Saturday, March 21, 2020

Why have many coronavirus patients died in Italy?




The country's high death toll is due to an ageing population, overstretched health system and the way fatalities are reported.
Of the 47,000 people confirmed coronavirus patients in Italy, 4,032 so far have died - with a record increase of 627 in the last 24 hours.
By contrast china has almost twice as many cases ,81,250, but 3,253 fatalities
In very crude terms, this means that around eight per cent of confirmed coronavirus patients have died in Italy, compared to four per cent in China. By this measure Germany, which has so far identified 13,000 cases and 42 deaths, has a fatality rate of just 0.3 percent.
So Why the disparity?
According to Prof Walter Ricciardi, scientific adviser to Italy’s minister of health, the country’s mortality rate is far higher due to demographics - the nation has the second oldest population worldwide - and the manner in which hospitals record deaths.
Country
cases
deaths
%age
Median age
china
81,303
3,259
4
67
Italy
47,021
4,032
8
46
Spain
21,571
1,093
5

Iran
20,610
1,556
7.5

Germany
20,046
69
0.3

USA
19,774
275
1.4

France
12,632
450
3.5

South ko
8,799
102
1

uK
3,983
177
4







A study in JAMA this week found that almost 40 per cent of infections and 87 per cent of deaths in the country have been in patients over 70 years old.




Monday, March 16, 2020

Wednesday, March 11, 2020

Monday, March 2, 2020

Saturday, February 22, 2020

ዘመዱ ደምስስ - ጦቢያ ግጥምን በጃዝ #103-02 | [Arts TV World]

የአዲስ አበባ ወጣት ለንጉሱ ያለውን ፍቅር ተመልከቱ የዛሬው ልዩ ነው

Ethiopia - ESAT በቅዳሜ "ና" እሁድ ክፍል 2 - Feb 22,2020

ለክቡር ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር አዲስ አበበ፤ ኢትዮጵያ፤ ዛሬም አሰብን እንላለን! በያዕቆብ ኃይለ ማርያም


 የአድህሮትና የክፍፍል በአንድ ጎራ፤ የነጻነትና የአንድነት ኃይሎች በሌላው ጎራ፤ ሰቅዞ፤ በያዛቸው ትግል ዉስጥ ሆነው፤በሚፋለሙበት በዚህ ተስፋ ሰጪ ወቅት፤የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዛሬ ማንሳት፤ዋናው የተጀመረዉ በጎ እንቅስቃሴ፤ ማዘናጋት እንዳይሆን የሚሰጉ ሰዎች ይኖራሉ። ሆኖም የአሰብ ባለቤትነት ጥያቄ የአገር ሕልዉናና ልማት ጥያቄ አንዱ አካል እንደመሆኑ መጠን፤ዛሬ በተከሰተዉ ብዙ ተስፋ ከጫረዉ የዲሞክራሲና የአንድነት እንቅስቃሴ ጋር ተደምሮ ገና በጥዋት መነሳት ያለበት ጉዳይ ነዉ። የአሰብን ጥያቄ ግዙፍነት ተረድተዉ አዲሶቹ የኢትዮጵያ መሪዎች በቅድሚያ አጀንዳቸዉ ዉስጥ እንዲያካትቱት በአክብሮት ለማሳሰብ ነዉ። ዛሬ የተነሱት የኢትዮጵያ መሪዎች የኢትዮጵያን ጥቅሞችና መብቶች የሚያስከብሩ ናቸዉ የሚል ፍንጭ ስለአየን ግዳዩን እንድናነሳ ቀሰቀሰን። ኤርትራ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ተገንጥላ፤ የኢትዮጵያን ሉዐላዊ ግዛት የነበረችዉን አሰብን ስትይዝ፤አሰብ በታሪክ፤በሕግና በስነመንግሥት እሳቤ የኤርትራ አካል እንዳልነበረች ለማስረዳት ኢትዮጵያዉያን ምሑራን ያልፈነቀሉት ድንጋይ፤ ያልማሱት ስር አልነበረም። በወቅቱ አሰብ የኢትዮጵያ ግዛት ለመሆኗ ለማስረዳት ያህል ኢትዮጵያዊ ጉዳይ አልነበረም። የአገሪቱ ፕሬዚደንት የነበሩት መቶ አለቃ ግርማ ወልደጊዮርጊስ የኢሓደግ ባለሥልጣናት አቶ መለስ ዜናዊ፤ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝና አቶ በረከት ስመዖን ከመንገዳቸዉ ወጥተዉ፤ አሰብ የኤርትራ ግዛት ነች፤ኢትዮጵያ በአሰብ ላይ ምንም መብት የላትም ሲሉ መስክረዋል። ይኸ ስም ማጥፋት ሳይሆን በሰነድ ሊረጋገጥ የሚችል ጉዳይ ነዉ። እ.አ.አ. በ2000 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በኤርትራ መሃከል በተደረገዉ አላስፈላጊና ትርጉም የለሽ ጦርነት በኢትዮጵያ ድል አድራጊነት እንደሚደመደም ግምት ተወስዶ ስለነነበረ፤ ጦርነቱ አልቆ ወደ ድርድር በሚኬድበት ጊዜ ለኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ግበዐት የሚሆኑ፤ በሕግና በታሪክ የተደገፉ ሃሳቦች፤ ምሁራን በተለያዩ ሚዲያ አቅርበዉ ነበር። ጦርነቱ እንደተጠበቀዉ በኢትዮጵያ አሸናፊነት ሲደመደም ኢሕአደግ ከመነሻዉ፤ኤርትራን ለማስገንጠል በብዙ የደከሙት የኢትዮጵያ ጠላት የአልጄሪያዉ ፕሬዚደንት ቡተፍሊካን አስታራቂ እንዲሆኑ ጠየቀ። ቡተፍሊካም አቶ ኢሳያስን ና አቶ መለስን አጨባብጠው ዉዝግቡ ዓለም ሁሉ እምነቱ ወደጣለበት ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት (International Court of Justice) ከመውሰድ ፈንታ በገንዘብ በተገዙ ግለሰቦች እንዲዳኝ የድንበር ኮሚሽኑ ጉዳይ ወደዚያ ተመራ። እዚህ ላይ አንድ አስገራሚ ምናልባትም በአገር ክሕደት ወንጀል የሚያስጠይቅ በደል መጠቀስ አለበት። የድንበር ኮሚሽኑ ዳኞች የቀረበላቸውን ማስረጃዎች ተንተርሰዉ ጾረና የኢትዮጵያ ግዛት መሆኗን ዉሳኔ በሚሰጡበት ጊዜ በኢትዮጵያ መንግሥት ተእዛዝ ኢትዮጵያን የወከሉ ጠበቆች፣ “የለም ተሳስታችኋል፤ ጾረና የኤርትራ ግዛት ነዉ” ብለዉ በመከራከራቸዉ ዳኞቹ ምርጫ በማጣት ጾረናን ወደ ኤርትራ አካለሉት።በታሪክና በሕግ ሥነ መንግሥት የተካኑ ኢትዮጵያዉያን አገልግሎታቸዉን በነጻ እንደሚለግሱ ቢረጋገጥም፤ ኢሕአደግ ስለኢትዮጵያና ኤርትራ ታሪካዊና ወቅታዊ ግንኙነት ምንም ዕዉቀት የሌላቸዉ ዳኞች በዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ተቀጥረዉ፤ ጉዳዩ ወደነዚህ ዳኞች ችሎት ተመራ።

Saturday, February 8, 2020

የሌለው “ጭንብላችን” ቢገለጥ ምን ይመጣል? (በመስከረም አበራ)


Ethiopian writer, Meskerem Abera.ሃገራችን ሩብ ምዕተ-ዓመት በቆየችበት ህወሃት-መር የጎጠኝነት ፖለቲካ እንደ አማራው ግራ የተጋባ ህዝብ/ልሂቅ የለም፡፡አማራው ከጎጥ ፖለቲካው ጋር መላመዱ አልሆን ብሎት እስካሁን  በገዛ ሃገሩ እንደ መፃተኛ ሆኗል፡፡በጎጥ መደራጀቱ እንደ የማይገለጥ ምስጢር የሆነበት የአማራ ልሂቅ መገፋት ገፍቶት የመሰረተው መአድ የተባለው ፓርቲ ግማሽ ጎኑ  አፍታም ሳይቆይ ወደ ህብረብሄራዊ ፓርቲነት ሲቀየር መቀየሩን ያልወደደው ቅሪቱ መአድ እንደ ሲኒ ውሃ እያደር ተመናምኖ ወዳለመኖር የተጠጋ ሁኔታ ላይ  ነው፡፡ መአድ የተባለው ፓርቲ መኢአድ ወደሚባል ህብረ ብሄራዊ ፓርቲ የተቀየረው መለስ ዜናዊ አማራውን የሚያሳድድበትን በትር፣የሚያሳርድበትን ቢለዋ ወደ ሰገባው ሳይመልስ ነው፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው አማራው በጎጥ መደራጀቱን ስለማያውቅበት ነው፡፡ይህ የዘመኑን ፋሽን ያለመከተል የአማራው ግርታ ያደረሰበት ጉዳት መጠነ ሰፊ ነው፡፡
አማራን ሁሉ ባላንጣ አድርገው የሚያስቡ ኦነጋዊ የኦሮሞ ብሄርተኞች  የአማራ ልሂቃንን ለዘውግ ፖለቲካ ባይትዋርነት “አማራው የብሄር ፖለቲካው አልገባ ብሎት ሲደናገር ሩብ ምዕተ አመት ሞላው፤ይህ ለኦሮሞ መልም ነው” ሲሉ በመሳለቅ ይገልፁታል፡፡እነዚህ ቡድኖች አማራው ሲሞትም፣ሲፈናቀልም፣ሲንጓጠጥም ሲገደለም ዝም ማለቱ ብቻ ይስማማቸዋል፡፡አማራው መናገር ሲጀምር ኦነጋዊ የኦሮሞ ብሄርተኞች እና ህወሃታዊ ትግራዊያን  የሚናገረው ሁሉ ያስበረግጋቸዋል፡፡አማራው በዘውጉ የሚደርስበትን ሁሉ ችሎ የለመደውን ኢትዮጵያዊነት ሲያጠብቅ በኢትዮጵያዊነት ስም ፍላጎቱን በብሄረሰቦች ላይ የሚጭን ጨቋኝ ሲሉ ኢትዮጵያን በማለቱ በድንጋይ መወገር የሚገባው  ሃጢያተኛ አድርገው ያቀርቡታል፡፡ እነሱው በየደረሱበት በሚሰኩት የአማራ ጥላቻ ሳቢያ በአማራነቱ መሞቱ ተሰምቶት ኢትዮጵያዊነቱን ሳይጥል አማራነቱ እያስገደለው እንደሆነ ከተናገረ ደግሞ በጭብላምነት ያብጠለጠሉታል፡፡ አማራውም ይጥለው ዘንድ የማይችለውን ኢትዮጵያዊነት በደሙ ውስጥ ይዞ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋም ለመከላከል ቢጣጣርም አማራነቱን ማጠባበቁ ከኢትዮጵያዊነቱ የሚጋጭ እየመሰለው በፈራተባ ውስጥ ይኖራል፡፡
የአማራው ዘመን አመጣሹን የጎጥ ፖለቲካ ፋሽን ተረድቶ ራሱን ከዘመኑ ጋር ማራመድ አለመቻሉ(በባላንጣዎቹ ንግግር “ግራ መጋባት”) ቋጥኝ የሚያክል ፈተና ያንዣበበትን የአማራውን ህዝብ ያለጠበቃ አስቀርቷል፡፡የጎጥ ፖለቲካውን መላመድ ድሮ ቀርቶ ዛሬ ያልሆነላቸው የአማራ ምሁራን በአማራ ብሄርተኝነት መስመር ተሰልፈው ሌሎች እንደሚያደርጉት ለህዝባቸው መሞገት አለመቻላቸው ለኦነግ ግርፍ የኦሮሞ ብሄርተኞች እና ህወሃት ቀመስ ትግራዊያን የአባት ገዳይን በግላጭ እንደማግኘት ያለ ሰርግ እና ምላሽ ነበር፡፡ሆኖም በአማራው ላይ የሚወርደው ዱላ የተኛ ቀርቶ ሙት የሚቀሰቅስ እየሆነ ሲመጣ ዛሬ ላይ የአማራ ምሁራንም ከእንቅልፋቸው መንቃት ጀመሩ፡፡ይህ ደግሞ ለኦነጋዊ የኦሮሞ ብሄርተኞች እና ለህወሃቶች መልካም አዝማሚያ አይደለም፡፡ ለእነሱ መልካም የሚሆነው ባፈው ሃያ ሰባት አመት እንደሆነው አማራው ከሞት በበረታ ዝምታ ውስጥ ሆኖ ግድያውንም፣መንጓጠጡንም፣መፈናቀሉንም፣መገደሉንም አጎንብሶ ሲቀበልነው፡፡
ይህ ሁለት ጥቅም አለው፡፡ አንደኛው አማራው “በሰራው ታሪካዊ ወንጀል” የሚሸማቀቅ በደለኛ እንጅ ስልጣን የሚጋራ የፖለቲካ ሃይል አለመሆኑ ለኦሮሞ ብሄርተኛ ሁለተኛውን ግዙፍ ዘውግ ከስልጣን ተገዳዳሪነት ይቀንስለታል፡፡ ሁለተኛው ጥቅም በታሪክ በድሎናል የሚሉትን ህዝብ በማሸማቀቅ የሚያገኙት ስሜት በቀለኝነት የሚጋልበውን የስነ-ልቦና ቀውሳቸውን ተንፈስ ያደርጋል፡፡ ስለዚህ አሁን አሁን ከበደል ብዛት የተነሳ እያቆጠቆጠ ያለውን የአማራ ብሄርተኝነት አይወዱትም፡፡ ምክንያቱም የአማራው ብሄርተኝነት ካቆጠቆጠ አማራው ያለ ስራው የተለጠፈበትን የበደለኝነት ተረክ የሚያፈርስ መልስ መስጠት ይጀምራል፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ አማራውን ጭራቅ አድርገው የሚያቀርቡበትን ተረክ ብቻቸውን እያወሩ፣ያወሩትም እንደእውነት እየተቆጠረ ወደስልጣን ማዝም አይቻልም፡፡አማራውን የማይስተሰረይ ሃጢያት የሰራ በደለኛ አድርጎ ማሸማቀቅም አይቻልም፡፡ ስለዚህ አማራው በደሉ እንዲሰማው አይፈለግም! በአይን የሚታየውን በአማራ ህዝብ ላይ ያንዣበበ አደጋም ሆነ በዚህ ህዝብ ላይ በወያኔ እና ኦነግ  የተደረገውን ግፍ አንስቶ የሚሞግት አማራም ሆነ ሌላ የሰው ዘር አይፈለግም፡፡
ከወያኔ ወደ ስልጣን መምጣት ወዲህ በአማራ ህዝብ ላይ በርካታ በደል የተፈፀመ፣አሁንም ይህ ህዝብ በሃገሪቱ ባሉ የዘውግ ፖለቲከኞች ሁሉ በክፉ አይን የመታየት  ፈተና ውስጥ ያለ ቢሆንም የአማራ ምሁራን እና ልሂቃን ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነታቸውን የሚቀማቸው የሚመስላቸውን የአማራ ብሄርተኝነት መልበስ አይፈልጉም፡፡በአንፃሩ የወጡበት ህዝብ ያለበት ፈተናም ያሳስባቸዋል፡፡ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነታቸውን ሳይጥሉ ስለ አማራው ህዝብ እንግልትም ይሟገታሉ፡፡የአማራ ህዝብ ሁሉ ባላንጋራቸው የሚመስላቸው ኦነጋዊ የኦሮሞ ብሄርተኞች ደግሞ መለስ ዜናዊ እንዳደረገው የአማራን ህዝብ ያለ አንዳች ጠበቃ መቅጣት ስለሚፈልጉ ይህን ነገር አምርረው ይጠላሉ፡፡ኢትዮጵያዊነትን ሳይጥል የአማራ ህዝብ ለምን በገዛ ሃገሩ እንዲህ ይደረጋል የሚል የሚል የአማራ ልሂቅ ሲገጥማቸው ሌባ እጅ ከፍንጅ እንደያዘ ሰው ባለድልነት ይሰማቸዋል፡፡
ለአማራ ልሂቃን/ምሁራን ኢትዮጵያዊነት የክብር ልብስ እንጅ ጭንብል አይደለም!ኢትዮጵያዊነት ጭንብላችን ቢሆን ኖሮ በአማራ ህዝብ ላይ ከመለስ ዜናዊ እስከ ጃዋር መሃመድ ነጋሪት ጎሳሚነት የደረሰው በደል ጭንብል ቀርቶ ቆዳ የሚያስወልቅ ክፉ  ነውና “ጭንብል”  ወርውሮ ጎጠኛ መሆን አስቸጋሪ ሆኖ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊነት በአማራ ህዝብ/ልሂቅ/ምሁር ዘንድ በደም ውስጥ የሚሮጥ ልክፍት እንጅ ጭንቅላት ላይ ለይምሰል ሸብ የሚደረግ ቡቱቶ ጨንብል አይደለም፡፡የአማራ ልሂቃንን በጭንብላምነት የሚከሱ የኦሮሞ ብሄርተኞች ኢትዮጵያ እንደኩንታል አናታቸው ላይ ተጭና የምትከብዳቸው ሸክማቸው እንደሆነች የፈረንጅ ጋዜጠኛ እጅ እየመቱ የሚምሉ፣ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር ናፍቆተኞች ናቸው፡፡ ስለዚህ ሁሉም እንደነሱ ይመስላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያን ማለት ትርጉም ስለማይሰጣቸው ሁሉም እንደእነሱ ኢትዮጵያን በጭንብሉ፤መንደሩን ሃገር አሳክሎ በልቡ ተሸክሞ የሚጓዝ የማነስ ልክፍተኛ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ የሌለ ጭንብል ይፈልጋሉ፡፡
ለማንኛውም እነሱ ጭንብል የሚሉት ነገር ለአማራው ማን እንደጣለበት የማያውቀው፣በደሉን እንኳን እንዳይቆጥር የሚያደርግ ኢትዮጵያን የሚያስብለው ከደሙ ጋር በመላ ሰውነቱ የሚዞር ልክፍቱ እንጅ አናቱ ላይ የተንከረፈፈ ጭንብሉ አይደለም፡፡ይህ ልክፍቱ ነው ኢትዮጵያን ካለ ጋር ሁሉ የሚያዛምደው፡፡አማራው ኢትዮጵያን ይላል ማለት ግን ስሟ በተጠራበት ልገኝ በሚልላት ሃገሩ  አማራነቱ ወንጀል ሆኖ ሲያስገድለው ዘላለም የማይገባው ነፈዝ ነው ማለት አይደለም፡፡ኢትዮጵያዊ ሆኖም በአማራነቴ አትግደሉኝ ማለትን የሚከለክል ፍርደ-ገምድል ህግ የለም! “ኢትዮጵያዊ ነኝ ካልክ አማራ ነህ ብየ ስገድልህ አመጣጤ አይግባህ” የሚባል አካሄድ ድሮ ቀርቷል፡፡ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለውን ሰው አማራ ነህ ብሎ ገድሎ ያስገደለህን ምክንያት ስሙን አትጥራ ማለት የሞኝ ብልጠት ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለውን ሰው አማራ ነህ ብሎ የሚያስገድለው አባዜ ሁለቱንም የመጥላቱ በሽታ መሆኑን ማን ያጣዋል?
ለማንኛውም አማራው አጠለቀው የተባለው የኢትዮጵያዊነት ጭንብል የኢትዮጵያዊነቱን ከፍታም ሳይለቅ በአማራነቱ ሚመጣበትን ፍላፃም ለመከላከልም የመሞከሩ  የሚዛናዊነቱ ምልክት ነው፡፡ አማራውን ኢትዮጵያዊ ነኝ በል እያሉ ግን በአማራነቱ የሚገድሉት አዳኞች ደግሞ ይህን አይወዱምና ኢትዮጵያዊነት ከአማራው ላይ እንደማይወልቅም፣ ጭምብል እንዳልሆነም እያወቁ “ጭንብልህን አውልቅ” ይላሉ፡፡ አይሆንም እንጅ አማራው ችሎ ኢትዮጵያዊነቱን  እንደተንከረፈፈ ጭንብል ቢያወልቅ ለኢትዮጵያ መልካም አይሆንም፡፡ አማራው ኢትዮጵያዊነቱን አወለቀ ማለት ትልቁ የኢትዮጵያ አእማድ ፈረሰ ማለት ነው፡፡ ይሄኔ ኢትዮጵያዊነት በአማራነት ይተካል፤ከተተካ ደግሞ የጎጥ ፖለቲካ መለያ የሆነው “ሁሉ ኬኛ” የሚባለው አባዜ አማራውንም ይዋሃደውና የቱ የአማራ የቱ የኦሮሞ ግዛት እንደሆነ የመነጋገሪያ ፋታ የለም! ያኔ መናጋገሪያው ጡጫ ይሆናል፡፡አንዴ ወደ ቁልቁለት ከተወረደ ደግሞ ጡጫ የማይጨብጥ እጅ ያለው የለም፤በአንድ እጅ አስር ጡጫ የሚጨብጥ ባለ ዘጠኝ ሱሪም የለም!

Saturday, January 25, 2020

የአማራ ክልል ፈተናዎች እና “ጭምት” አመራሩ – ክፍል ሁለት (በመስከረም አበራ)



በሃገራችን ሩብ ምዕተ-ዓመት ያስቆጠረውን የህወሃት የበላይነት ያስወገደውን ለውጥ ተከትሎ የአማራ ክልል አዳዲስ ፈተናዎች እንደተጋረጡበት ባለፈው ሳምንት ባስነበብኩት ፅሁፍ ለመዳሰስ ሞክሬያለሁ፡፡እነዚህ ፈተናዎች በህወሃት የበላይነት ዘመን ለአማራ ህዝብ ላይ ተጋርጠው በነበሩት ፈተናዎች ላይ የተደረቡ መሆናቸው ፈተናውን ድርብርብ እና ውስብስብ ያደርገዋል፡፡የመጣው ለውጥ የአማራን ህዝብ የቆዩ ፈተናዎች በማቃለል ረገድ ያመጣው ተጨባጭ ነገር አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም፡፡በአማራ ህዝብ ላይ የተቃጣው ጥቃት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተወረወረው ፋላፃ አካል ነው፡፡በአማራ ክልል ላይ የፈተና ዶፍ የሚያወርዱ አካላት ኢትዮጵያን እና አፈጣጠሯን የማይወዱ የፖለቲካ ሃይሎች ናቸው፡፡ይህን የደደረ ፈተና ለማቃለል ደግሞ የፈተናውን  ክብደት የሚመጥን ንቁ፣ቆራጥ፣ጥንቁቅ እና የተሰጠ አመራር ያስፈልጋል፡፡ሆኖም አማራ ክልልን የሚመሩ አመራሮች ወቅቱ የሚጠይቀውን የአመራር አቋም ይዘው ስለመገኘታቸው አፍ ሞልቶ የሚያስወራ ምልክት ያለ አይመስልም፡፡
የአማራ ክልል አስተዳዳሪዎች በህዝባቸው ልብ የሚጣልባቸው እንዳይሆኑ ያደረገ በርካታ ምክንያት አለ፡፡ የመጀመሪያው የጥራዝ ነጠቁ የተማሪዎች እንቅስቃሴ ትግል የአማራን ህዝብ በጨቋኝት የፈረጀበት ደመ-ነፍሳዊ አካሄድ የወለደው አማራውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ መርገም ሁሉ ምንጭ አድርጎ የማየቱ ትንተና ያመጣው ነገር ነው፡፡ ይህ አማራውን ጨቋኝ አድርጎ የማየቱ ነገር ህወሃት የተባለው የባሰበት ጥራዝ ነጠቅ ደደቢት ከመሸገበት፣ አዲስ አበባ እስከ ገባበት፣ ከዛም ፈላጭ ቆራጭ ሆኖ ግማሽ ምዕተ አመት ስልጣን ላይ በተወዘተበት ዘመን ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ህወሃት ጌታ ሆኖ ኢትዮጵያን ሲያሾር በኖረበት ዘመን ካሰማራቸው ሶስት የእህት አምስት የአጋር ድርጅት ሎሌዎች መሃል አንዱ የአማራ ክልልን የሚያስተዳደርው ብአዴን ነበር፡፡
ሁሉም የአባል/አጋር ፓርቲ ሎሌዎች በአሳዛኝ ራስን የማከራየት ጎስቋላ ህይወት ውስጥ የነበሩ ቢሆኑም የብአዴንን ለየት የሚያደርገው በራሱ ህዝብ ላይ የተቃጣውን ጦርነት ሊያጋፍር የወጣ ሎሌ መሆኑ ነው፡፡ይህ ቡድን ከሎሌነቱ የባሰ ሌላ ፈተና ነበረበት፡፡ ይኽውም “እንደ ወጣበት ህዝብ ትምክህተኛ አለመሆኑን” ለጌታ ህወሃት የማስመስከር የማያልቅ ስራ ነበር፡፡ይህን ለማስመከር ደግሞ ህወሃት በአማራ ህዝብ ላይ የሚያወርደውን ሁለንተናዊ መከራ ዝቅ ሲል ባላየ ማለፍ ከፍ ሲል ደግሞ ከህወሃት ጋር ተደርቦ የራስን ህዝብ ልብስ አስወልቆ በእሾህ ለበቅ መለብለብ ያስፈልግ ነበር፡፡ይህን በማድረግ የብዴን ሹማንነት “አማራ በመሆናቸው ምክንያት ከዘር የወረሱትን  የትምክህተኝነት ሃጢያት” የማራገፋቸውን ለጌታ ህወሃት ያስመሰክሩ ነበር፡፡ይህ ከሩብ ምዕተ-ዓመት በላይ ከብአዴን ሹማምንት ጋር አብሮ የኖረ አባዜ እንዲህ  በቀላሉ ትቷቸው ሊሄድ አይችልምና ዛሬም ለህዝባቸው ለመቆም ወገባቸውን ሳይዘው አልቀረም፡፡
ይህ ድክመት ከብአዴን ሹማንምንት ያለፈ ታሪክ ብቻ የሚቀዳ አይደለም፡፡ይልቅስ ከላይ ከፍ ብሎ እንደተቀመጠው ከነጥቆ በረሩ የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ንፋስ ውስጥ አማራውን ጨቋኝ አድርጎ የመሳሉ ነገር ዛሬ ድረስ ተሻግሮ ክልሉን የሚመሩ ባለስልጣናት ለህዝባቸው እንዳይሰሩ ቀላል የማይባል ተፅዕኖ ሳያስከትል አልቀረም፡፡ይህም ማለት የአማራ ክልልን የሚመሩ ባለስልጣናት ለህዝባቸው የመቆርቆር ነገር ካሳዩ “የቆየ ትምክህታቸውን ሊመልሱ፣የቀድሞውን ስርዓት ሊያመጡ” የሚል ዜማ ይከተላቸዋል፡፡ ይህ ነገር የአማራ ክልል አመራሮች ከሌላው በተለየ “ጭምት” እንዲሆኑ ሳያደርግ አልቀረም፡፡ይህን ነገር ለመስበር ደግሞ የክልሉ አመራሮች በህወሃት ዘመን በከፍተኛ የስነልቦና ስልበት ውስጥ የቆዩ በመሆናቸው ዛሬ ብድግ ብለው በራሱ የሚተማመን፣የሚቆምለት መርህ ያለው፣የፖለቲካ ተደራዳሪነትን ካርዶችን አሰላስሎ ሰብስቦ አጀንዳ አስቀማጭ ሊሆኑ አይችሉም-በጥብቅ ሰንሰለት ታስሮ የኖረ ምርኮኛ ሰንሰለቱ ቢፈታለትም ቶሎ እጁን ማዘዝ እንደማይችል ሁሉ!
ይህ ልማድ ግን ለአማራ ህዝብ ደህንነትም ሆነ ለኢትዮጵያ ህልውና ሲባል ነገ ዛሬ ሳይባል መወገድ ያለበት ልማድ ነው፡፡አማራ ክልልን የሚመሩ መሪዎች “ጭምትነታቸውን” ማቆም አለባቸው፡፡በክልሉ ላይ የተደቀነው ፈተና በትናንቱ የፖለቲካ ልማድ የሚወጡት አይደለም፤ለአፍታም የሚያስተኛ አይደለምና ወገብ ጠበቅ አድርጎ መስራት ያስፈልጋል፡፡ እዚህ ላይ “የሚሰራው ስራ ምንድን ነው?” የሚል ተገቢ ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፡፡የሚሰራው በርካታ ስራ ቢሆንም እኔ የታየኝን ላስቀምጥ፡፡
ነቀፌታን ማስወገድ
ለውጥ መጣ ከተባለ ወዲህ በተለይ ወያኔ እንኳን ወደመረሻው አካባቢ ረስቶት የነበረውን የአማራን ህዝብ የማብጠልጠል ነገር በተለይ በኦሮሞ ፖለቲከኞች ዘንድ በግልፅ በአደባባይ እየተቀነቀነ ይገኛል፡፡ይህ የአማራን ህዝብ የማብጠልጠያው መግቢያ በር “ነፍጠኛ” የሚለው አማራው ሊያፍርበት የማይችለው፣ይልቅስ የሚኮራበት ስም ነው፡፡ሆኖም ዋናው ጉዳይ ያለው አማራው “ነፍጠኛ” ለሚለው ስም  የሚሰጠው ትርጉም ላይ አይደለም፡፡ዋናው ጉዳይ ያለው ሌሎች ለዚህ ስም የሚሰጡት ትርጉም ላይ ነው፡፡ የመከፋፈል ካህኑ መለስ ዜናዊ “ነፍጠኛ” የሚለውን ቃል አማራው ከሚያውቀው በተለየ ሁኔታ ለካድሬዎቹ ሲያሰለጥን ኖሯል፡፡አማራውን ከኢትዮጵያ እኩል የሚጠሉ አክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞችም ሆኑ የሌላ ዘውግ ፖለቲከኞች “ነፍጠኛ” ለሚለው ስም ያላቸው ትርጓሜ ከመለስ ዜናዊ ጥራዝ ነጠቅ ካድሬዎች የተለየ አይደለም፡፡
በነዚህ አካላት ትርጉም “ነፍጠኛ” ማለት ቅኝ ገዥ፣የሰው ባህል ጨፍላቂ፣የሰው መሬት ቀማኛ፣በኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ላይ የዘር ማጥፋት ያደረገ ጨካኝ ማለት ነው፡፡በዚህ እሳቤ መሰረት አሁን በህይወት ያሉ፣ የዚህ ነፍጠኛ የተባለው “ጭራቅ” ልጆች ደግሞ አሁን ላይ የአባቶቻቸውን ሃጢያት ደሞዝ ማግኘት አለባቸው የሚል የማይናወጥ አቋም አለ፡፡ይህ እሳቤ ነው በኢትዮጵያ ዳርቻ ላሉ አማሮች በህይወት የመኖር ስጋት፣ይህ እሳቤ ነው አማራ ክልልን በየአጋጣሚው የማሳቀል ምክንያት፣ይህ እይታ ነው ጊዜ እና ቦታ ሳያስመርጥ ከባስልጣን እስከ መደዴ የፖለቲካ ንግግር ማሳመሪያው አማራን ማንጓጠጥ አድርጎ እንዲታሰብ ያደረገው፡፡ችግሩ አማራውን በማንጓጠጥ የሚቆም ቢሆን ኖሮ በአመዛኙ  የአማራ ህዝብ ካለው ጠንካራ የስነልቦና ውቅር አንፃር አሳሳቢ አይሆንም ነበር፡፡ ዋናው ችግር ይህ እሳቤ ወደ ተግባር ተቀይሮ እጅ እና እግር፣ጥፍር እና ጥርስ አውጥቶ አማራውን እና የአማራ የተባለን ነገር ሁሉ ሊውጥ መንደርደሩ ነው፡፡ይህ አደጋ በቀጥተኛ ቋንቋ ሲገለፅ ከክልሉ ውጭ የሚኖረው አማራ በተለይ በከፍተኛ የእልቂት ስጋት ውስጥ መገኘቱ ነው፡፡
ይህን ችግር ለማቃለል ክልሉን ከሚመሩት መኳንንት የቀረበ ሰው የለም፡፡ችግሩን ለማቃለል በክልሉ ሹማንት ሊደረግ የሚገባው ቀዳሚው ነገር ከክልሉ ውጭ ለሚኖረው አማራ ሃላፊነት ያለባቸው መሆኑን መረዳት ነው፡፡ይህን ከተረዱ በኋላ በመጀመሪያ ከእራሳቸው ፓርቲ ጓዶች የሚመጣውን እልቂት የሚጠራ የአደባባይ ንግግር በአንክሮ ተመልክቶ በጠንካራ ወገብ መፋለም ነው፡፡ይህ ማለት አንድ ሁለት ቀን ተደርጎ የሚረሳ የሁለት ካድሬዎች የፌስ ቡክ ንትርክ ማለት አይደለም፡፡ከዛ ያለፈ ነገር ያስፈልጋል፡፡ባለቤት ካልናቁ አጥር አይነቀነቅምና “በአንድ ፓርቲ ጥላስር ያለ አጋር ተዝናንትቶ በአደባባይ የምመራውን ህዝብ የሚወርፈው እኔን እንዴት ቢያየኝ ነው?” ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል፤በግማሽ አይን መታየት ጥሩ ነገር አለመሆኑን ለራስ መንገር ያስፈልጋል፣መከባበር የሌለበት የሽንፈት ህብረት ወንዝ እንደማያሸግር አምኖ ለዚሁ መስራት ያስፈልጋል፡፡ ይህን ገቢራዊ ለማድረግ በፓርቲ ስብሰባዎች፣በፖለቲካዊ ግንኙነቶች ወቅት አጥንት ለብሶ መቆምን ይጠይቃል፡፡
የቤትን እርግጫ አደብ ካስያዙ በኋላ የሚቀጥለው ከወጭ የሚመጣውን ውረፋ መቋቋም ነው፡፡ከውጭ የሚመጣው ውረፋ ከዘውግ ብሄርተኞች የሚሰነዘር የአማራውን ህዝብ ህይወት እጅግ ለከፋ አደጋ የሚያጋልጥ፣የማምለክ መብቱን የሚጥስ በአጠቃላይ አማራነትን የሞት ምልክት የሚያደርግ እጅግ አደገኛ ነገር እየሆነ መጥቷል፡፡ይህን ነገር ዝም ብሎ ማየት የአማራ ህዝብ ፍትህን ከእጁ እንዲያገኝ መገፋፋት፣ሃገራችንንም ወደ አላስፈላጊ ትርምስ መክተት ነው፡፡ቤኒሻንጉል ላይ የአማራ ህፃናት ሳይቀሩ በቀስት ሲሰነጠቁ ክልሉን የሚመራው አመራር ችላ በማለቱ የሆነው ነገር የሚታወቅ ነው፡፡ያን መሰል ድርጊት አሁንም እንዳይደገም መፍትሄውን ማምጣት የሚችለው መራሩ ነው፡፡መፍትሔ ማምጣት ማለት ደግሞ ህፃን ልጅን እንኳን የማያሳምን “እየተከታተልን ነው፣ጎጅ ባህል ስለሆነ ነው፣እልባት ለመስጠት አቅጣጫ ተቀምጧል” የሚል አሰልች ፕሮፖጋንዳ መደርደር አይደለም፡፡የአማራ ህዝብ በሚገደልበት ክልል ሁሉ ክልሉን የሚመሩ ባለስልጣናት ችልታ ወይ እገዛ አብሮ አለ፡፡ይህ ቅድም ከላይ የተነሳው መለስ ዜናዊ በካድሬዎቹ ውስጥ አስርጎት የሄደው ስልጠና ውጤት ነው፡፡ ስለዚህ አማራው በሚታረድበት ጥጋጥግ ያሉ አመራሮች ሁሉ ሃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው የሚጠየቁበትን መንገድ ጠንከር ብሎ መጠየቅ የአማራ መኳንንት ፋንታ ነው፡፡በየሚያስተዳድሩት ክልል  አማሮች ሲታረዱ፣ቤታቸው ሲቃጠል፣እምነት ቦታቸው ዶግ አመድ ሲሆን ዝም የሚሉ በብልፅግና ፓርቲ ስር ያሉ አመራሮች አማራ የክልልን ከሚመሩ ጓዶቻቸው ይልቅ ለነጃዋር የሚቀርብ ስነ-ልቦና ያላቸው እንደማይጠፉ ግልፅ ነው፡፡እነዚህን አመራሮች ተከታትሎ መገዳደር የአማራ መኳንንት ስራ ነው፡፡በአጠቃላይ የአማራ ህዝብ ስቃይ ነፍጠኛ የሚለውን ስም እና ተከትሎት የሚመጣውን እሳቤ ተንተርሶ የሚመጣ ነውና ይህን የነቀፌታ እሳቤ በአደባባይ ማፀባረቅ ቀለል ተብሎ የሚነገር መሆኑን ማስቆም ግድ ነው፡፡ሌሎች ብሄረሰቦች ሊባሉ የማይፈልጉትን ስም ማስወገድ የቻሉት ወከልናችሁ የሚሏቸው ልጆቻቸው ተግተው ስለሰሩ ነው፡፡ “ለሌሎች ህዝቦች የሚደረገው ጥንቃቄ ለእኔ ህዝብ የማይደረገው እኔ ምን ቢጎድለኝ ነው?” ብሎ ማሰብ ከባድ ነገር አይደለም!
ራስን በትክክል መግለፅ
የዘውግ ፖለቲከኞች የአማራን ክልልን በውስጡ ያሉ ብሄረሰቦችን መብት ካለማክበር እስከ ዘር ማጥፋት ወንጀል መፈፀም ድረስ በደረሰ የበሬ ወለደ ክስ እንደሚያብጠለጥሉ የሚታወቅ ነው፡፡ የክልሉ መንግስት ለዚህ ዘመቻ ምንም የሚመልሰው ነገር ስለሌለ የሃሰት ክሱ የብቸኛ እውነትነትን ማማ ተቆናጦ ቁጭ ብሏል፡፡ ዛሬ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያውቀው የቅማንት ህዝብ በህገመግስቱ በተደነገገው መሰረት  ብሄረሰብ የሚያስብለው የተለየ ቋንቋ ሳይናገር፣ አማርኛ እየተናገረ የልዩ ብሄረሰብ አስተዳደር የተሰጠው ብቸኛ ህዝብ መሆኑን ሳይሆን ጥያቄው ታፍኖ በአማራ ልዩ ሃይል የዘር ማጥፋት እየተደረገበት እንደሆነ ነው፡፡ይህን የሚያራግበውን ሚዲያ በህግ ተጠያቂ ማድረግ ቀርቶ የተለያዩ ሚዲያዎችን ተጠቅሞ የአማራ ክልል ለቅማነት ህዝብ ያደረገውን እላፊ መብት የማክበር ፈለግ የማስተዋወቅ ስራ እንኳን መስራት አልተቻለም፡፡ ስለዚህ ሃሰቱ እውነት አክሎ በአማራ ህዝብ ጠላቶች የፕሮፖጋንዳ ከበሮ ይመታበታል፡፡
የአማራ ክልል የሚብጠለጠልበትን የብሄረሰቦች መብት የመደፍጠጥ የሃሰት ወሬ ውድቅ የሚያደርገው የቅማንት ጥያቄ ጉዳይ ብቻ አይደለም፡፡ ለኦሮሞ፣ለአገው ህዝቦች የተሰጠው የራስን በራስ የማስተዳደር መብትም ሌላው ምስክር ነው፡፡ የአማራ ክልልን በብሄረሰቦች መብት ጨፍላቂነት የሚከሱ ሰዎች የእኛ በሚሉት ክልል በአማራው፣በጋሞው፣በጉራጌው ወላይታው፣ጌዲኦው ላይ  በአደባባይ በማይክራፎን ግልፅ የዘር ማጥፋት አዋጅ የሚታወጅበት ነው፡፡ይህን ጠቅሶ ታገሱ የሚል እውነታውን የሚያሳይ ያልተጋነነ፣ፕሮፖጋንዳ ያልሆነ፣ህዝብን ከህዝብ የማያጋጭ ግን ደግሞ እውነቱን የሚያሳይ የሚዲያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ነገር ካልተሰራ እነዚህን አካላት ከአማራው ህዝብ አናት ላይ ማውረድ አይቻልም፡፡ይህን ለማድረግ ደግሞ የአማራን ክልል የሚመሩት አመራሮች ቀዳሚ መሆን አለባቸው፡፡ በተግባር ሲታይ ግን ይህን በማድረጉ ረገድ አንድ የፌስቡክ ገፅ ያለው ግለሰብ የተሻለ እንቅስቃሴ እያደረገ ይመስላል፡፡ ይህ የግለሰቦች የማህበራዊ ደረ-ገፅ እንቅስቃሴ ደግሞ ደምፍላት ያለው፣ሙሉ እውነታውን ሊያቀርብም የማይችል፣ጭራሽ ግጭቱን የሚያካርር በመሆኑ ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚበልጥ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ የክልሉ መንግስት ነገ ዛሬ ሳይል የክልሉን ተጨባጭ እውነታ ለኢትዮጵያ ህዝብ በማቅረብ ሃሰትን ቦታ ማስለቀቅ ይጠበቅበታል፡፡
ያደረ አጀንዳን የመግለጥ ስራ
በአሁኑ ወቅት እየተጋጋለ የመጣው አክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኝነት ጎራ ከህወሃት ውድቀት ወዲህ የታየው ለውጥ በኦሮሞ ልጆች ትግል የመጣ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ስለሆነም ህወሃት ያደርግ እንደነበረው የትግል ጀብዷቸውን እየተረኩ የህወሃት የበላይነትን በኦሮሞ ሊሂቃን የበላይነት ለመተካት ይሻሉ፡፡ ሆኖም የኢትዮጵያ ህዝብ ንቃት ከዚህ አልፎ በመሄዱ ምኞታቸው ስጋ ሊለብስ አልቻለም፡፡ይልቅስ ኦሮሞ ብቻ ታግሎ እንዳመጣው የሚያምኑት ለውጥ የዘረጋው ፖለቲካዊ ዘይቤ እያሳካ ያለው  ነፍጠኛ/አሃዳዊ እያሉ በተለያየ ስም የሚጠሩትን የአማራን ህዝብ ፖለቲካዊ እሳቤ እንደሆነ ያምናሉ፤አምነውም ይብሰለሰላሉ፡፡በአክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጎራ እሳቤ መሰረት ኢትዮጵያ የተሰራችበትን እውነት ተቀብሎ፣የሚታረመውን አርሞ፣አንድነቷ ተጠብቆ ወደ ዲሞክራሲያዊ ፖለቲካ የምትሄድበትን መንገድ መተለም የአማራ ብቻ ናፍቆት ነው፡፡ለዚህ ነው ከኦሮሞ  ህዝብ የወጣውን ጠቅላይ ሚንስትር አብይን አፄ ምኒልክን በሚጠሉበት ጥላቻ አምርረው የሚጠሉት፣በአማራ ጉዳይ አስፈፃሚነት የሚከሱት፡፡ይህን ሁሉ ያመጣው አሁን የመጣው ለውጥ የመጣው በኦሮሞ ልጆች ትግል ሆኖ ሳለ የጠቀመው ግን አማራን ነው ብሎ ከማሰብ ነው፡፡
ይህን የተንሸዋረረ እሳቤ ማስተካከል አሁንም በብልፅግና ፓርቲ ውስጥ ያሉ የአማራ መኳንንት ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት፡፡የማስተካከያ ስራው መጀመር ያለበት ደግሞ የመጣው ለውጥ አክራሪ ብሄርተኞች እንደሚያስቡት ለአማራው የተለየ ያመጣው ነገር እንደሌለ ነው፤ይልቅስ የአማራህዝብ ሃገሩ በለውጥ ምጥ እንዳትሞት ፣ለውጡ እስኪረጋ ድረስ ጊዜ በመስጠት፣ከሁሉ በላይ ኢትዮጵያን በማስቀደሙ ብቻ በይደር ያስቀመጣቸው በርካታ አጀንዳዎች እንዳሉት ማሳወቅ ነው፡፡በይደር የተቀመጡ አጀንዳዎችን ወደማሳቱ ከማለፌ በፊት ግን ሌላ አበይት ነጥብ ማንሳት ያስፈልጋል፡፡ይኽውም ጠ/ሚ አብይን ወደ ስልጣን ያመጣው ለውጥ ሲረገዝም ሆነ ሲወለድ አማራው በአቶ ደመቀ መኮንን በኩል ከማንም በላይ ለስልጣን ቅርብ ሆኖ ሳለ ለስልጣን ልሙት ሳይል ሃገር የሚያረጋጋው መንገድ ስልጣን መያዙ ስላልመሰለው ስልጣኑ ወደ ኦሮሞ ተወላጁ ዶ/ር አብይ እንዲዞር አድርጓል፡፡ እዚህ ውስጥ ብዙ ትርጉም አለ!
ይህን ትርጉም ለማወቅ የሃገር አጀንዳ ከዘውግ አጀንዳ ዘለግ እንደሚል መረዳትን ይጠይቃል፡፡ ይህን ያደረገ ሰው ናፍቆቱ ገዘፍ ያለው ሃገር የማዳን ተግባር እንጅ የመንደር ልፊያ እንዳልሆነ የሚገባው የሃገርን ትርጉም የሚያውቅ ብቻ ነው፡፡ጠ/ሚ አብይ ከገዛ የዘውጉ ሰዎች ሰባት ጦር የሚወረወርበት ይህ የገባው ሰው ስለሆነ ነው፡፡ጠ/ሚው የሚጠበቅበትን ያህል ሃገር የማረጋጋት ስራ እንዳይሰራ እግር ተወርች የታሰረውም በዚሁ እሳቤ ተሸካሚ የዘውጉም፣የፓርቲውም መካከለኛ እና ዝቅተኛ  ሹመኞች፣የህግ /የፀጥታ አካላት ህቡዕ ስራ ነው፡፡
ስልጣን ላይ ልሙት ሳይል ስልጣን አሳልፎ የሰጠው የአማራው ናፍቆት ሃገር ማዳን ነበር፡፡ የዚህ ስራ ትክክለኛ ትርጉም የሚገባው ግን ለሃገር ግድ የሚለው ብቻ ስለሆነ ክልል እና ሃገር የተሳከረባቸው ሰዎች የሰጡት ትርጉም ሌላ ሆነ፡፡ ስልጣንን አሳልፎ መስጠት ማጉድል መሆኑ ቀርቶ ማትረፍ ተደርጎ ተተረጎመ፡፡በታሪክ ለኢትዮጵያ ሲሞቱ የነበሩ ኦሮሞ አርበኞችን ለአማራ ንጉስ ብለው ነው ወደ ጦርሜዳ ሄደው ቀኝ ገዥን የተፋለሙት ሲሉ የኖሩት የኦሮሞ ብሄርተኞች አሁን የሃገሪቱን የመጨረሻ ስልጣን የያዘው ኦሮሞው አብይ ሲሆንም ኢትዮጵያን የሚለው በስሩ ላሉ አማሮች ተገዝቶ እንደሆነ ሲናገሩ አያፍሩም፡፡ስለዚህ የአማራ መኳንንት በመጣው ለውጥ ሃገር ያሰነበቱ መስሏቸው ሳይከራከሩ ስልጣን አሳልፈው እንደሰጡ፣በዚህም መላው አማራ ከማንም በላይ ደስ እንዳለው ማሳሰብ ሳይስፈልጋቸው አልቀረም፡፡ለዚህ ለውጥ መምጣት የብአዴን ባለስለጣናት ከህወሃት ጋር ያደረጉትን ትንቅንቅ መግለፅ ቢቻልም በአክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞች ዘንድ እየበዛ የመጣውን የብቸኛ ጀግንነት አጉል ቀንድ ሊሞርደው ይችላል፡፡
ከዚህ ቀጥሎ የሚመጣው የአማራ ፖለቲከኞችም ሆነ ህዝቡ ኢትዮጵያ ከለውጥ ነውጥ እስክትድን በእናት ሃገራቸው ህመም ላይ ሌላ ራስ ምታት ላለመጨመር ሲሉ ያሳደሯቸው አጀንዳዎች እንዳሉ ማሳወቅ ነው፡፡ይህን ማድረጉ ለውጡ ለአማራ የተለየ ቱርፋ ያመጣ ለሚመስላቸው አካላት እንዲረጋጉ በማድረግ በኩል ጥቅም ይኖረዋል፡፡ከነዚህ አጀንዳዎች አንዱ ወልቃይትን ጨምሮ ሌሎች ከጎንደር ግዛት ላይ በህወሃት ተዘርፈው የተወሰዱ ለም መሬቶች፣እነዚህን ለም መሬቶች ለመወሰድ ሲል ህወሃት በአማራ ህዝብ ላየ የፈፀማቸው ዘር ማጥፋቶች፣ሰው ሰራሽ የዲሞግራፊ ለውጦች፣የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ጉዳይ ነው፡፡ሌላው ቀርቶ ከዚሀ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከጎንደር ግዛቶች እየታፈኑ ተወስደው ትግራይ እስርቤት ስለታሰሩ እስረኞች ቢነሳ ብዙ ጉድ አለ!
እንደሚታወቀው በደቡብ ክልል ያለው የሲዳማ ዞን ልሂቃን  ወደ ክልል ለማደግ የሚያደርጉትን ትግል አጧጡፈው ያነሱት ህወሃትን ባስወገደው ለውጥ ማግስት ነው፡፡ ይህን ትግል ሲያደርጉ ዛሬውኑ ጥያቄያችን ይመለስ የሚል ፋታ የሌለው ትግል አድርገው፣በርካታ ነዋይ ፈሰስ ተደርጎ ሪፈረንደም አስደርገው ጥያቄያቸው አንድም ሳይሸረፍ መቶ በመቶ መልስ አግኝቷል፡፡ የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄም በአማራ ህዝብ ዘንድ ከዚህ ያነሰ አንገብጋቢነት ያለው ነገር አይደለም፡፡ነገር ግን ከህወሃት ጋር ጠመንጃ እስከመማዘዝ ደርሶ የነበረው የወልቃይትማንነት ኮሚቴ ለውጡን ተከትሎ የመረጋጋት ዝንባሌ አሳይቷል፡፡ ይህ የሆነው የምንወዳት ሃገራችን ባለባት ህመም ላይ ሌላ ህመም ጨምሮ ሞቷን ላለማፋጠን ሲባል እንጅ አማራው በወልቃይት ጉዳይ ላይ የደረሰበት መከራ ቀላል ሆኖ ወይም ለወጡ ጥያቄውን መልሶለት አይደለም፡፡
ሌላው አጀንዳ በአማራው ህዝብ ቁጥር ላይ ያለው ጥያቄ ነው፡፡እንደሚታወቀው ህወሃት አማራውን ለማሳነስ ካለው አምሮት የተነሳ 2.8 ሚሊዮን አማራ የገባበት ጠፋ ሲል በአደባባ ተናግሯል፡፡ይህ የቁጥር መቀነስ ስትራቴጅ አማራው በፓርላማ ያለውን ወንበር ለማሳነስ፣ለክልሉ የሚመደበውን በጀት ለመቁረጥ፣የህዝቡን የፖለቲካ ተደራዳሪነት ግዝፈት ለመቀነስ የተደረገ የህወሃት የዝቅተኝት ስነልቦና የወለደው አካሄድ ነው፡፡ይህ የህዝብ ቁጥር ጉድለት አማራው ሁሉ ይሁን ብሎ የተቀበለው ጉዳይ አይደለም፡፡ ይልቅስ ሃገርን በማስቀደም የተተወ ነገር እንጅ! ሐገርን ባያስቀድም ኖሮ ይህ ሁሉ ህዝብ የገባበት ጠፋ የተባለው የአማራ ህዝብ የህዝብ ቆጠራ ተደርጎ ሎች እንደሚሉት “በቁመናየ ልክ ወንበር ካልተደለደለልኝ ምርጫ ውስጥ አልገባም” በማለት ሃገር የማመሱን ረብሻ መቀላቀል ይችል ነበር፡፡ህዝብ ቆጠራው ቢቀር እንኳን ጠፋ የተባለው ህዝብ ተደምሮ አሁን ባለኝ ህዝብ ቁጥር ላይ ይደመርልኝ ማለት ይቻላል፡፡ግን አልተደረገም፤አልተደረገም ማለት ግን ጥያቄ የለም፤እንደሚታሰበውም ለውጡ ለአማራዊ ፍላጎት የቆመ ስለሆነ አማራው ደስ ብሎት ዝም አለ ማለት አይደለም፡፡ይልቅስ አማራው ኢትዮጵያን የሚለው ከጉድለቱ ጋር ጭምር በመሆኑ ነው፡፡ይህን አስረግጦ ማስረዳት ደግሞ የአማራ መኳንንት ስራ ነው፡፡ ካልሆነ ሃገር ባልሆነ ተረክ ስትታመስ መክረሟ ነው፡፡
እያዚም ቤት እሳት እንዳለ ማሳሰብ
የአማራን ክልል በእጅ አዙር እያመሰ ያለው የቅማንትን ጥያቄ ተገን አድርጎ ከዘውግ ፖለቲከኞች የሚነሳው ተግዳሮት ነው፡፡ የዚህ ተግዳሮት ፊት አውራሪ ህወሃት ስትሆን ቀጣዩ ደግሞ ህወሃት የእስትራቴጅክ አጋሩ እንደሆነ በአደባባይ የመሰከረው የጃዋር ካምፕ ነው፡፡በተለይ ህወሃት የቅማንትን ጉዳይ ያለ ይሉኝታ የገባበት ከመሆኑ ብዛት የቅማንት ኮሚቴ እያለ ለሚጠራቸው ስብስቦች መቀሌ ቢሮ እስከመስጠት ደርሷል፡፡ በዚሁ ኮሚቴ ስም ታጣቂ እያስገባ የአማራ ክልልን የሚያምሰው ነገርም የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ህወሃት ይህን የሚያደርገው የቅማንት ህዝብ የትግሬ ማንነት አለኝ ባላለበት ሁኔታ ነው፡፡በአንፃሩ የትግራይ ክልል አማራ ነኝ የሚሉ የወልቃይት ህዝቦች እና ወደ አማራ ክልል መካለል እንፈልጋለን የሚሉ የራያ ህዝቦች  ያሉበትን መሬት በጉልበት ዘርፎ ወስዶ፣ሰዎቹን መብታቸውን ረግቶ በግዞት እያኖረ ነው፡፡
ይህን ህወሃት መራሹ የትግራይ ክልል አስተዳደር የሚያደርገውን ግፍ ለመታገል የወጡ የወልቃይት ማንነት እና የራያ ማንነት ኮሚቴዎች ግን ወደ ግዛቱ እንካለል ከሚሉለት የአማራ ክልል አስተዳደር ይህ ነው የሚባል እርዳታ አግኝተው አያውቁም፡፡የትግራይ ክልል አስተዳደር ምንም በማይመለከተው የቅማንት ማንነት ኮሚቴ ውስጥ ይህን ያህል የወሳኝነት ሚና ሲወስድ የአማራ ክልል አማራ ነኝ ለሚሉ ግን ደግሞ በህወሃት ከባድ ቀንበር ስር ላሉ ህዝቦች ይህ ነው የሚባል እርዳታ ያለማድረጉ የመፋዘዙ እንጅ የብልህነቱ ምልክት ሆኖ አይታየኝም፡፡በርግጥ ህወሃት በአማራ ክልል ላይ እንደሚያደርገው የአማራ ክልል ሹማምንትም ወደ ትግራይ ክልል ታጣቂ እያሰረጉ ማተራመስ ልክ መንገድ አይደለም፡፡ከዚህ በመለስ ግን አማራ ነን በማለታቸው አበሳ ለሚያዩ ህዝቦች ድጋፍ ማሳየት ተገቢ ነገር ነው፡፡ይህ ዋናው ነገር ሆኖ እግረ መንገዱን ለህወሃትም እዚያም ቤት እሳት አለ የሚል መልዕክት መስጠቱ አይቀርም፡፡ ይህ ደግሞ የትግራይ ክልል አስተዳደር የራሱ መታወቂያ የሆነውን የህዝቦች መብት መደፍጠጥ ወደ አማራ ክልል የማላከክ ፕሮፖጋንዳውንም ሆነ ወደ አማራ ክልል የሚልከውን ፈተና ለመቀነስ ይረዳል፡፡