሮች ላይ የውይይት መድረኮችን የሚከፍቱት፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ማኅበራዊ አውታሮችም በኢትዮጵያ እንዳይነበቡ እየታገዱ ነው፡፡ ለእገዳው የተለያዩ ኃላፊነቱን ሊወስዱ የሚችሉ ቢሮዎች ቢኖሩም፣ ዋናው ግን የተሌኮም አገልግሎቱን በብቸኝነት የሚመራው ኢትዮ-ቴሌኮም ነው፡፡
የኢትዮ-ቴሌኮም የመረጃ ማጥለል ሥራ፣ በግል ባደረግነው የማጣራት ሙከራ ብቻ ከ200 በላይ ድረአምባዎችን እና ጦማሮችን በኢትዮጵያ እንዳይነበቡ አግዷል፡፡ ይህ እገዳ ሲደረግ ምንም የተሰጠ መግለጫ ባይኖርም መንግሥትን ‹‹የሚያስቀይሙ›› ሥራዎች ላይ መሆኑ በግልጽ ያስታውቃል፡፡ ሌላው ቀርቶ፣ ዓለም አቀፎቹ የሲኤንኤን፣ ቪኦኤ እና አልጄዚራ ድረአምባዎች በተለያዩ ጊዜ ባቀረቡት መረጃ ምክንያት የመዘጋት እና እንደገና የመከፈት ዕጣ ቀምሰዋል፡፡ ይህንን የተመለከተ ዜጋ ምናልባት የሚታገዱት የመረጃ ምንጮች ለሕዝብ ደኅንነት የሚያሰጉ መረጃዎችን የያዙ ይሆናል ብሎ ሊያስብ ይችላል፤ ነገር ግን የሚታገዱትን ገጾች መረጃ ላነበበ እውነታው አያሻማም፤ ገጾቹ የሚያቀርቡት መረጃ እና ዕውቀት ቢሆንም መንግሥት ላይ ያላቸውን ተቃውሞ/ትችት ግን የማይሸሽጉ ናቸው፡፡ ሌላው ቀርቶ በኢትዮጵያ ለማኅበረሰብ ደህንነት የማይበጁ፣ ከሕዝቡ ባሕልና ወግ ጋር የማይሄዱ የሚባሉትን የልቅ ወሲብ ቪዲዮ እና ምስል የሚያቀርቡ ድረገጾች - አንዳቸውም አለመታገዳቸው ሌሎቹ ድረአምባዎች የሚታገዱት ለማኅበረሰቡ ታስቦ እንዳልሆነ መልዕክት ይሰጣል፡፡
ስለዚህ ክቡራን ሚኒስትሮች፣
መንግሥት የዜጎችን ሐሳቦች፣ ጋዜጦች እና ጦማሮች በተደራጀ መልኩ እያሰሰ እና እያነበበ የሕዝቦችን ብሶት እና ችግር ተረድቶ ለመፍትሔው መረባረብ ሲኖርበት፣ ዜጎች መረጃዎቹን እንዳያወጡ እንቅፋት መሆንን ከመረጠ በየት በኩል ኃላፊነት የሚሰማው ማኅበረሰብ መፍጠር ይቻለዋል? መንግሥት በምሳሌነት የማያሳየውን ሥርዓት ከሕዝቡ እንዴት መጠበቅ ይቻለዋል?
እንግዲህ እነዚህን ጥያቄዎቼን በቅን ልቦና ተረድታችሁ ለጥያቄዎቼ ሁሉ መልስ እንደምትሰጡኝ በማመን የሕገ-መንግሥቱን አንቀጽ 29 (2) በመጥቀስ ደብዳቤዬን እቋጫለሁ፡-
‹‹ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳቡን የመግለጽ ነጻነት አለው፡፡ ይህ ነጻነት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ወሰን ሳይደረግበት በቃልም ሆነ በጽሑፍ ወይም በሕትመት፣ በሥነ ጥበብ መልክ ወይም በመረጠው በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ፣ ማንኛውንም ዓይነት መረጃና ሐሳብ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት ነጻነቶችን ያካትታል፡፡››
ሕገ-መንግሥቱ ይከበር፤ የአመለካከትና ሐሳብን በነጻነት የመያዝና የመግለጽ መብት ይከበር!
ሐሳባቸውን የመግለጽ ነጻነታቸውን ከተነፈጉት ዜጎች አንዱ፣
በፍቃዱ ኃይሉ
source zone9ethio
staff reporter | February 21, 2013 at 7:15 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1sL

Comment   See all comments

Saudi religious police arrest Ethiopian workers for practicing Christianity


By

Published February 21, 2013
FoxNews.com
Saudi Arabia’s notorious religious police, known as the mutawa, swooped in on a private gathering of at least 53 Ethiopian Christians this month, shutting down their private prayer, and arresting the peaceful group of foreign workers for merely practicing their faith, FoxNews.com has learned.
The mixed group of men and women was seized in a private residence in the city of Dammam, the capital of the wealthy oil province in Eastern Arabia, and Saudi authorities charged three Christian leaders with seeking to convert Muslims to Christianity. The latest crackdown on Christianity in the ultra-fundamental Islamic country comes on the heels of a brutal 2011/2012 incarceration and torture of 36 Ethiopian Christians, and drew a sharp rebuke from a U.S. lawmaker.
“Nations that wish to be a part of the responsible nations of the world must see the protection of religious freedom and the principles of reason as an essential part of the duty of the state,” Rep. Jeff Fortenberry, R-Neb., who sits on the Caucus on Religious Minorities in the Middle East, told FoxNews.com.

“The U.S. … should demand that any expatriate worker detained and held without charge for private religious activity in the Kingdom should be released immediately.”
- Dwight Bashir, U.S. Commission on International Religious Freedom
During Advent in 2011, Saudi authorities stormed a prayer meeting at the private home of one of the Ethiopian workers in the Red Sea city of Jeddah. The Saudi mutawa imprisoned 29 women and six men for more than seven months in barbaric prison conditions, where the men faced severe beatings and the women were subjected to sexually intrusive torture methods. After Christian organizations and human rights groups, as well as the United States government, complained, the Saudis deported the 35 Christian Ethiopian workers in August 2012.
Last March, Abdulaziz ibn Abdullah Al al-Sheikh, the grand mufti of the Kingdom of Saudi Arabia, declared it is “necessary to destroy all the churches in the Arabian Peninsula.”
Still, Saudi officials claim to tolerate other faiths even as the mutawa, or Commission to Promote Virtue and Prevent Vice, mount their crackdowns, said Dwight Bashir, deputy director for policy at the U.S. Commission on International Religious Freedom.
“During an official USCIRF visit to the Kingdom earlier this month, Saudi officials reiterated the government’s long-standing policy that members of the Commission to Promote Virtue and Prevent Vice, also known as the religious police, should not interfere in private worship,” Bashir said. “However, the past year has seen an uptick of reports that private religious gatherings have been raided resulting in arrests, harassment and deportations of foreign expatriate workers.
“The U.S. government and international community should demand that any expatriate worker detained and held without charge for private religious activity in the Kingdom should be released immediately,” Bashir added.
A spokeswoman for the Saudi Embassy in Washington said she “is not allowed” to give her name and referred a FoxNews.com query to Nail al-Jubeir, a spokesman for the Saudi Embassy in Washington. He did not immediately return FoxNews.com telephone and email requests. Diplomats from Ethiopia’s embassy in Washington told FoxNews.com they are looking into preparing a statement about the arrests.
Nina Shea, the director of the Washington-based Hudson Institute’s Center for Religious Freedom, told FoxNews.com that the arrests in Dammam are “part of Saudi Arabia’s policy to ban non-Muslim houses of worship and actually hunt down Christians in private homes.”
Shea, who was in the Saudi capital Riyadh as part of a U.S delegation two years ago, sharply criticized the Saudis for breaking their 2006 pledge to the U.S. government to not disrupt non-Islamic religious practices. The U.S. Commission on International Religious Freedom termed in its 2012 report Saudi Arabia a “country of particular concern”– along with other authoritarian states such as the Islamic Republic of Iran, North Korea, China and Sudan– for repression of religious freedom.
The Saudi government adheres to a strict form of Sunni Islam called Wahhabism that has animated many followers to engage in terrorism across the globe. The 9/11 terrorists, 19 of whom were Saudis, followed the Wahhabi school of militant Islamic ideology.
Shea said “the U.S. government does not raise its voice in protest” as part of the U.S.-Saudi strategic partnership. She added the failure to push the Saudis to change their intolerant behavior “has taken the backseat to oil and the war on terror. The Saudis are playing a double game — cooperating with the war on terror and working against the war on terror campaign.” A telling example, she stressed, involves the Saudi government sending text books around the world that contain extreme forms of Islam.
Benjamin Weinthal is a journalist who reports on Christians in the Middle East and is a fellow at the Foundation for Defense of Democracies. Follow Benjamin on Twitter: @BenWeinthal.
Read more: http://www.foxnews.com/world/2013/02/21/saudi-religious-police-arrest-ethiopian-workers-for-practicing-christianity/#ixzz2LcSULySV

Wednesday, February 20, 2013

Ethiopian Military-Run Company Seeks More Foreign Partners (1)William Davison

Gudu Kassa
Metals & Engineering Corp., an Ethiopian military-run corporation, said it plans to partner with more foreign companies as it spearheads a government-drive to develop industries in Africa’s second-most populous nation.
METEC, as it’s known, is already working with companies including Alstom SA, Europe’s second-largest power-equipment maker, U.S.-based solar-panel manufacturerSpire Corp. (SPIR) and China Poly Group Corp. on engineering and manufacturing projects. Some of the company’s budding industries, like vehicle-assembly and engineering businesses, may generate more than 20 billion birr ($1.1 billion) of revenue a year, spokesman Michael Desta said in an interview.
“We’re doing this in collaboration” with foreign companies, he said on Feb. 15 in the capital, Addis Ababa. “We want to learn from them.”
Ethiopia is using one of Africa’s largest armies to help develop an economy that grew an average 8.7 over the past five years, according to the International Monetary Fund. The country operates a state-led development model that targets public and private investment in value-adding industries in order to diversify an economy in which agriculture accounts for 46 percent of total output.
The government is in the midst of a five-year plan in which it’s spending 569 billion birr until 2015 on projects including the $5 billion Grand Ethiopian Renaissance Dam, which would be the site of Africa’s biggest hydropower plant.

Military Efficiency

“The military happens to be relatively efficient, disciplined and well-organized to be entrusted with such grand projects,” said Merkeb Negash, a lecturer in political science and international relations at the Department of Governance and Development Studies at Jimma University in Ethiopia.
Ethiopia’s armed forces numbered about 200,000 in November 2011, making it one of the biggest on the continent, according to the website of Global Security, the Washington-based research company. Officers connected with the rebel movement that overthrew the country’s military regime in 1991 dominate senior positions in the government, it said.
Former Prime Minister Meles Zenawi, who ruled Ethiopia for 21 years before he died in August, may have created METEC to give the military a “stake” in the economy, said Merkeb. “Now the military will always defend the system whatsoever,” he said in an e-mailed response to questions on Feb. 6.

Grand Renaissance

The Ethiopian Electric Power Corp. contracted METEC to build the electro-mechanical works for the $5 billion Grand Ethiopian Renaissance Dam on the Blue Nile River in partnership with Alstom. The Paris-based company will provide eight turbines and generators for 250 million euros ($333 million) to METEC and commission the plant.
METEC is also building the 50 billion-birr Coal Phosphate Fertilizer Complex Project in Illubabor Zone of Oromia Region for the Privatization and Public Enterprises Supervising Agency, and is the main contractor for the Sugar Corp., a government enterprise that’s building 10 cane plantations and processors nationwide at a cost of about $5 billion, Michael said. The fertilizer project will be transferred to the newly formed Chemical Industry Corp. when it’s finished, he said.
The organization is involved in “priority areas and import-substitution,” Deputy Prime Minister Debretsion Gebremichael, who is responsible for economic coordination, said in a Jan. 23 interview. “They cannot do it by their own so they look for partners, international as well as local. They’re bringing many actors to the picture but at the heart of everything it’s METEC.”

Vehicle Manufacturing

METEC was established in June 2010 with 10 billion birr of capital by grouping nine businesses previously owned by the Defense Ministry, including Dejen Aviation Industry and Gafat Armament Industry, Michael said. Six other industries, including plastic, tractor and vehicle spare-parts manufacturers, were transferred to METEC from the privatization agency and it now operates as many as 75 factories nationwide, Michael said.
METEC is overseen by a board headed by Defense Minister Siraj Fergessa, Michael said. It employs about 13,000 people, including more than 1,000 engineers, he said.
Siraj in September opened a 200 million-birr factory in Modjo, 70 kilometers (44 miles) southeast of Addis Ababa that will make turbines, generators and high-voltage electricity- transmission cables, according to state-owned Ethiopian Radio and Television Agency. A METEC arms factory was opened the same day, it said on its website.
Poly Technologies Plc, part of the Beijing-based China Poly Group, is building truck-assembly plants in Modjo and Bishoftu for METEC, Xinhua reported on Sept. 27.
“In the future we will avoid importing everything but the engine,” Michael said. “Maybe in the future the engine will be produced here.”
To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa at wdavison3@bloomberg.net
To contact the editor responsible for this story: Antony Sguazzin at asguazzin@bloomberg.net

Tuesday, February 19, 2013

የሠራዊቱ ቀንና የሠራዊቱ ክብር

 

                      

ሰሞኑን የመከላከያ ሰራዊት ቀን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው፡፡ “የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን” ተብሎ በመንግስት ዕውቂያ መጀመሩም መልካም ጀምር ነው፡፡ ነገር ግን፣ ከ1983 ዓ.ም በፊት ኢትዮጵያ ምንም የመከላከያ ሠራዊት እንዳልነበራት አድርጎ የማቅረብ ችግሮች በመገናኛ ብዙኃኑም ሆነ በመከላከያ ሠራዊቱ ቃል-አቀባዮች ዘንድ ይንጸባረቃል፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ እንዲያማ ከሆነ፣ የአህመድ ግራኝን ወረራ ማን መከተው? ከደቡብ ተነስቶ ወደመሃል አገርና ወደሰሜን ይገሰግስ የነበረውን የሉባዎቸ ጦር ማን ተዋካው? የኦቶማን ቱርክን፣ የግብጹን ፓሻህ እና የመሃዲስቶቹን ጦር ማነው መክቶ የመለሰው? ኧረ ማንን ሊዋጋ ነው ጄኔራል ናፒዬር ከህንድ ድረስ የመጣው? ማነው የመተማውን ውጊያ የተፋለመው? መነውስ በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ ወድ የሌለውንፀ ድል አድዋ ላይ የተቀዳጀው? ለመሆኑ ማነው የፋሺስቶችን ግፍና መርዝ ጋዝ ተቋቁሞ ሀገሩን ነፃ ያወጣው? ኢትዮጵያ ከ1983 ዓ.ም በፊት የመከላከያ ሠራዊት ካልነበራት ወያኔና ሻዕቢያ አዲስ አበባንና አስመራን ለመያዝ ለምን አስራ ሰባት ዓመታት ፈጀባቸው? መልሡ ቀላል ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ስለነበራት ነው፡፡
ኢትዮጵያ እንኳን በ20ኛው ክፍለ ዘመንና ጥንትም ሠራዊት ነበራት፡፡ በ1983 ዓ.ም ወያኔ/ኢሕአዲግ አዲስ አበባን ከመቆጣጠሩ አራት መቶ ዓመት በፊት የነበረውን የኢትዮጵያ ሠራዊት አውድ፣ አባ ባሕርይ እንዲህ ሲሉ ዘግበውታል፡፡ በ1583 ዓ.ም ሙልአታ የተባለው የቢፎሌ ልጅ፤ ዘጠነኛው ሉባ ሆኖ ተሾመ፡፡ የዚያን ጊዜ፣ ጦርነቱ የመሬት ወረራ፣ የሰው ምርኮና የወደደውን ደግሞ በጉዲፈቻና በሞጋሳ መቀበል ብቻ አልነበረም፡፡ “የቁንዳላ ጦርነትም” ተካሄደ፡፡ ይህም የቁንዳላ ጦርነት ጎጃምን፣ ሸዋንና ዳሞትን በእጅጉ ጎዳቸው፡፡ ወደምዕራብ አቅጣጫም ተስፋፍቶ ከፍተኛ ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አስከተለ፡፡ ከአርባ አምስት ዓመታት በፊት ከተደረገው አህመድ ግራኝ ካስከተለው ቀውስ የማይተናነስ ቀውስ ተከተለ፡፡ በዚህ ወቅት ንጉሡ ሠርፀ ድንግል ሠራዊቱን ይዞ አንዴ ደቡብ አንዴ ሠሜን ሲራወጥ ነበር፡፡ ሉባ ሙልአታ የተመከተው በራስ ወልደ ክርስቶስ በቤጌምድር ላይ ነበር፡፡ በተረፈ ግን ደል ወደ ሉባ ሙልአታና ወደርሱ ጦር ያጋደለ ነበር፡፡
የዚህ ጊዜ ታዲያ በዘመኑ የነበረውና የነሉባ ሙልአታን ወረራና የንጉሥ ሠርፀ ድንግልን በአራቱም አቅጣጫ የሚራወጥበትን ችግር ምክንያት ለመረዳት የፈለገው አባ ባሕርይ ሊጽፍ ሲነሳ እንዲህ ብሎ ጠየቀ፡፡ “በአፎ ይመውአነ ሙልአታ እንዘ ብዙኃን ወብዙኅ ንዋየ ጸብዕነግ (ማለትም፣ እንዴት ነው የሙልአታ ጦር እኛ (የክርስቲያኖቹ ጦር አባላት) ብዙ ሆነን ሳለ፣ የጦር መሣሪያችንም ብዙ ሆኖ ሳለ የተሸነፍነው?)” ሲል አደገኛውን ጥያቄ ከ400 ዓመታት በፊት ይጠይቃል፡፡ መልሱንም ለመስጠት አይዘገይም፤ ለዚህ ዋናው ምክንያት “የክርስቲያኖቹ ደንብ” እና የሕብረተሰቡን አደረጃጀት አብራርቶ ይገልጥልናል፡፡ “ከአሥሩ ደንብ ውስጥ አንዱ ብቻ ነው ተዋጊ ሆኖ የሚወጣው፡፡ ዘጠኙ ደንብ በቀጥታ ከጋሻ ጃግሬነትና ከውትድርና ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፤” ሲል ያትታል፡፡ አንፃሩ ግን፣ “በሙልአታ የሚመራው ወራሪ ኃይል ከሕዝቡ አብላጫው (ከግማሽ በላይ) የሚሆነው ተዋጊ ስለሆነ ነው፤” ሲል ያጠቃልላል፡፡
አባ ባሕርይ እንዳተተው የክርስቲያኑ ጦር የተደራጀባቸው ዐስሩ ደንቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡ አንደኛ፤ መነኮሳት ናቸው፡፡ እነዚህም ቁጥራቸው ብዙ ነበር፡፡ ዋና ተግባራቸውም ጸሎት ማድረግ ስለሆነ ዘመቻ አይወጡም፡፡ ሁለተኛ፤ ደባትር ናቸው፡፡ እነዚህም ሥራቸው በማኅሌትና በዝማሬ እግዚአብሔርን ማመስገን ስለሆነ ዘመቻ አይወጡም፡፡ ሦስተኛ፤ ዣን ሐፀናና ዣን ማሰሬዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ ዋና ሥራቸው ወንበርተኞች/የወረዳ ወይም የቀበሌ ካድሬዎችና የቀላድ ጣዮች ስለሆኑ ዘመቻ አይወጡም፡፡ አራተኛ፤ የሴት ወይዛዝርት ደጋፊዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ ወይዘሮዎችን ማጀብ ስለሆነ ሥራቸው ለዘመቻ አይወጡም ነበር፡፡ አምስተኛዎቹ ደንበኞችም፤ ሽማግሎች ናቸው፡፡ እነዚህም “ወባዜ” ይባሉ ነበር፡፡ ዋና ሥራቸው ርስት ማካፈል ብቻ ስለነበረ፤ ወደዘመቻ አይወጡም ነበር፡፡ ስድስተኛ፣ አራሾች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ ከእርሻ በስተቀር ሌላ ሥራ አያውቁም ነበር፡፡ ሰባተኛ፤ ነጋዴዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ መሸጥና መለወጥ እንጂ ውጊያን ስለማያውቁ ዘመቻ አይወጡም ነበር፡፡ ስምንተኛ፤ የእጅ ባለሙያዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ በሽመና፣ በቀጥቃጭነትና በአንጥረኝነት እንዲሁም በልዩ ልዩ ሥራዎች ይሰማራሉ እንጂ ወደዘመቻ አይሄዱም ነበር፡፡ ዘጠነኛው ረድፍ ላይ ያሉት ደንበኞች ደግሞ፤ የኪነት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ በአዝማሪነትና በአመሸታ ቤት ይሆናሉ እንጂ ወደዘመቻ ለውጊያ አይሄዱም ነበር፡፡ዐሥረኞቹና የመጨረሻዎቹ፣ ጋሻ ጃግሬ የሚባሉት ናቸው፡፡ እነዚህ ወታደሮች ናቸው፡፡ ዋና ሥራቸውም ውጊያ ነበር፡፡ ይህም የመጨረሻው ደንብ ቁጥሩ አነስተኛ ስለነበረ፤ “ጠፍአት ሀገርነ (አገራችን ጠፋች)” በማለት አባ ባሕርይ ይደመድማል፡፡
ከ1583 እስከ 2005ዓ.ም ድረስ ቢያንስ አራት መቶ ሃያ ሁለት (422) ዓመታት ያህል ተቆጥረዋል፡፡ ያም ሆኖ፣ ኢትዮጵያ ካሳለፈችውና ካደረገቻቸው መራራ የነፃነትና የሉዓላዊነት ትግሎች አንጻር ገና “ብቁና ንቁ የመከላከያ ሠራዊት” አላደራጀችም፡፡ ቀድሞም ሆነ አሁን የመከላከያ ሠራዊቱ በግለሰቦች ጥላ ሥር ነው ያለው፡፡ ያኔም “የራሶችና የደጃዝማቾች ጦር” ነበር፤ አሁንም በዚያው መንገድ ላይ እየተጓዘ ነው፡፡ ያኔም ሆነ አሁን፣ ራስ አመልማሎች፣ ራስ ወልደ ክርስቶሶች፣ ራስ አሊዎች፣ ደጃች ውቤዎች፣ ደጃች ካሳዎች፣ ፊታውራሪ መሸሻዎችና ፊታውሪ አሰጌዎች አሉ፡፡ ጦሩ/ሠራዊቱ ገና የኢትዮጵያ ጦር ሆኖ አልቆመም፡፡ አሁን የምናየው፣ የሕወሃት/ወያኔ ጦር፤ የብአዴን/ኢሕአዲግ ጦር፤ የአሕዲድ/ኢሕአዲግ ጦር የሚባለውን ከራሶችና ከደጃዝማቾች ወደ ፓርቲ-ራስነትና ደጃዝማችነት የተለወጠውን ነው፡፡ ማለባበስ አንፈልግም፡፡ ሀቁን አውቀን ወደፊት ልንራመድ ይገባናል፡፡
ይሄው ጦር በሰሜን፣ በምስራቅና በምዕራብ በኩል ደሙን እያፈሰሰ ሳለ፤ ለምን በግለሰብ “ራዕይ” ላይ ተንጠልጠል እንደተባለም አልታየንም፡፡ ጦሩ፣ አሁንም ቢሆን ቅድመ 1983 ዓ.ም በነበረው ቅርጹና መልኩ እንዲደራጅና እንዲሄድ የመፈለግ ዝንባሌ አለ፡፡ ይህም ዝንባሌ በሠራዊቱ አባላትና መኮንኖች የተመከረበት ሳይሆን በፖለቲከኞቹ የተጫነበት ነው፡፡ በጥቂት የፓርቲን ጥቅምና የሀገርን ጥቅም በሚያቀላቅሉ ወገኖች የተደረገ ረብ-የለሽ ተግባር ነው፡፡ ይሄውም ተግባር የሚገለጥባቸው ወሳኝ ነጥቦች አሉ፡፡ በዋናነት ሥስት ናቸው፡፡ አንደኛ፤ ከፍተኛውን የወታደራዊ ሥልጣን የመቆጣጠር አባዜ ነው፡፡ ይህም ቢሆን ከሙሉ ኮሎኔል በላይ ባለው የወታደራዊ ማዕረግ አሰጣጥ ላይ ጎልቶ ይታያል፡፡ ከብርጋዴር ጄነራል ማዕረግ ጀምሮ የሚፈቀደው ለሥርዓቱ ታማኝ መሆናቸው ለተረጋገጠላቸው ሰዎች እንጂ (በአገልግሎት ወይም በጀብዱ አፈጻጸም) የሚሰጥ አይደለም፡፡ በዚህም መስፈርት መሠረት ካየነው አብዛኛውን ቦታ የተቆጣጠሩት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ከአንድ ፓርቲ የመጡና የሥርዓቱ ታማኞች ሆነው እናገኛቿቸዋለን፡፡ ከላይ እንደጠቀስነው፣ በፓርቲ ስም የተደራጁ ራሶች፣ ደጃዝማቾችና ፊትአውራሪዎች የማዘጋጀት አዝማሚያ ነው፡፡
በሁለተኛ ደረጃም የሚነሳው ነጥብ፣ ስለሠራዊቱ “ሁሉንም ልቆጣጠር፣ ሁሉንም ልሽጥ-ልሸቅጥ” የሚለው አባዜ ነው፡፡ ይህም ከላይ ከጠቀስነው ከፍተኛውን ወታደራዊ ሥልጣን ከያዙት የአንድ ፓርቲ/ራስና ደጃዝማቾች የግል ጥቅምና ፍላጎት ጋር የተሣሰረ አደጋ ነው፡፡ በቀጥታ ከገንዘብና ከጥቅም ጋር የተቆራኘ ነው፡፡ ብዙዎቹ ግዙፍ የመዋለ-ንዋይና የቴክኖሎጂ አቅምን ይዘው የተደራጁ ናቸው፡፡ ለምሳሌ የመከላከያ ብረታ-ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን፣ የላሊበላ ኮንስትራክሽንን መውሰድ እንችላለን፡፡ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የምዕዋለ-ንዋይ አላቸው፡፡ ሆኖም ግን ከፍተኛ አመራራቸው ከቅድመ 1983 ዓ.ም በፊት ከነበረው መንፈስ ብዙም የራቀ አይደለም፡፡ የአንድ ቡድን የበላይነት ጎልቶ ይታይበታል፡፡ ከጥበቃ እስከ ባለሙያና የመምሪያ ኃላፊዎች ድረስ የአንድ ቡድን/ፓርቲ የጎላ ቁጥጥርና ርብርብ ይንፀባረቅበታል፡፡ ለምን ኢትዮጵያዊ እንዲሆን አይደረግም? ለምንስ የአንድ ቡድን/ፓርቲ ቀልብና መንፈሥ ብቻ እንዲንጸባረቅበት ተፈለገ? ለመሆኑ የእስራኤልን ወይም የግብጽን መከላከያ ሞዴል አድርጎ መነሳቱ ባልከፋ፡፡ ነገር ግን፣ ለምን እንደስራኤልና እንደግብጽ ሀገራዊ ቅርጽና መልክ እንዲኖረውስ አልተደረገም? መልሱ ቀላል ነው፡፡ የራሶችና የደጃዝማቾች መንፈስ ዛሬም ስላለ ነው፡፡ ሁሉም በየፊናው “ዘመናዊ ፊታውራሪ” ለመሆን ቋምጧል፡፡
ወደሦስተኛው ችግር እንለፍ፤ ይሄውም ከጦሩ/ከሠራዊቱ አባላት ክብር፣ መብትና ጥቅም ጋር የሚነሳ ነው፡፡ መከላከያው ከፍተኛ የሆነ የጥቅምና የመብት አለመከበር ችግሮች አሉበት፡፡ ብዙኃኑ የመከላከያው ሠራዊት ወታደራዊ አባላት ክፍያ የሚያተጋ አይደለም፡፡ ሌላውን ትተነው እንኳን የመሥመራዊ መኮንኖች (ከም/መ/አለቃ እስከ ሻምበል ያሉት) ደሞዝ ከ2300.00 ብር ያነሰ ነው፡፡ የአንድ ኮሎኔልም ደሞዝ ቢሆን እምብዛም ነው፡፡ ኧረ! ከእጅ-ወዳፍ ነው ቢባልም ማጋነን አይሆንም፡፡ ስለሆነም፣ የሠራዊቱ አባላት ከፍተኛ የሆነ የጥቅም አለመከበር ችግር አለባቸው፡፡ ጥቅማቸው ባለመከበሩም፣ ከፍተኛ የሆነ የመብትና የክብር ጥያቄዎችን በየስብሰባዎቹ ላይ እንደሚያነሡም ይታወቃል፤ ከፍተኛ አመራሮች የሚሠጡት መልስ ግን አጭር ነው፡፡ “መንግሥት በጀት የለውም!” የሚል ነው፡፡ ይህ በርግጥ አሳማኝ አይደለም፡፡ ምክንያቱም፣ ሠራዊቱ ካለበት ኃላፊነትና ካለበት የሀገርን ሉዓላዊነት የማስከበር አደራ አንጻር ዝቅተኛ ነው፡፡ በተለይም፣ ለነፍሱ ሳይቀር ሳይሳሳ ለሚያደርገው ተጋድሎው የሕይወትም ሆነ የአካል መጥፋትና መጉደል ዋስትናና መድን (Inesurance) የሌለው ምስኪን መሆኑን ለሚያውቅ ሰው ምን ያህል የሠራዊቱ-ክብር፣ መብትና ጥቅም እንዳልተከበረ ይረዳል፡፡
ሌላም ተያያዥ ችግር አለ፡፡ ይኼውም በሠራዊቱ ውስጥ ካሉት የተማሩ ሙያተኞች ጥቅምና መብት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ይህንን ሃሳብ በምሳሌ ማስረዳቱ ያዋጣል፡፡ አንድ የማስተርስ ዲግሪ ያለው የትኛውም የመከላከያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለ ባለሙያ የሚከፈለው ደሞዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የደሞዝ ስኬል መሠረት ነው፡፡ የቤት አበልም አለው፡፡ በአጠቃላይ አንድ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ያለ የሲቪል ባለሙያ የሚከፈለው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ያለ ማንኛውም የማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ የሚከፈለውን ደሞዝ ነው፡፡ ነገር ግን፣ አንድ የመከላከያ የኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሠራ መሳሳይ የት/ት ደረጃ ያለው ባለሙያ ከዚህ በጣም ያነሰ ክፍያ ነው ያለው፡፡ ለምን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዋጅ በወሰነው መሠረት እንደማይከፈላቸው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ዋናው ምክንያት ግን፣ “የከፍተኛ መኮንኖች ደሞዝ ስንት ነው?” የሚለው ነው፡፡ እጅግ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ በተለይም በፋይናንሻል ተቋማት (በባንኮች፣ በኢንሹራንስ ተቋማት)፣ በግንባታ ድርጅቶችና በመንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ያሉ ኃላፊዎች ከሚከፈላቸው ጋር ካነጻጸርነው እጅግ አናሳ ነው፡፡
ይህንንም ጉዳይ በምሳሌ ብናወሳው ሳይሻል አይርም፡፡ አንድ የግል ባንክ ውስጥ የሚሠራና በሥሩ አራት መቶ ሃምሳ የማይሆኑ ሰራተኞችን የሚመራ የባንክ ሥራ-አስፈጻሚ ከሠላሳ ሺህ ብር በላይ ይከፈለዋል፡፡ በዚያ ላይ ቢያንስ ሁለት መኪናዎችና የቤት አበል፣ እንዲሁም የተለያዩ ጥቅማ-ጥቅሞች አሉት፡፡ ይህ ሰው ልጆቹን የተሻለ ትምህርት ቤት ልኮ ያስተምራል፡፡ ዘመዶቹ ሲመጡ የቻለውን ያህል የሚረዳበት ገንዘብም አለው፡፡ መስረቅም ሆነ ሙስና ውስጥ መግባቱ (ዓመል ካልሆነበት በስተቀር) እምብዛም አያስፈልገውም፡፡ አንድ የዓለም አቀፍ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ የሚሠራም የብሔራዊ ድርጅት ሥራ-አስኪያጅ ከሠላሳ ሺህ ብር በላይ የከፈለዋል፡፡ እንደባንኩ ሥራ-አስፈጻሚ ሁሉ፣ የመኪና፣ የቤትና የተለያዩ ጥቅማ-ጥቅሞች አሉት፡፡ ልጆቹን የተሻለ ትምህርት ቤት ማስተማርም ሆነ ለወደፊቱ መጦሪያውን ማስቀመጥ/መቆጠብ ይችላል፡፡ ነገር ግን፣ የአንድ የዕዝ ኃላፊ የሆነ ጄኔራል ክፍያ በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ እርግጥ ነው የቤት፣ የመኪናና የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች ቢኖሩትም ቅሉ፤ ደሞዙ የባንኩን ወይም የመንግሥታዊ የልሆነ ድርጅት ውስጥ የሚሠራውን ሰው ደሞዝ አንድ ስድስተኛ (1/6) ገደማ ቢሆን ነው፡፡
ይህ ደሞዝና የገቢ ምንጭ አንድን የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የሚያተጋው አይደለም፡፡ ምናልባትም ለመርኅ መከበርም በጽናት እንዲቆም ላያደርገው ይችል ይሆናል፡፡ ስለሆነም፣ ስልጣኑም ሆነ ከስልጣኑ የሚገኘው ጥቅም “የዛፍ ላይ ዕንቅልፍ” ከመተኛት ብዙም የተለየ አይሆንም፡፡ ደንበኛ እንቅልፍ ለመተኛት ደግሞ የአንዱ ቡድን/ፓርቲ አባል መሆን የግድ ይላል፡፡ አለበለዚያ፣ በፖለቲካ ታማኝነት የሚሰጠው ከብ/ጄነራል በላይ ያሉትን ማዕረጎች ማሰብ ቀርቶ ማለምም አይቻልም፡፡ በዚህ መስመርና በዚህ ታማኝነት የሚመጡ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ደግሞ እንደምን አድርገው የመከላከያው ውስጥ ያሉትን የሠራዊቱ አባላትና ሙያተኞች መብትና ጥቅም ሊያስከብሩ እንደሚችሉ መሰቡ ራሱ ከባድ ችግር አለው፡፡ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖቹ ተጠሪነታቸው ለሾማቸው አካል እንጂ ለሚመሩት ሠራዊትና ሙያተኞች አለመሆኑ ስለሚያመዝን ነው፡፡ ስለሆነም፣ አንድ የማስተርስ ዲግሪ ያለው መቶ አለቃ የሚከፈለው ክፍያ፤ ከሲቪሉ ጋር ተመሳሳይ ሥራ እያከናወነ ከሙያውና ከትምህርቱ ጋር የማይመጣጠን ነው፡፡ “ለምን ሆነ?” የሚል ካለ መልሱ ቀላል ነው፡፡ የመከላከያ የደሞዝ እርክን ማሻሻያ የሚያስፈልገው ስለሆነ ነው፡፡ (መዘንጋት አልነበረበትም፤ ግን ተዘንግቷል፡፡)
ይህንን ሁሉ ያተትነው የመከላከያ ሠራዊቱ ከተከናነበው የቡድናዊነት ስሜት ወጥቶ እንደምን የሀገራዊ/ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት መሆን ይችላል የሚለው ጉዳይ ስሊያሳስበን ነው፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም ከአራት መቶ ሃያ ዓመታት በኃላ የወራሪዎች ችግር ከውስጥም ከውጭም ተጋርጦባታል፡፡ ያለምንም ጥርጥር ችግሩ የፖለቲካና የሥልጣን ችግር እንደሆነም እናውቃለን፡፡ በኦጋዴንም ሆነ በጋምቤላና በባሌ እንዲሁም በትግራይና በጎንደር አካባቢ ያሉት ቡድኖች የሥልጣን ትግል አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን መካድ አያሻም፡፡ በተለይም፤ ከኤርትራና ከሶማሊያ በኩል ያለውን ችግር በቁርጠኝነት የሚመክት ደንበኛ መከላከያ ሠራዊት እንዲኖረን እንፈልጋለን፡፡ ስለሆነም፣ እንደግብጽ ጦር የተሽከርካሪዎች መለዋወጫና አንዲት ካይሮ አጠገብ ያለች የ25 ሰዎች መኖሪያ የምትሆን ደሴት ልቆጣጠር የሚል ቀቢጸ-ተስፋውን ትቶ ሀገራዊ ኃላፊነቱንና ሉዓላዊነትን የሚያስቀድም የመከላከያ ሠራዊት እንዲኖረን እንፈልጋለን፡፡ መከላከያ ሠራዊቱ አይዘመን፣ ወይም ደግሞ ራሱን አይቻል አላልንም፤ አንልምም፡፡ ኢትዮጵያንም ከግብርና-መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ-መር ኢኮኖሚ አሻሸጋግራት አላልንም፤ አንልምም፡፡ ነገር ግን፣ ቅድሚያ ሰጥቶ ሠራዊቱን ኢትዮጵያዊ መልክና ቁመና ይስጠው፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርና የሕዝብ አለኝታ እንጂ፣ የአንድ ወይም የጥቂቶች ፖለቲካዊ አጀንዳና ድርጅት ደጋፊ መልክ እንዲኖረው ማድረግ አይገባም፡፡
የመከላከያ ሠራዊቱ ከክልላዊነት ስሜቱ ወጥቶ የብሔራዊነት ስሜትንም እንዲላበስ ሊከበሩለት የሚገቡ የክብር፣ የመብትና የጥቅም ጉዳዮች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው መከናወን አለባቸው፡፡ አሁኑኑ፣ በአፋጣኝ የመከላከያ ሠራዊቱን ከፍተኛ አመራር በኢትዮጵያዊነት መርኆና የብሔራዊ ስሜት አብነትን ባረጋገጡ ኃላፊዎች መተካት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡ የጋራ ቤታችንን ኢትዮጵያን የሚጠብቀውና ለነፃነቷ የሚጋደለው ከተለያዩ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሆኖ ሳለ፣ እነዚህን ሙሉ-ለሙሉ የማይወክል አመራር ቆም ብሎ ማሰብ ይጠበቅበታል፡፡ ሰባ በመቶ (70%) የሚሆነው የመላከያ ሠራዊት እስከ አፍንጫው ታጥቆ፣ አንድ ክልል ላይ ብቻ ለምን እንደተከማቸም ሊመረመር ይገባዋል፡፡ መከላከያው ራሱን እንዲመረምር ጊዜውም ዕድሉም አለውና ፋታ ወስዶ ይመርምር፡፡
ከዚህ በተረፈ፣ እንኳንም የመከላከያ ሠራዊቱን ቀን ለማክበር ጅማሮው መታየቱ መልካም ነው፡፡ ሆኖም፣ በአምስቱም ዕዞችና በየክፍለ ጦሮቹ ብቻ በሚደረግ የወታደራዊ ትርኢትና ኤግዚቢሽን ብቻ ከሚወሰን በተለያዩ ክፍለ ጦሮችና ዕዞች አማካይነት በሚደረጉ ስፖርታዊ ውድድሮችም ታጅቦ ቢቀርብ መልካም ነው እንላለን፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸውን የመከላከያ ሠራዊቱ አባላትንም ሆነ የሕዝቡን ተሳትፎ ለማግኘት ያስችላል፡፡ በ1950 ዓ.ም ጀምሮ ይደረግ የነበረውና ቀዳሚው “የመከላከያ ሰራዊት ቀን” እንዴት ይደረግ እንደነበርም ታሪክን መርምሮ መነሳቱ ያዋጣል፡፡ እነዚህን “የመከላከያ ሠራዊት ቀን” አከባበሮች በተመለከተ የምድር ጦር፣ የአየር ኃይልም ሆነ የክብር ዘበኛ ተቋማት እያንዳንዳቸው ከዐሥር በላይ የክብረ በዓሉን አስመልከቶ ዘጋቢ መጽሔቶችን አሳትመው ነበር፡፡ ስለሆነም፣ ታሪክን አጥንቶና መርምሮ ከታሪክ መማርና የተሻለ ለመሥራት መሞከርም ይገባል፡፡ (በቸር ያቆየን!)
maleda times | February 17, 2013 at 9:45 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/s2gxmh-5563
Unsubscribe or change your email settings at Manage Subscriptions.
Trouble clicking? Copy and paste this URL into your browser:
http://www.maledatimes.com/2013/02/17/5563/

“የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ



ስለ መሬት ነጠቃው ኢህአዴግ “እንወያይ” አለ
mittal metho
“መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር።
“ትግል አርቆ ማሰብ ይጠይቃል፤ እቅድ ይፈልጋል። ትግል ህዝብን ማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልምና ራዕይ ሊኖረው ያስፈልጋል። ስለዚህ ምን እናድርግ? ከየት እንጀምር?” የሚል ጥያቄ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች አነሱ። አቶ ኦባንግም የሚመሩት ድርጅት ዕቅዱና ራዕዩ በሂደት እዚህ እንዳደረሰው አስረዱ። በቀጣይም ከህንድ ዜጎች ስለሚጠበቀው ዋንኛ ትግል አወሱ። ካሩቱሪ የሚባለው ኩባንያ በኢንቨስትመንት ስም እያከናወነ ያለውን ተግባር ህንዶች ካሳለፉት የቀደመው ችግራቸው ጋር በማያያዝ ተናገሩ። መሃትማ ጋንዲ ገድል ፈጽመው ያለፉበትን ትግል በማድመቅ ይህ ትውልድ የጋንዲን ዓላማ በማንሳት ለወገኖቹ ስቃይ የመድረስ ግዴታና የታሪክ ውርስ እንዳለበት አሳሰቡ። በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ በመረጃ ተንትነው አብራሩ።
ኦባንግ “ጥቁሩ ሰው” ወደ ህንድ ያመሩት ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር ለመነጋገር አልነበረም። በመጀመሪያ የተገኙት የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል “Understanding Land Investment in East Africa” በሚል ስያሜ ባዘጋጀው ምክከርና የትግል ልምድ መለዋወጫ መድረክ ላይ ንግግር እንዲያቀርቡ ተጋብዘው ነው። አስቀድሞ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲሳተፉ በጋራ ንቅናቄው የተመረጡ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ግለሰቦች የነበሩ ቢሆንም ከወጪ እና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶቹ ካጋጠማቸው ሌሎች ተዛማች ችግሮች ምክንያት ሳይሳካ እንደቀረ ተጠቅሷል፡፡
የኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር አኑራድሃ ሚታል
በዚሁ ታላቅ መድረክ ላይ ኦባንግ “ነጻ ስለመሆን የማንንም ፈቃድ አንጠይቅም። ሰው በሰውነቱ የሚከበርበት አገር እስከምንመሰርት ድረስ እንታገላለን። የብሶታችንና የትግላችን መነሻ ለናንተ አዲስ ትግል አይደለም” በማለት የስብሰባውን ቀልብ አነሱት። በህንድ የነጻነት ትግል ውስጥ አብሪ ኮከብ ሆነው የሚኖሩትን መሃትማ ጋንዲን በማስታወስ አገራቸውን ተቀራምተው የነበሩትን የእንግሊዝ የመሬት ቀማኞች እንዴት ድል እንደመቱ አሞካሽተው አቀረቡ። ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጥያቄ መልስ የሰጡት አቶ ኦባንግ በዩኒቨርስቲው ንግግራቸው ጋንዲን ማጉላታቸው ብቻ ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ውስጥ ሌሎች ጋንዲዎች ስለመኖራቸው መናገራቸው ታላቅ ትርጉም የሰጠ እንደነበር ገልጸዋል።
በምክክሩ ላይ የክብር ተናጋሪ የነበሩት የኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር አኑራድሃ ሚታል “በኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ሁሉ በፍጹም ተቀባይነት የለውም” በማለት ምክንያታቸውን አስረዱ። በኢትዮጵያ በወልቃይት ጠገዴ፣ በዋልድባ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ ስለተካሄደው መሬት ንጥቂያና ግፍ የተሞላበት ተግባር በዝርዝር አቀረቡ። የአኑራድሃ ንግግር ህንዶቹን አስደነገጠ።
የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል ባዘጋጀው በዚህ የምክክርና የትግል ስልት የልውውጥ መድረክ የህንድ ፖለቲከኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋንዲያዊ የትግል መስመር አጥብቀው የሚከተሉ የተለያዩ ፖለቲከኞች፣ የህንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ የገዢው ፓርቲ ተወካዮች፣ የቀድሞ ፖለቲከኞች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ተሟጋቾች፣ ተለያዩ ማህበራት ተወካዮችና የተለያዩ አካላት የተገኙ ሲሆን ታላላቅ የመገናኛ አውታሮችም ተገኝተዋል።
ዶላር ከዜጎቹ የበለጠበት ኢህአዴግ
“ህወሃት/ኢህአዴግ ዶላር ካገኘ ለሚገባበት ገደል የሚቀርበውን አፋፍ አይመርጥም” በማለት የሚተችበትን ነጥብ ማስታወስ አግባብ ይሆናል። ኢህአዴግ ከስልጣኔ፣ ከወገኖቻቸውና ከዓለም መገናኛ ጀርባ ያሉ፣ በመረጃ ጨለማ ውስጥ የሚኖሩ ምስኪን ዜጎችን በሚዘገንን የንዋይ ፍቅር መብታቸውን እየጨፈለቀ ለመናገር የሚታክት በደል ፈጽሞባቸዋል። አኑራድሃ እንዳሉት “መሬት የመንግስት ነው” በሚል ዜጎችን የግድግዳና ጣሪያ ባለቤት በማድረግ ከቅድመ አያት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ሃብታቸውን ዘርፏቸዋል።
ይህ አገር እየመራ እንኳን ራሱን በነጻ አውጪ ስም የሚጠራ ድርጅት በር ዘግቶ በዜጎቹ ላይ የሚፈጽመውን ተግባር በማጋለጥ ቅድሚያ የያዘው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ነበር። ይህንን አቢይ ተግባር ጊዜ በመውሰድ ያጠናውና በመረጃ በማስደገፍ ስርዓቱ የህዝቦችን ደም እንደሚጠጣ ያጋለጠው አቶ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ለነዚህ ወገኖች አንደበት በመሆን በዝግ የሚፈጸመውን ርህራሄ የጎደለው ግፍ ይፋ እንዲሆን አደረገ። “እመራዋለሁ” የሚለውን ህዝብ በንዋይ፣ ለዚያውም በዓለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሂሳብ ድንግል መሬት የሚቸበችበው ህወሓት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ አንድ ሄክታር መሬት ከአንድ ዶላር በታች እንደ ጉሊት ጨው መቸርቸሩ ይፋ መሆኑንን ከሰሙ መካከል የኦክላንድ ተቋም ቀዳሚ ሆነ።
አቶ ኦባንግ ሜቶ
በቅርቡ የአማርኛው ትርጉም ይፋ የሚሆነውን “በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” የተሰኘውን ጥናት ያካሄደው የኦክላንድ ተቋም አቶ ኦባንግ ከሚመሩት ድርጅት ጋር በጋራ እየሰራ የሚገኝ ነው፡፡ ይህንንም ጥናት ተግባራዊ ለማድረግና በዘገባ መልክ ለማውጣት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያደረገውን አስተዋጽዖ የተቋሙ ዳይሬክተር በአደባባይ የሚመሰክሩት ሲሆን ለጥናቱ የጀርባ አጥንት በመሆን ያሳየውን ዕገዛ ያደንቃሉ፡፡ ተቋማቸው ባደረገው በዚህ ጥናት ኢትዮጵያን አስተዳድራለሁ የሚለው ኢህአዴግ ዜጎቹን ሳያማክርና ፈቃድ ሳይጠይቅ እንደ አሮጌ እቃ በየስርቻው የሚጥል አገዛዝ መሆኑን በማስረጃና በተግባር አራግፈው በአደባባይ ሰቀሉት።
ህንድ እንዴት ተደረሰ?
“የወረቀት ትግል ውጤት የለውም” ሲሉ የሚከራከሩ ነበሩ። አሁንም አሉ። አቶ ኦባንግ ግን በተቃራኒው ይህንን አስተሳሰብ አይቀበሉም። ህንድ አገር ስለመድረሳቸው ዋና ምክንያትና አጋጣሚ ተጠይቀው “ህንድ አገር ባጋጣሚ አልሄድኩም” በማለት መልሳቸውን ይጀምራሉ። በኢትዮጵያ ያለውን ስርዓት የለቀቀ አገዛዝ የሰለቻቸውን ዜጎች ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት ድርጅታቸው በየደረጃው ያስቀመጣቸው አካሄዶች እንዳሉ ይናገራሉ። “ህንድ አገር በመሄድ የህዝብ ለህዝብ የተቀናጀ ትግል እንደምናደርግ ያቀድነው አስቀድመን ነው። በዚህ አያቆምም። በእቅዳችን መሰረት እንቀጥላለን” የሚሉት ኦባንግ ሜቶ በኢትዮጵያ የሚካሄደው የመሬት ዝርፊያ ማቆሚያ እንደሚበጅለት በርግጠኛነት ያስረዳሉ። ይህ ግን የድርጅታቸው የመጨረሻ ግብ አይደለም።
ምን ውጤት ተገኘ?
ካሩቱሪ የተባለው ድርጅት በኢትዮጵያ ድንግል መሬት በመውሰድ ቅድሚያ አለው። ይህ ድርጅት የሚጠራው በህንዶች ስም ነው። በህንድ መንግስት በተወሰነ መልኩ የሚደገፍም ነው። በርካታ የአክሲዮን ባለድርሻዎችን ያሰባሰበ ነው። መሰረታዊው የምክክሩ ዓለማ የህንድ ወንድምና እህት ህዝብ እያወቁ እነሱ ታግለው ድል የነሱት የመሬት ዝርፊያ በነሱ ስም በሃያ አንደኛው ክፍለዘመን በኢትዮጵያዊያን ላይ መካሄዱን ማሳወቅ ነበር።
በዚሁ መሰረት ዜጎች ከራሳቸው ምድር ላይ እየተፈናቀሉ፣ እየተገረፉ፣ እየተገደሉ፣ እየተሰደዱ ወዘተ መከራ ሲደርስባቸው እንደነበር የሰሙ አዘኑ። “ይህ በስማችን ስለመደረጉ አናውቅም ነበር” ሲሉ ሃዘናቸውን ገለጹ። አንድ አዛውንት የስብሰባው ተሳታፊ “በኢትዮጵያና በህንድ ህዝብ መካከል ልዩነት የለም። አንድ ነን። ተያይዘን እንታገላለን። ህብረት እንፈጥራለን። ተያይዘን የምንታገልበት አንድ ቀን አሁን ነው” ሲሉ አስተያየት ሰጡ።
“ትግል እቅድ ይጠይቃል። ትግል ህዝብን የማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልም ሊኖረው ይገባል። አሁን ምን እናድርግ? ከምን እንጀምር” የሚል ጥያቄና የትግል ዝግጁነት ተሰማ። ለተከታታይ ቀናት የተካሄደውን ምክክር የህንድ ብሄራዊ ሚዲያዎችና ታዋቂ የዓለም መገናኛዎች ለህብረተሰቡ ይመግቡ ስለነበር፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ውይይት በመደረጉ ካሩቱሪ ተሸበረ።
የህንድ ዜጎች ምን ያደርጋሉ?
“በስማችን ወንጀል ሊሰራ አይገባም። በመንግስት ስም የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲካሄድ ዝም ብለን አንመለከትም። መንግስት ለካሩቱሪየሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ እንዲያቆም፣ የካሩቱሪ ባለ አክሲዮኖች ለዚህ ክፉ ተግባር ተባባሪ ከመሆን ተቆጠቡ” የሚሉና በየደረጃው እየጠነከረ የሚሄድ ማስገደጃ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተሳታፊዎቹ አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ባለሃብቱንና ባለ አክሲዮኖቹን በማስጨነቁ የድርጅቱ የባለ አክሲዮኖች ስብሰባ ከመካሄዱ በፊት የሚጀመረው ዘመቻ በጎርፍና በከብት መንጋ ኪሳራ ደርሶበት የነበረውን ኩባንያ በኪሳራ እስከማዘጋት የሚደርስ ትግል እንደሚደረግ ቃል ከማስገባት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ አቶ ኦባንግ ይናገራሉ። አይያዘውም “የሰከነ ትግል ውጤቱ አሁንም በሰከነ መንፈስ በመከታተል የሚታይ ይሆናል። በዚህ አይበቃም ይቀጥላል። በስሜትና ጊዜያዊ በሆኑ ጥቅሞች ሳንነዳ እቅዳችንና ግባችን በሚያዘን መሰረት እንጓዛለን” ሲሉ ለጎልጉል ተናግረዋል።
መንግስት ለምን ፈራ?
ኢህአዴግ ስብሰባውንና የስብሰባውን ውጤት የፈራው ጥቅሙን ስለሚያጣ ነው። ካሩቱሪ ለቅቆ ሲወጣ ሁሉም መሬት ለመንጠቅ የመጡ ባለሃብቶች በየተራ ይወጣሉ። ይህ ዶላር ፍለጋ የሚምልባቸውን ምስኪን ህዝቦች እየገፋ ያለ ስርዓት ለአፈናው ለሚያወጣው ከፍተኛ በጀት፣ ለተነከረበት ከፍተኛ ሙስናና ዝርፊያ የሚሆን ገቢ ሲያንሰው የራሱ “ሌቦች” ጭምር ስለሚከዱት የህንድ ወገኖች እያሳዩ ያሉት ተቃውሞ ሳይነድና ሳይጠነክር አስቀድሞ ለማስቆም ህወሃት/ኢህአዴግ ሩጫ ጀምሯል።
የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት በህንድ አገር የተካሄደው ምክክር በተጠናቀቀበት እለት ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ለኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ደብዳቤ ተጽፎላቸዋል። ደብዳቤው ዋና ዳይሬክተሯን ለማነጋገር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ጉዳዩም አሁን በተጀመረው ዘመቻ ዙሪያ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። አቶ ኦባንግ ጉዳዩን አስመልክቶ ለተጠየቁት ሲመልሱ “የመሬት ነጠቃን በተመለከተ ማንኛውም ዓይነት ውይይት አይታሰብም። የተላከው ደብዳቤ ምንም ይሁን ምን አኑራድሃ ስለ ኢትዮጵያ መንግስትና ስለ ቅጥፈቱ ከበቂ በላይ መረጃ ስላላቸው ሊያሳስቷቸው አይችሉም። እኛም በብዙ ፈርጁ ከምናካሂደው ትግል አንዱ በመሆኑ ነቅተን ጉዳዩን እንከታተለዋለን” የሚል መልስ ሰጥተዋል።
maleda times | February 18, 2013 at 8:27 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1rQ
Comment

        

Sunday, February 17, 2013

Ethiopia’s real ambassador-at-large(By Abebe Gellaw)

 

Abebe Gelaw
Ethiopia has so many “ambassadors” and “diplomats” across the globe. Unfortunately, they neither represent our country nor can proudly stand in front of the oppressed people of Ethiopia. If at all they dare to do so, they know that they will be booed, condemned and pelted with rotten eggs, if not worse. The reason why they are held in great contempt is that they are emissaries of tyranny that constantly lie and degrade themselves to please their TPLF paymasters. The opportunists and sycophants that shamelessly call themselves Ethiopian diplomats and ambassadors are actually willing accomplices of TPLF’s untold crimes, oppression and plunder against the poor people of Ethiopia.
One of TPLF’s admirable skills is admittedly grooming and recruiting servile puppets and opportunists in different colors and stripes, such as Hailemariam Desalegn, Girma Woldegiorgis, Shimelis Kemal and Tesfaye Habiso, who will do and say anything as long their bellies are taken care of. TPLF’s Trojan horses, disguised as ambassadors, like Girma Biru, Genet Zewidie, Dawit Yohannes, Kassahun Ayele, Fisseha Yimer, Berhanu Kebede, Suleiman Dedefo, Teshome Toga, Konjit Sinegiorgis, Tekeda Alemu et al, not to mention TPLF’s first-class emissaries and missionaries all over the world, are unscrupulous messengers of the criminals in power. They are driven by greed, self-interest and TPLF’s privileged reps at every embassy. They loyally and slavishly serve their masters at Arat Kilo that have been committing all sorts of brutal repressions and atrocities against the people of Ethiopia. Quite obviously, their bellies are always full but, alas, their conscience is starkly empty.
The greater majority of “ambassadors” and “diplomats” shamelessly tell the world that Ethiopia is democratizing,human rights is constitutionally guaranteed, free press is flourishing, the economy is booming without saying whose economy it is….They are willingly enslaved to constantly condemn the past and praise the prevailing apartheid system under the guise of ethnic federalism. After all, it they dare to tell just a gain of truth, they know they will be booted out by the TPLF. That is why they are just wagging their tails like hungry dogs to please their masters that throw them some bones to gnaw.
While the so-called ambassadors and diplomats work against the basic interests of Ethiopia and Ethiopians, there are unpaid missionaries of freedom that have been traveling far and wide to defend liberty, condemn tyranny and expose the daylight robberies in Ethiopia. One man stands tall above others. Our brother artiste and activist Tamagn Beyene, who has been the unwavering voice of truth and freedom for over two decades, is undoubtedly one of Ethiopia’s real ambassadors serving the nation tirelessly and selflessly. Unlike TPLF’s bogus ambassadors and diplomats, who represent no one but tyranny and brutality, Tamagn speaks the unvarnished truth loudly and clearly.
Had Tamagn just wanted to fill his belly at the expense of his conscience, he would have stayed closer to his former friend, billionaire tycoon Sheik Mohammed Al Amoudi. In a video clip I had once the privy to watch, Al Amoudi praises Tamagn gushingly as his most beloved brother. He said Tamagn never asked him to do anything for himself but to be generous to others. But the most serious difference between them appears to be the Sheik’s blind support to the TPLF regime, the ethno-fascist oppressive front that has been dividing and misruling Ethiopia for over two decades. When Al Amoudi became one of the sponsors of TPLF’s tyranny, the once respected billionaire fell from grace and his immense fortune proved to be not worthy enough to buy back the genuine respect and love of the Ethiopian people. No matter how poor Ethiopians are, they know their true friends and allies irrespective of their wealth.
The tireless Tamagn never says no when it comes to promoting the interests of Ethiopia and Ethiopians across the world. I had the privilege to travel to a few cities with Tamagn for ESAT’s fundraising events. His unmatchable love for his country, his passion for freedom, unwavering voice for the truth, humor and eloquence has won him genuine admiration and respect among his fellow Ethiopians.
Tamagn is currently touring Europe to garner support for ESAT, which has emerged as a powerful voice for Ethiopia. Wherever he goes, patriotic Ethiopians come out in full force to receive and honor him. While TPLF emissaries are held in contempt and spat at wherever they go, Tamagn Beyene gets accolades and flowers. While Ethiopia’s so called ambassadors and diplomats hide from the ordinary men and women that they were supposed to serve as servants, Tamagn enjoys acclamations and standing ovations. In contrast to that, when “Ethiopian” embassies hold meetings, the majority handpicked to attend are surely TPLF agents, members and their cronies. The rest of Ethiopians who are asking hard questions are excluded shamelessly.
There may indeed be a few junior diplomats, but certainly none at ambassadorial and high-ranking levels, that want to serve their country and people with integrity. But that is obviously mission impossible as long as they humbly serve their blood sucker paymasters at every embassy, which have been effectively converted into TPLF’s foreign offices at the expense of poor taxpayers. They all know full well that even the ministry of foreign affairs, the supposed command center of diplomacy, is one of the useless government agencies that have been crippled with discrimination, corruption and nepotism. In order to serve as a diplomat, the most important criterion is being slavish and servile to the TPLF. Never tell any inconvenient truths that can offend the TPLF. That is the unwritten rule that no one can break.
The famous journalist and scholar Isaac Goldberg (1887-1938) once said that diplomacy is the art of doing and saying the nastiest things in the nicest way. Unfortunately, our ambassadors and most of our diplomats do and say the nastiest things in the nastiest way. In the process, they have lost their conscience, honor and dignity for the sake of serving the TPLF, one of the worst terrorist organizations in the world. If there are any “diplomats” with a conscience, they should join the struggle for freedom and dignity, sooner rather than later. It is better to starve in dignity and earn a living by working hard rather than being paid for standing against the oppressed people of Ethiopia.
Let every “diplomat”, irrespective of their rank, answer one simple question honestly. Who are you serving? The people of Ethiopia, yourself or TPLF’s ethno-fascistic tyranny. We already know the answer but you also need to sleep over it.
As far as so many Ethiopians are concerned, Tamagn Beyene is the foremost but unpaid ambassador-at-large of Ethiopia, who is inspirational to millions of Ethiopians. On the contrary, the depressing agents and emissaries of tyranny, whose main mission is lying on behalf of the despicable TPLF-led regime, are condemned to live in hiding—not from criminals but from the ordinary men and women that they were supposed to serve with clear conscience and utmost humility.
Some people may wonder what an ambassador-at-large does. According to the Macmillan Dictionary of Diplomacy, an ambassador-at-large is a diplomat or a minister of the highest rank who possesses great experience and as a result appointed to handle major issues without being tied to a particular country. As per diplomatic protocol, an ambassador-at -large is addressed as His/Her Excellency.
I personally salute Tamagn for his patriotism, integrity and struggles for freedom. I see him as my older brother with admiration and veneration. As Tamagn said once, everyone one of us have a calling to stand for the dignity and liberty of our country no matter how high the cost is. If few individuals can make a difference, all the oppressed people of Ethiopia can do miracles when they rise up in unison against TPLF’s unjust war against Ethiopia and its people. Yes, we can undoubtedly reclaim our God-given liberties and the land we can proudly call Ethiopia.
His Excellency Tamagn Beyene, represents me and millions of freedom-loving and voiceless Ethiopians wherever his goes. He has the full authority to speak on behalf of ordinary Ethiopians like me that aspire to make tyranny history in our beloved country suffering under oppressors and occupiers. The unpaid ambassador-at-large serves us with utmost integrity unlike those who will be asked, sooner or later, to reimburse all the salaries and benefits that they are paid for working against the people of Ethiopia.
Your Excellency Tamagn Beyene, I take my hats off for your unflinching, unwavering, consistent and vocal stand against the ethno-fascistic enemies of freedom that have turned our country into one giant prison. We will march together until tyranny is defeated in Ethiopia once and for all.
In the end, we shall overcome!
staff reporter | February 16, 2013 at 11:44 pm | Categories: Africa | URL: http://wp.me/p2gxmh-1ru

Comment   

Saturday, February 16, 2013

:“ሠራዊቱና አብዮታዊ ዲሞክራሲ” የሚለው ቀዩ መፅሃፍ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ አለመሆኑን ያረጋግጣል::

 

Gudu  Kassa
“ሠራዊቱና አብዮታዊ ዲሞክራሲ” የሚለው ቀዩ መፅሃፍ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ አለመሆኑን ያረጋግጣል::

የአረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉዓላዊነት (አረና) ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ገብሩ አስራት በበኩላቸው፤ ስለ ኤግዚቢሽኑ እንዲሁም ስለ ወታደራዊ ተግባራቱ በሚዲያ እየቀረቡ ያሉትን ከመከታተል ባለፈ በአካል እንዳልተመለከቱት በመግለፅ፤ በአሉን አስመልክቶ እየቀረቡ ያሉት መሣሪያዎች ግን መከላከያው ብቃት ያለው መሆኑን የሚያስመሰክሩ ሆነው እንዳላገኟቸው አስታውቀዋል፡፡ የሀገራችን መከላከያ ሃይል ተጠናክሮ የሀገሪቱን ደህንነት በሚገባ እንዲያስጠብቅ እፈልጋለሁ የሚሉት አቶ ገብሩ፤ የኛ ተቀናቃኞች ዛሬ ታንክና ተዋጊ ጀት ከመገጣጠም አልፈው ኒውክለር እየሰሩ ባለበት ሁኔታ እነሱን የሚመጥን ዝግጅት ሳናደርግ የመከላከያው ብቃት አድጓል ማለት እንደማይቻል ይገልፃሉ፡፡ በህገ መንግሥቱ አንቀፅ 87 ንዑስ አንቀፅ 5 ላይ የመከላከያ ሠራዊቱ ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነፃ በሆነ አኳኋን ያከናውናል የሚለውን ድንጋጌ መነሻ በማድረግ የገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም የሆነው አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለሠራዊቱም ዋና መመሪያና መንቀሳቀሻ መሆኑ ተገቢ አለመሆኑን አቶ ገብሩ ተናግረዋል፡፡
በተለይ ቀዩ መፅሃፍ እየተባለ የሚጠቀሰውና “ሠራዊቱና አብዮታዊ ዲሞክራሲ” የሚለው መፅሀፍ የሠራዊቱ ዋና መመሪያ መሆኑ መገለፁ፣ ተቋሙ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ አለመሆኑን እንደሚያረጋግጥም አቶ ገብሩ ተናግረዋል፡፡የአረና ሊ/መንበር በቀመጠል ሲናገሩም፤ የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ብቻ እንደሆነ ተደርጐ መቅረቡ እሳቸው ከሌሉ የሠራዊቱ ቀጣይ እጣ ፋንታ ምን ይሆናል የሚለውን ጥያቄ እንደሚያጭርና የሁሉም ነገር አድራጊ ፈጣሪ እሳቸው ከሆኑ ሌላው ከተላላኪነት የዘለለ ሚና የለውም የሚለውን አንደምታ አጉልቶ እንደሚያሳይም ገልፀዋል፡፡ የመድረክ አመራር አባል የሆኑት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ እንዲሁ ኤግዚቢሽኑን በጊዜ መጣበብ ሊመለከቱት እንዳልቻሉ፣ ነገር ግን በሚዲያ የሚተላለፉትን መልክቶች እና ህዝቡ የሚሰጠውን አስተያየት ማጤናቸውን በመጠቆም ስለወታደራዊ ሃይሉ የተጋነኑ መልክቶች የተላለፉ እንደሚመስላቸው ገልፀዋል፡፡ በበአሉ አከባበር ላይ የተንፀባረቀውም የመከላከያው የኢንዱስትሪ ዘርፍ እድገት እንጂ የሰው ኃይል ልማት፣ በመከላከያ ውስጥ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ መከላከያው ጥቃትን የመቋቋም አቅሙን የሚፈትሹ ጉዳዮች እንዳልሆኑ ያስታወሱት ፕ/ር በየነ፤ በተለይ በአሁኑ ሠዓት በአመራሩና በተራው አባል መካከል የጌታ እና የሎሌ አይነት የእዝ ሰንሰለት ነው ያለው የሚል ቅሬታ እንደሚቀርብ፣ በዚህ አይነት ቅሬታ ከሠራዊቱ የወጡ አባላት የነገሯቸውን በመጥቀስ ገልፀዋል፡፡
ይህን ወቅት ጠብቆ እንዲህ ባለ ሥነሥርዓት የወታደሩን አቅም የማቅረቡ ፋይዳ ምንድን ነው የሚል ጥያቄ አለኝ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፤ “አሁን እየተወራለት ያለው የወታደራዊ ኢንዱስትሪ ከኢህአዴግ በፊት በነበረው ስርአት የተጀመረበት ሁኔታ ነበር፡፡ እነሱ ብቻ የጀመሩት አድርገው ማቅረባቸው ተገቢ አይደለም፤ አበልፅገነዋል፣ አሻሽለነዋል የሚሉ ከሆነ መልካም ነው፡፡ የሁሉም ነገር ጠንሳሽ ነን የሚለው ግን የሚያስኬድ አይደለም” በማለት አስተያየታቸውን ቋጭተዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ አመራር እና የፓርላማ አባል የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ፤ አውደ ትርዒቱን ገና እንዳልተመለከቱት ነገር ግን በሚዲያ የተከታተሉትም ሆነ ስታዲየም በነበረው የበዓሉ መዝጊያ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው እንደታዘቡት፣ የመከላከያ ሃይላችን ጠንካራ ሆኗል ከሚሉት ሃይለ ቃሎች ውጪ ጠንካራ መሆኑን የሚያረጋግጡ ማሳያዎች እንዳልተመለከቱ ገልፀዋል፡፡ “ከዚህ የበለጠ በጣም የሚያስፈሩ የደርግ ሠልፎችን አይቼ አውቃለሁ” ያሉት አቶ ግርማ፤ የመከላከያ ቀን መከበሩ መልካም ሆኖ ሳለ ዓላማው ግልፅ ባለመሆኑ አልገባኝም፣ ከዚህ ቀደም ይወራ ከነበረውም የተለየ አዲስ ነገር አልቀረበም” ብለዋል፡፡
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ራሱን ችሎ የወጣ ድርጅት መሆኑን ያስታወሱት አቶ ግርማ፤ ሆኖ ሳለ ከመከላከያ ጋር ተሳስሮ መቅረቡ በራሱ አግባብ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ አንዳንድ በአውደርዕዩ ላይ ቀረቡ የተባሉ እንደሰው አልባ ጀት የመሳሰሉት ለእይታ መቅረባቸውን ሲቃወሙም ተቀናቃኝ ሃይሎች ማክሸፊያውን ለማዘጋጀት እድሉን ይሰጣቸዋል ብለዋል፡፡
በኤግዚቢስን ማዕከል የቀረበውን መጐብኘታቸውን የገለፁት ኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ሙሼ ሰሙ፤ እዚህ የፈጠራ አቅም ላይ መደረሱ በራሱ የሚደነቅ ሆኖ ሳለ የቀረቡትን ናሙናዎች ብቻ በማየት አጠቃላይ ወታደራዊ አቅማችን አድጓል ለማለት እንደማያስደፍር ተናግረዋል፡፡ “የመከላከያው አቅም በሚገባ ጐልብቷል ለማለት የቀረቡት ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎች አድገውና ተባዝተው መቅረብ አለባቸው” የሚሉት አቶ ሙሼ፤ አንዳንድ ከወታደራዊ ቴክኖሎጂ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ነገር ግን በመከላከያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች እንዳላስደሰታቸው ይናገራሉ፡፡

በግል ባለሀብቶች፤ ኢንቨስተሮች ሊከወኑ የሚችሉ የመኪና መጠጋገንና መገጣጠም የመሳሰሉት ሥራዎች ከመከላከያ እጅ ሊወጡ እንደሚገባቸውም አቶ ሙሼ አሳስበዋል፡፡ “የመኪና መጠጋገን የመሳሰሉ ስራዎች ውስጥ መንግሥትና የመንግሥት ተቋማት ሊገቡ አይገባም፤ ይሄን የግል ዘርፉ ሊሰራው ይችላል፡፡ አንዳንዶችም ሰርተው እንደሚቻል እያሳዩ ነው፡፡ መንግሥት የሚገባው የግሉ ዘርፍ ሊሸፍነው የማይችለው ሲሆን በቻ ነው” ያሉት አቶ ሙሼ፤ ወታደራዊ ተቋሙ እስካሁን የሰራውን በአጠቃላይ ቢያደንቁም ይበልጥ ትኩረት ሊሰጥ የሚገባው ኢትዮጵያ አንድ ችግር ቢገጥማት በብቃት እንድትከላከል የሚያስችላትን ታንክ፣ አውሮፕላን እና ሌሎች ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችን በማምረቱ ላይ እንደሆነ አመልክተዋል፡