Friday, July 24, 2015

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበ

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ የጀመሩትን ታሪካዊ ሀገር የማዳንን ትግል ዳር ለማድረስ ወደ ኤርትራ መግባታቸው ተዘገበ

July 19, 2015
/ ብርሃኑ ነጋ ከቃሊቲ እስር ተፈተው ቀደም ሲል ይኖሩበት ወደነበረው አሜሪካን ሀገር ከተጓዙ በኋላ አፍታም ሳይቆዩ ነበር የሁለገብ ትግልን አስፈላጊነት መናገር የጀመሩት። / ብርሃኑ ወዲያውም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ ከሌሎች ሃሳባቸውን ከሚጋሩ ስመጥር ፖለቲከኞች እና የለውጥ አራማጅ ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄን መሰረቱ፣ በወቅቱ / ብርሃኑ የእርሳቸውን እና በግንቦት 7 ዙሪያ የተሰባሰቡ ጓዶቻቸውን ቁርጠኛነት ሲያስገነዝቡዘረኛውን የወያኔ አምባገነን አገዛዝ ከህዝብ ጫንቃ ላይ ለማውረድ የማንፈነቅለው ድንጋይ አይኖርምነበር ያሉት።



https://www.youtube.com/watch?t=16&v=b-upNBStOVM

ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ 7 ጠንካራግንቦት የተዋጊ ሃይል ማቋቋም የቻለ ሲሆን ለጥቆም ቀደም ሲል ጀምሮ ወያኔን ማስወገድ የሚቻለው በሃይል ብቻ ነው በማለት መስዋዕትነት በመክፈል ላይ ከነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ጋር በመዋሃድ የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄን መፍጠር ተቻለ።
ዛሬ በወያኔ እጅ ወድቆ የሚገኘው በሳሉና ቆራጡ ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እስካሁን ግንቦት 7 በተጓዘባቸው የስኬት ጎዳናዎች ሁሉ አሻራው እንዳለበት በቅርብ አብረውት ሲታገሉ የነበሩ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ይመሰክራሉ።
በወጣት አርበኞች የተገነባውና እራሱን ለውጊያ ብቃት ሲያደራጅ የሰነበተው አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ ክንዱን ማሳረፍ በጀመረ ማግስት ነው እንግዲህ የንቅናቄው መሪ / ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም አመራሮች በአካል የትግሉን ጎራ ለመቀላቀል ወደ ሜዳ የወረዱት።
የዶ/ ብርሃኑ ነጋንና የሌሎች አመራሮችን የትግሉን ጎራ በአካል መቀላቀል አስመልክቶ ንቅናቄው ባሰራጨው አጭር መልዕክት እንደገለጸው፣
የተቀደሰ አላማን ያነገብን እርኩስ አላማን በሚያራምዱት ላይ ድልን እንቀናጃለን፣ / ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም የንቅናቄው አመራሮች የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ነጻነት፣ የፍትህ እና የዴሞክራሲ ጎዳና እንደሚመሩት ጥርጥር የለንምብሏል።
አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ቀጥሎ ባለበት ሁኔታ የዶ/ ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎችም የንቅናቄው አመራሮች በአካል ከአርበኞቹ ጎን መገኘት ከፍተኛ ሞራል እና መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በአለም አቀፍ ህብረተሰብ ዘንድ ከፍተኛ ተደማጨነት ያላቸው የሰላምና የዴሞክራሲ ግንባር ቀደም ታጋይ ናቸው። ይህን ችሎታቸውም ኢትዮጵያን ወደ ነጻነት ለመውሰድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

No comments:

Post a Comment