Thursday, August 16, 2018

ለማ መገርሳ እና ፖል ካጋሜ በጨረፍታ (ዶ/ር በቃሉ አጥናፉ ታዬ)



Lemma Megersa
ሩዋንዳ በምሰራቅ አፍሪካ የምትገኝ ትንሽ አገር ስትሆን በ1994 እንደ አ.አ ከደረሰበት የሁቱና ቱትስ  እልቂት አገግማ ዛሬ ሰላማዊ አገር ሆናለች፡፡ የሩዋንዳ የዘር ፍጅት የሰው ልጅ አረሚያዊ ማነቱን ያሳየበት አንዱ የታሪክ ክስተት ነበር፡፡ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች  ሁቱና ቱትስ በዘውግ ተቧድነው አንድ ሚሊዮን ገደማ የሚደርሱ ዜጎቻቸውን ያጡበት ክስተት ዋናው ምክንያት የዘርን ጥላቻ በሚሰብኩ የፖለቲካ ሊህቃን ምክንያት ነው፡፡
በሩዋንዳ በ1994 ከተፈጸመው የዘር ፍጅት በፊት የሩዋዳ ዜጎች በቋንቋ አንድ ቢሆኑም በብሔር ተከፋፍለው  በዘውግ መታወቂያ ደብተር ላይ ቱትሲ፣ ሁቱ እና ትዋ በሚል የዘር መታወቂያ ካርዶች ልዩነታቸው ገዝፎ ነበር፡፡ ጭካኔ በተሞላበት የዘር ፍጅት መታወቂያቸው ላይ የተጻፈው የብሔር ማንነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡ ከዘር ፍጅቱ በኋላ የፖል ካጋሜ ስልጣን መያዝ ተከትሎ የብሔርና እና የኃይማኖት ማነትን የሚገልጽ ስያሜ በመታወቂያቸው ላይ እንደዳይሰፍር ተደረገ፡፡ ዛሬ በሩዋዳ ውስጥ ቱቲስ እና ሁቱ የሚል መከፋፈል እንደነውር የሚቆጠር ሆኗል፡፡ ዜጎች በችሎታቸው ብቻ የሚለኩበት ስርዓት በመፈጠሩ ፖል ካጋሜ ሀገሪቱን እያዘመናት ይገኛል፡፡
ከሩዋንዳ የዘር ፍጅት ትምህርት የቀሰሙት እንደ ታንዛንያ ያሉ ሀገራት በዜጎቻቸው መታወቂያ ላይ ምንም ዓይነት የኃይማኖትና የብሔረ ማንነትና የሚገልጽ ቃላት እንደይኖሩ በማድረግ ከ120 በላይ ያሉ ብሔሮች በሰላም ለማስተዳደር ችለዋል፡፡
የህወኃት ወራሹ ስርዓት በ1983 ስልጣን ከጋዛ በኋላ የብሔር ጥላቻን የሚፈጥሩ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ፣ በብሔር ስም ህዝቡን በመከፋፈል በርካታ የጎሳ ግጭት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗል፡፡ ዘረኞች መሰረተ-ቢስ በሆነ ጥላቻና በራስ ወዳድ ማነታቸው ምክንያት ህዝቡን በዘር እያቧደኑ በሚፈጠረው ግጭት የስልጣን እድሚያቸውን ለማራዘም ብዙ ጥረዋል፡፡ ይህም ይሳካላቸው ዘንድ በመታወቂያቸው ላይ የብሔር እና የኃይማኖት ማንነታቸንን በግዴታ ጭነውብን ለ27 ዓመታት ለጎሪጥ ስንተያይ፣ ስንጋጭ፣ ስንጋደል፣ ስንሰደድ ቆይተናል፡፡
ፖል ካጋሜ በሩዋንዳ ላይ ከተፈጠረው እልቂት ተምሮ ከዘር ፍጅቱ በፊት የነበረውን የብሔር ማንነት አጥፍቶ አንድነት የሰፈነባት ሩዋንዳን ሲመሰረት ብልሁ፣ ወጣቱ መሪ ለማ መገርሳ ደግሞ ያንዣበበውን የብሔር ግጭት ተረድቶ የዘር ፍጅቱን በማስቀረት አገሪቱን ከዶ/ር አብይ አህመድ ጋር ሊታደጓት እየታተሩ ነው፡፡
አሁን ለሚታየው የለውጥ ሂደት ጠንሳሽ እና ፊታውራሪ የሆነው የቁርጥ ቀን ኢትዮጵያዊ  ለማ መገርሳ በአገሪቱ ያንዣበበውን አደጋ በመረዳት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ሀገሪቱን እየታደጋት ይገኛል፡፡ ለማ መገርሳ  ከወሰዳቸው በርካታ እርምጃዎች አንዱ የብሔር ማንነትን በዜጎች መታወቂያ ላይ ፍቆ በኢትዮጵያ ዜግነት መተካቱ ነው፡፡የቆራጥ መሪያችንን የለማ መገርሳን አርያን በመከተከል ለሌሎችም የክልል ርእሰ-መስተዳደር ከዜጎቻቸውን መታወቂያ ላይ ከብሔር ማንነት ይልቅ ኢትዮጵያዊነት በማስፈር በአንድነታችን ጉዞ ላይ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የህወኃት ወራሹ ስርዓት ባለሟልና ተቆርቋሪ ነን የሚሉ የሰርኣቱ አጋፋሪዎች ከጎሳ ድርጅት ይልቅ በአስተሳሰብ ልዩነትን ያማከለ የፖለቲካ ድርጅት መሰረት ላይ ማንነታቸውን እንዲገነቡ እና የጎሳ ፖለቲካ እና የብሔር ቡድነኝነት ከአንድነት ይልቅ መለያየትን፣ ከመተማመነን ይልቅ መጠራጠርን ከሰላም ይልቅ ግጭትን፣ ከፍቅረ ይልቅ ጸብን የሚያራግብ እንደሆነ ከበቂው የታሪክ መዛግብት ትምህርት ቢቀስሙ መልካም ነው ፡፡

ኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ጥቅም ለአሁኗና ለወደፊቷ ኢትዮጵያ



ከፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም. 
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ 
“ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን” ብለው አንድነታችንን የሚያጠናክር ንግግር ሲናገሩ የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ጥቅም በሚገባ እንደ ገለጹት ተረድተናል። ቀጥለውም ኢትዮጵያን ከኢትዮጵያ መውሰድ ይቻላል! ነገር ግን ከኢትዮጵያዊ ልብ ኢትዮጵያ ዘላለም አትወጣም ትኖራለች! ብለው የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ጥቅም ደግመው አጉልተውታል። ኢትዮጵያ የጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ በብዙ ጥቁር ሕዝቦች ዘንድ ኢትዮጵያ ልዩ ቦታ አላት። ኢትዮጵያውያን ብዙ ላናውቅና ላንረዳ እንችላለን እንጂ፣ ከኢትዮጵያ ከኢትዮጵያዊነት የኢትዮጵያዊኒዝም አስተሳሰብና ፍልስፍና ተወልዷል።1 ኢትዮጵያኒዝም የተፈጠረው በኃይማኖትና በፖለቲካ ከጭቆና ውስጥ የነበሩ የጥቁር ዘር ባላቸው ሰዎች ነው። አፈጣጠሩ አፍሪቃ ለአፍሪቃኖች ትገባለች የሚለውን የፓናፍሪካ ፍልስፍና አስቀድሞ በመጀመሪያ የገለፀ ነው። ሲጠነሰስ ጀምሮ መንፈሳዊነትን ከሰው ልጆች ነፃነት ጋር አጣምሮ አቀናጅቶ አስተባብሮ የተፈጠረ ፍልስፍና ነው።2 ኢትዮጵያኒዝም በስፋት የተጀመረው 1660 ዓ.ም. ጀምሮ ሲሆን ከ1776 ከአሜሪካ የነፃነት ትግል በኋላ እያየለ መጣ። አፍሪቃ/አሜሪቃኖች በአሜሪካ ነፃነት በተፈጠረው ለቀቅ ያለ ሁኔታ በመጠቀም ኢትዮጵያኒዝምን ፈጠሩ። በ1808 ዓ.ም. የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ቤ/ክ በአሜሪካ አቋቋሙ።3 በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና በዓለም ተስፋፋ። የሚገርመው ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙም የታወቀ ፍልስፍና ሆኖ አልገባም። ትልቁ ጥያቄ አሁን ኢትዮጵያኖች እንዴት ይህን ፍልስፍና ያዩታል? የሚለው ነው። ስለ ሐገሪቱ የወደፊት አቅጣጫ ይጠቅማል ብለው ይሄን ፍልስፍና መመርመርና መወያየት ቢችሉ ጥሩ ነው የሚል አስተያየት አለን። እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ቀላል የምንቆጥረው ኢትዮጵያዊነት በኢትዮጵያኒዝም መልክ በሌሎች ሕዝቦች ዘንድ ያለውን አዎንታዊ ተጽእኖ ብንረዳው የበለጠ ኢትዮጵያዊነታችንን ለማጠናከር ሊረዳንም ይችል ነበር።4 የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍናን ያስፋፉት እነማን ናቸው? ኢትዮጵያኒዝምን በመጀመሪያ ያስፋፉት በ19ኛው ክፍለ ዘመን በመንፈሳዊ ዓለም የተሰማሩት በአሜሪካና በደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ቄሶች ናቸው። በመሠረቱ ዘረኝነት በፖለቲካና በኢኮኖሚ ዓለማዊ ዙሪያ ላይ ብቻ ሳይሆን በጥቁሮች መንፈሳዊ ዓለም ላይም ከባድ ጫና ነበረው። በሃይማኖት ሳይቀር ጥቁርን እንደ ሰይጣን ነጭን እነደ መልዓክ ማየት የተለመደ የነጭ ቄሶች እምነትና ተግባር ነበር። ገጽ 2 የ8 በመሠረቱ ነፃነት የሚፈልጉ የጥቁር ቄሶች ሁለት ችግሮች ገጠሟቸው፤ የነጭ ቄሶች ሲሰብኩ ጥቁርን እንደ ሉሲፈር (ሰይጣን) ስለሚቆጥሩ የነሱ ቄስ ሆኖ ማገልገል በራሳቸው በጥቁሮች ላይ መንፈሳዊ ኩነናን እንደ መቀበል መስሎ ስለ ታያቸው መቀበል አልዋጥላቸው አለ። በሁለተኛ ደረጃ የነጭ ቄሶች ለጥቁር ቄሶች ምንም ቢሆን ያመራር ተግባር እንዳያገኙ ከለከሏቸው። ሌላው በጣም ያማረራቸው ደግሞ የነጭ ቄሶች ሲሰብኩ የጥቁር ቄሶች ቀና ብለው ወደ ላይ አምላክን ከማየት ወደ ታች አንገታቸውን ደፍተው ቁልቁል እንዲያዩ አምላክን አሻቅበው እንዳያዩ የነጭ ቄሶች እንዳገዷቸው እንደሳፈሯቸውና እንደ ጨቆኗቸው ይናገራሉ። ጭቆናው እየቀጠለ በሄደ ቁጥር ነጮች በሚቆጣጠሯቸው ቤተክርስቲያን መቀጠል እንዳንገፈገፋቸው ይናገራሉ። በአንድ በኩል ቤተክ/ያን እንዲቀይሩ ጥያቄ ያቀርባሉ፤ ካልተቀየረ ግን ሌላ ቤተክ/ ለማቋቋም አቋም ይወስዳሉ። ያቀረቡት ጥያቄ ሙሉ የመንፈሳዊ ነፃነት ማግኘት እንደ ምዕመናን ወደ እግዚአብሔርና ወደ ክርስቶስ ካላንዳች ዘረኝነትና አድልዎ የሚያገናኝ ሃይማኖትና ቤተክ/ ፈለጉ። የነጮች ቤተክ/ ይህንን ጥያቄያቸውን ሊያሟሉ አልቻሉም፤ ስለዚህ አዲስ ቤተክ/ ማቋቋም ወይም የነበረውን ቤተክ/ መቀየር ፈለጉ፤ እናም በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ስሟ የተጠቀሰው ኢትዮጵያ ስለ ሆነች የኢትዮጵያ ቤተክ/ እያሉ ማቋቋም ፈለጉ። ኢትዮጵያ የጥቁር ሐገር በመሆኗ ሌላው ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ስለሚል ያለምንም መድልዎና ዘረኝነት ወደ እግዚአብሔር እምታገናኘን ቤተክ/ ናት ብለው ኢትዮጵያኒዝምን አቋቋሙ።5 ኢትዮጵያኒዝምን ያዩት እንደ መንፈሳዊ ጎዳና ከእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር በቀጥታ መንገድ ከፋች፤ ሌላው ደግሞ ኢትዮጵያ የጥቁር ሐገር ሆና እራሷን ማስተዳደር የቻለች ታላቅና ክቡር እንዲሁም የራሳችው ሐገርና እንደ አለኝታ በመቁጠር ነበር የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና በመንፈሳዊ ትግል የጀመሩት፤ ያነፁትና የገነቡት።6 የሚገርመው የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና መንፈሳዊ መሠረት ይኑረው እንጂ ለተጨቆኑት የዓለም ሰዎች ሁሉም መመሪያ አድርገው ነው የመሠቱት። ከመንፈሳዊ መሠረቱ ወደ ዓለማዊ ጭቆናዎችን ለመቋቋም የኢትዮጵያኒዝም የሚከተሉትን ስምንት ባሕሪያት ያጠቃልላል፤ 1. መንፈሳዊ ነፃነት 2. በራስ መተማመን 3. ለራስ ክብር 4. እራስን መቻል 5. የውጭ ጭቆናን መቋቋም 6. መንፈሳዊ ነፃነት ከዓለማዊ ነፃነት ጋር ማጋራት አብሮ እንዲሔድ ማድረግ 7. የተጨቆኑ ሰዎች በጋራ መተባበር 8. ሰብአዊነት፣ መረዳዳትና እርስበርስ መተሳሰብ። እነዚህ ስምንት ታላላቅ ፅንሰ ሀሳቦች የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና የሚያራምዱና በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያኒዝምን ተከትሎ የመጣውን ፓንኣፍሪካኒዝምን ለአፍሪቃ ነፃነት አንድነት ሕድስና ስር መሠረት የሰጡ ታላቅ አስተዋጽኦ ያደረጉ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸው። የኢትዮጵያ ነፃነትም ጠቅሟል።7 ገጽ 3 የ8 እንግዲህ ኢትዮጵያኒዝም በ16ኛው ክፍለ ዘመን ተጀምሮ 18ኛው ክፍለ ዘመንን ተደግፎ እሰከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ የቆየ ፍልስፍና ነው።8 ኣሁንም ቢሆን የቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝዳንት ታቦይ ኢምቤኪ እንደሚሉት የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና አሁን ላለንበት ዘመን ያስፈልጋል ይላሉ።9 እናም የኢትዮጵያ ቤተክርስትያኖችም በደቡብ አፍሪቃ በአሜሪካና በካሪቢያን ሀገሮች አሉ፤ አሁንም ቢሆን እነዚህ ቤተክርስትያኖች ከመንፈሳዊ አገልግሎት በተጨመማሪ ያላለቀውን የነፃነት ትግል የገለፁ ናቸው። ኢትዮጵያኒዝም በዓለም መድረክ ያመጣቸው ለውጦች በደቡብ አፍሪቃ የአፍሪቃን ናሽናል ኮንግሬስ ያቋቋሙት በደቡብ አፍሪቃ የኢትዮጵያ ቤተክ/ ቄሶች ናቸው፤ እናም የመጀመሪያው የአፍሪቃ ናሽናል ኮንግሬስ ፕሬዝዳንት ጆን ላንጋቢሌሌ ዱቤ በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍናቸውና አቋማችው ታስረው ከተፈቱ በኋላ የአፍሪቃ ናሽናል ኮንግሬስ ፕሬዝዳንት ሆነዋል።10 የስማቸው ቅፅል ግልፅ ኢትዮጵያዊ ሁልጊዜ አደጋ ላይ ያሉ ይሏቸው ነበር፤ እናም ነጮቹ 1906 የኢትዮጵያኒዝምን ፕሮፖጋንዳ አንቋሽሸው ኢትዮጵያኒስትን ማሰርና አልፎ አልፎም መግደል ጀመሩ። ቀጥለውም የኢትዮጵያኒዝም እንቅስቃሴን እንደ አደጋና እንደ ረብሻ አሰራጭ ቆጥረው የወታደር ኃይላቸውን አሳደጉ። የዙሉ እንቅስቃሴ 1906 ቀጥሎም ባንባታ በሌሎችም አካባቢዎች ያፓርታይድ ተቃውሞ እንቅስቃሴ ተጀመረ። እንቅስቃሴውውንም ያስጀመሩት እንዲሁም ይመሩት የነበሩት ኢትዮጵያኒዝሞች ነበሩ። እንዲሁም በተለያዩ የአፍሪቃ ሐገሮች በእንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ፖርቱጋል፣ በቅኝ ግዛት ተገዝተው የነበሩ በኢትዮጵያኒዝም በመጠቀም ሃይማኖትን ከፖለቲካ ጋር በማገናኘት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት ተጠቅመውበታል። ራስተፈሪያኒዝንም የፈለቀው ኢትዮጵያኒዝም በሚለው ፍልስፍና ነው። አፍሪቃ ለአፍሪቃዊያን የሚለው አስተሳስብ የመጣው ኢትዮጵያኒዝም በሚለው ፍልስፍና ነው። ቅኝ ግዛትን በመቃወም እነፕሬዝዳንት ጆሞ ኬኒያታ ሳይቀሩ በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና እሰከ 1960 ዓ.ም ድረስ ተጠቅመውበታል። በተለያየ መንገድ ቢገለፅም የተለያዩ ሰዎች በተለያየ መንገድ ቢጠቀሙበትም መሠረታቸው ኢትዮጵያኒዝም እንደ ሆነና አፍሪቃን ሙሉ ከቅኝ ግዛት ለማውጣት እንደ ችቦ መብራት እነደ ተጠቀሙብት ጥርጥር የለውም። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያኒዝም የኢትዮጵያ ሚና በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ምንድነው ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። በመጀመሪያ ኢትዮጵያን የኢትዮጵያኒዝም መሠረት አድርጎ ሲፀነስ ሐገሪቷ ልዩ ቦታ እንደ ተሰጣት ምንም ጥርጥር የለውም። በመሆኑም ኢትዮጵያ መንፈሳዊ ምግብ ለዓለም የሰጠች መሆኑ ምንም የሚያሻማ ነገር የለውም። ዛሬ ቁሳቁሳዊ እርዳታ ከሚሰጡት እንደ አሜሪካ ካሉ ሀገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ መንፈሳዊ የነፃነት ምግብ ለዓለም የሰጠች ታለቅ ሐገር መሆኗ ጥርጥር የለውም። እንግዲህ ኢትዮጵያን ሊጎዷትና ሊገድሏት ያሰቡ ሐገሮች ግለሰቦች እንዲሁም ቡድኖች ማወቅ የሚገቧቸው ነገሮች ቢከሷትም በታሪኳ ቢፈርዱም ብትሞትም ዘላለም የምትኖር ሐገር ናት። ሁላችንም ቢሆን ይህችን ሀገር እንዲህ ያለ የተጨቆነውን ዓለም በሙሉ ያከበረውን መንፈሳዊ ስጦታ ያበረከተች ሐገር አሳልፈው የሰጡንን አባቶቻችንና እናቶቻችንን ማክበር እንጂ በውጭ ገጽ 4 የ8 ሐገር ፕሮፖጋንዳና በማናውቀው ሥልጣኔ ባልገባንና ባልተረዳነው ተውጠን ይህችን ሐገር መናቅ ትልቅ ስሕትተ ነው። በተጨማሪም ኢትዮጵያኒዝም የተመሠረተው በክርስትና ሃይማኖት ላይ የነጭ ቄሶች ዘረኝነትን በማስፋፋት የእግዚአብሔርን መልክ በነጭ ቅልፅ በመግለፅ ሌሎችን በማግለልና መጠቀሚያ ብቻ በማድረግ እንደማይቻል በመቃወም ነበር። የእስልምና ሃይማኖትን በኢትዮጵያኒዝም አመለካከት ስናየው ተቃውሞ በተነሳበት ጊዜና ምዕመናኑ ስደት ባጋጠማቸው ወቅት የኢትዮጵያ ድጋፍ ትልቅ ልዩነት እንዳመጣ ታሪክ ይመሰክራል።11 ኢትዮጵያ ለሙስሊሞች ያደረገችው ድጋፍ ሙሉ በሙሉ የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ይገልፃል። ከእኛ ምን ይጠበቃል? በመጀመሪያ ይህንን ታሪክና ፍልስፍና ማወቅ ይገባናል። ይህንን ታሪክና ፍልስፍናን መሰረት አድርገን ዘመናዊነትን ለመገንባት ዝግጁ መሆን ያሰፈልጋል። ከውጭ የተለያዩ ሀሳቦችን እየኮረጅን ሐገራችን የፈጠረችውን ፍልስፍና ማንቋሸሽና ታሪኳን መወንጀል አላግባብ መፍረድ አይገባም። መጠየቅ ያለብን የራሳችን ሐገር ምን ፈጠረች፣ ለምን በዓለም ዙሪያ ያሉ ሐገሮች እንደዚህ ተማሩባት አከበሯት ብለን በትሕትና ሐገራችንን አክብረን ያለባትን የተወሳሰቡ ችግሮችን አጥንተን ተወያይተን ተባብረን አንድ መንገድ ፈጥረን በሐገሪቷ ባህል መሰረት ካላንዳች ኩረጃ ታላቋን ኢትዮጵያ መፍጠር እንችላለን። መደምደሚያ ሃሳብ የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ለአዲስ ብሔራዊ ውይይት አሁን አዲስ የብሔራዊ ውይይት ኢትዮጵያ ያስፈልጋታል። ስለ ሐገራችን ነባራዊ ሁኔታ በሰለጠነ አስተሳሰብ መወያየትና ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል። ለውጥ መጣ በተባለበት ዘመን ማለትም ባለፉት ዓርባ አመታት ሁሉን አቀፍ የሆነ ብሔራዊ የውይይት መድረክ ነበር ማለት ያስቸግራል። ከእንግዲህ ወዲህ ግን ይህ የብሔራዊ ውይይት መድረክ መፈጠር አለበት። ኢትዮጵያ የት ነው ያለችው፣ ወደ የት ነው ምትሔደው? ያለችበት ጎዳና ትክክል ነው ወይስ አይደለም በሚሉ ሀሳቦች ላይ በጋራ በመወያየት ስምምነት ላይ በመድረስ በኢትዮጵያኒዝም በመጠቀም አሁን ሐገራችን ካለችበት ውስብስብ ችግር መውጣት እንችላለን። ባጠቃላይ ከእንግዲህ ወዲህ ለውይይት የሚጠቅሙን ኢትዮጵያ በንፅህናዋ የተበጀውን ፣ በመንፈሳዊ ኃይል የተመራውን የኢትዮጵያኒዝምን ፍልስፍና ተጠቅመን ትልቅ እንደ ነበረች እንደ ገና ትልቅ ለማድረግ ተሳስበን ተደማምጠን በታላቅ ትሕትና በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንገንባት። ሁሉ ነገር ከሃገራችን ስለ ተፈጠረ ለሌሎች ምሳሌ ስለ ሆንን ሃገራችን ወደ ፊት እንድትሄድ ጠንክረን እንሥራ። ከእርስዎ አመራር ምን ይጠበቃል? ገጽ 5 የ8 ሌሎች ሃገራት በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ተጠቅመው ነጻ የወጡና ሃገራቸውን ወደ ተሻለ መንገድ የመሩት በእኛ ኢትዮጵያዊነት ጥንካሬ እና የደረሱብንን የተለያዩ ተግዳሮቶች ተቋቁመን በነፃነት መኖር በመቻላችን ነው። አሁን ሃገራችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ስንመለከት በዘር፤ በኃይማኖት እና በጎሳ ተከፋፍሎ ሕዝቡን በቋንቋ እና በክልል አዋቅሮ በመግዛት፤ ከኢትዮጵያዊነት በፊት ለጎሳ ቅድሚያ እንዲሰጥ፣ በሥራ ምክንያት ከቦታ ወደ ቦታ በነፃነት እንዳይንቀሳቀስና ሥራ እንዳይሠራ አድርጓል። ሕገ መንግሥቱ በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን በክልል መንግሥት አደረጃጀት የተመሠረተ ስለሆነ ሕዝቡ ከሃገሩ ይልቅ ቅድሚያ ለብሔሩ እና ለክልሉ እንዲሰጥ አድርጎታል። ይህ የክልል አደረጃጀት እስካልተስተካከለ ድረስ አሁን ሃገራችን ከገባችበት ውጥንቅጥ ችግር ውስጥ መውጣት አትችልም። ሃገራችን ከገባችበት ዘርፈ ብዙና ውስብስብ ችግር ልትወጣ የምትችለው የክልል አወቃቀር ተስተካክሎ ዜጋው ከቦታ ወደ ቦታ በነፃነት የመዘዋወር፤ የመሥራት፣ የመማርና የመኖር መብቱ ተጠብቆ ሊያስኬድ የሚቻለው ለኢትዮጵያዊነት ቅድሚያ የሚሰጥ ሕገ መንግሥት ሲኖር እንደሆነ እሙን ነውና ሕገ መንግሥቱ መሻሻያ ቢደረግበትና ቢስተካከል ለሃገራችን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት ይቻላል። ሃገራችን ኢትዮጵያ ለውጪው ዓለም በተለይም ለተጨቆኑ ሕዝቦች ራሷ ተቸግራ እና የደም ዋጋ በመገበር የሰጠችው መንፈሳዊ ፀጋ ቀላል የሚባል አይደለም፣ ከራሷ አልፋ ለተጨቆኑ ሕዝቦች ሁሉ ምሳሌ እና አርዓያ የሆነች ሕገራችንን ችግሮቿን እና እንከኖቿን እኛ ልጆቿ በሰለጠነ እና በሰከነ መንገድ በመነጋገር በመደማመጥና በመከባበር ልንፈታና አሁን ካለችበት ወደ ተሻለች ኢትዮጵያ ልናሸጋግራት ይገባል። የሃገራችን የትኛውም ዓይነት ችግር መፈታት ያለበት በራሷ ልጆች መሆን አለበት! በፖለቲካ አመለካከት እና አመከንዮ ባንግባባም እንኳ ለሃገራችን እና ለሕዝቧ ቅድሚያ በመስጠት ወደ መፍትሔ መንገድ መምጣት እንችላለን። እርስዎ የጀመሩት ኢትዮጵያዊነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በአራቱ አቅጣጫ አስተጋብቷል! ሕዝቡም ሲናፍቀው የነበረ ዓቢይ ጉዳይ ነውና ተቀባይነትዎ ጨምሯል! ይጨምራልም። አሁን የተጀመረውን ኢትዮጵያዊነት መነቃቃት ወደ ተሻለ እና ከፍ ወደሚል ደረጃ ለማድረስ እርስዎ ብቻ ሳይሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ ኃላፊነቱን መወጣት እና አሁን ካለንበት የብሔር እና የሃይማኖት ችግር ወጥተን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሃገሩ ተከብሮ የሚኖርበትን ዕድል ለመፍጠር ሁላችንም በጋራ የምንሠራበት ዕድል መፈጠር ይኖርበታል። አሁን ከሚታየው ተስፋ እና ጅማሮ በመነሳት ሃገራችን ወደ ቀድሞ ክብር እና ዝናዋ የምትመለስበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም። በእርስዎ አመራር የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባሮች እንዲከናወኑ በትሕትና እናመለክታለን፤ 1ኛ/ የኢትዮጵያኒዝም መንፈስ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪቃና በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲሰራጭ፤ እንዲዘረጋና እንዲዳብር ማድረግ፤ 2ኛ/ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ሙሉ መሻሻል እንዲያስገኝ መለወጥ ከሚገባቸው ብዙ ጉዳዮች አንዳንዶቹን እንጠቁማለን፤ ገጽ 6 የ8 የክልል አስተዳደር ኢጣልያኖች ኢትዮጵውያንን መግዛት የሚቻለው በመከፋፈል ነው በማለት የዘረጉት አስቀያሚ ሥልት ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ መላቀቅ አለባት። በዘር፤ በኃይማኖት፤ በቋንቋ የኢትዮጵያን ሕዝብ መከፋፈል እንደ ሀጢአት የሚቆጠር በመሆኑ ሐገራችን በክፍለ፟ ሐገር እንድትደራጅ ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር የሃገራችንን ረጅም ታሪክ፤ ጥበብና ዕውቀት በሚያጎላ መንፈስ እንዲስፋፋ ይሁን። በተለይ ሰንደቅ ዓላማው ኣረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ ቀለማት ብቻ የሚታይበት ሆኖ መንግሥት በተቀየረ ቁጥር ሊለዋወጥ አይገባም። በአፍሪቃ አፍሪቃውያን የፈጠሩት ፊደል ግዕዝ ብቻ ነው። ስለዚህ በዚህ ታሪካዊ ፊደል መጠቀም ሲገባን በሌሎች ባእድ ቋንቋዎች ፊደሎች ለምሳሌ በላቲን መጠቀም ተገቢ አይደለም።12, 13 ከኢትዮጵያ አካባቢ እንደዚሁም የመላ አፍሪቃ አንድነት በጣም አስፈላጊ ነው። በእዚህ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያ ልዩ ሚና እንዳላት መገንዘብ ያስፈልጋል። ይኸውም በዓለም ሕዝብ ከ1829 እስከ 1929 ድረስ የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ጊዜ የነበረ መሆኑ በዓለም ተሰራጭቷል። በኢትዮጵያ ስም ሁለት ማኒፌስቶዎች (መመሪያዎች) በ1829 ዓ.ም. በአሜሪካ፤ በ1896 በደቡብ አፍሪቃ፤ ከአድዋ ጦርነት ድል በኋላ ተሰራጭተዋል። አፍሪቃ በሙሉ በኢትዮጵያ ስም የሚታወቅበት ጊዜም እንደ ነበረ ማስተዋል ይገባል። ኢትዮጵያ በታሪኳ ያከናወነችውን አሁንም እንድትቀጥልበት ያስፈልጋል። ይህም ታሪካዊ መሠረታችን ነው። ከእዚህ ቀደም የነበረው የእርስ በርስ መፈራረጅ፤ የመለያየትና ችግር ሲያጋጥም ወደ ጦርነት ከማዘንበልና በውጭ ሃገሮች መሣሪያ ከመጠቀም፤ ወደ መወያየት፤ መግባባትና መመካከር ባሕል መለወጥ ይጠቅማል። የኢትዮጵያን ችግር በኢትዮጵያውያን መፍትሔ ማስወገድ ይገባል። በውጭ እጅ ላይ መተማመን መክፋፈል ያስከትላል። የመንግሥቱ አወቃቀር ግልጥነት፤ የወስጥ ቁጥጥር፤ ውጤታማነት የሚያሰፍን ሊሆን ይገባዋል። የመንግሥት ሠራተኞችና ባለሥልጣኖችም ሊመደቡ የሚገባው በተገቢ መስፈርት ብቁነታቸው ብቻ ሳይሆን ተደጋጋሚ ሥልጠናም እየተከናወነላቸው በቂ ቅልጥፍናና ከሙስና የተላቀቀ አገልግሎት እንዲያበረክቱ ማድረግ ያስፈልጋል። የበላይ አመራሩ የጊዜ ገደብ ይወሰን። 3ኛ/ ኢትዮጵያ ካለችበት ቀውጢ ጊዜ ተላቅቃ አስተማማኝ ወደ ሆነ ጎዳና እንድትገባ ሁሉም ማለት የፖለቲካ፤ የማሕበረ ሰብዓዊ፤ የመንፈሳዊ፤ ወዘተ ድርጅቶች የሚሳተፉበት የሽግግር ሒደት ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ። የእርስዎንም የአስተዳደር ዘመን እስክ መጨረሻው ለሃገር የሚበጅ ውጤታማ እንዲሆን እንመኛለን። ኣገርን በጎሳ መከፋፈል ኢትዮጵያን ሰማንያ ቦታ መከፋፈል ነው። በኢትዮጵያዊነቱ ተከባብሮ መኖር የማይችል ሕዝብ በየቤተሰቡ መንግሥት ፈጥሮ መኖር ኣይችልም። ለኣፍሪቃውያን መከታና ኣለኝታ ሆኖ የቆየው ኢትዮጵያዊነት ኣፍሪቃ ኣንድ ኣገር ሆና መብቷ በዓለም ደረጃ እስኪመለስ ከመንደርና ጎሳ ኣስተሳሰብ መላቀቅ ይገባናል። ከታላቅ አክብሮት ጋር! እግዚአብሔር ሃገራችንን ይባርክ!! 
1 ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ 
2 ፕሮፌሰር ሲሳይ አሰፋ 
3 ፕሮፌሰር ብርሃኑ መንግስቱ 
4 ፕሮፌሰር ኃይሌ ላሬቦ 
5 ዶ/ር ኣበራ ሞላ 
6 ዶ/ር ወርቁ አበራ 
7 ዶ/ር ጌታቸው ተመስገን ገጽ 7 የ8 
8 ዶ/ር አበባ ደግፌ 
9 ዶ/ር እጀቡሽ አርጋው 
10 ወ/ሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታ
11 የተከበሩ የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ ግርማ ሰይፉ 
12 አቶ ምንተስኖት መንገሻ  አቶ ሰይፉ ኣዳነች ብሻው
13 አቶ በትሩ ገብረ እግዚአብሄር  አቶ ኪዳኔ አለማየሁ
14 አቶ እርቅርማሪያም ደረስ  አቶ ተፈራወርቅ አሰፋ  አቶ ይልማ ዘሪሁን  አቶ ይርጋለም ጎበዜ 
15 አቶ ከድር ሰይድ  አቶ መሸሻ ካሳ 
16 አቶ ኤሊያስ ማሞ 
17 አቶ ብርሃኑ ገመቹ 
18 ወ/ሮ አስቴር ኃይሌ 
19 አቶ በቀለ ተገኝ 
20 አቶ አብርሃም ቀጀላ 
21 አቶ ግርማ ካሳ 
ዋቢ 1. Ethiopianism, http://www.druglibrary.net/olsen/RASTAFARI/campbell.html
2. ETHIOPIANISM IN PAN-AFRICAN PERSPECTIVE, 1880-1920, https://www.upjournals.co.za/index.php/SHE/article/view/85
3. Abyssinian Baptist Church, New York City (1808- ) http://www.blackpast.org/aah/abyssinian-baptist-church-1808
4. Ethiopianism in African Christianity, https://repository.up.ac.za/bitstream/handle/2263/21579/011_Chapter10_p258- 277.pdf?sequence=12 5. Ethiopianism and African Nationalism in South Africa before 1937, https://www.persee.fr/doc/cea_0008-0055_1986_num_26_104_1689
6. Ethiopianism, http://www.blackpast.org/gah/ethiopianism
 7. Ethiopianism and the Independent Church Movement, http://www.worldhistory.biz/sundries/4707
8-ethiopianism-and-the-independent-churchmovement.html 8. Ethiopianism, https://www.britannica.com/topic/Ethiopianism
9. Ethiopianism a symbol of resistance to injustice, http://www.aau.edu.et/blog/ethiopianism-a-symbol-of-resistance-to-injustice-thabo-mbeki/
10. John Dube, http://www.anc.org.za/content/john-dube ገጽ 8 የ8
11. Ethiopian Muslims History, http://www.selamta.net/ethiopian%20muslims%20history.htm
12. http://www.ethiomedia.com/1000dir/oromigna-be-amara-kilil-be-geez-fiddelendiset.pdf
 13. http://www.ethiomedia.com/1000dir/open-letter-to-president-lemma-megersa.pdf8

ክስተቱ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮችን አስቆጥቷል



ዋዜማ ራዲዮ- የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የሕዳሴው ግድቡ ዉሀ የሚተኛበትን ሰፊ ቦታ ከደን ነጻ እንዲያደርግ 2 ቢሊዮን ብር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን የተሰጠው ከዓመታት በፊት ነበር፡፡ አሁን ግን ገንዘቡ ሳይባክንብኝ አልቀረም እያለ ነው፡፡ ይህ ገንዘብ የተከፈለው ከመንግሥት አሠራር ውጭ ፣ ያለምንም መደበኛ ውል፣ ሥራው ተሠርቶ እንደተፈጸመ ተደርጎ መቶ እጅ ክፍያን በመፈጸም ነው፡፡
ሜቴክ ገንዘቡን ከተቀበለ በኋላ ግን ሥራው መስተጓጎል ገጥሞታል፡፡ ገንዘቡን ጠፍቶበታል፡፡
ፕሮጀክቱ የሚጠይቀው የሰው ኃይል እጅግ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ ሁኔታ መሠራት ቢኖርበትም ሜቴክ በወቅቱ ያዘጋጀውን ጨረታ በመሰረዝ የቀድሞው የሕወሓት ታጋዮች መቋቋሚያ እንዲሆናቸው በሚል ሥራውን ያለጨረታ አሳልፎ ሰጥቷቸው ነበር፡፡
ኾኖም ነባር ታጋዮች ለተሰጠው እድል አመስግነው ሥራውን በወቅቱ የተረከቡ ቢሆንም የስራውን ስፋት ከግምት በማስገባት ለሌላ ሦስተኛ አካል ‹‹ሰብ ኮንትራት›› መስጠት እንዳለባቸው ከስምምነት ደርሰው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት በግምት ከአዲስ አበባ እስከ ዝዋይ ያክላል የሚባለውን ይህን ሰፊ በደን የተሸፈነ ቦታ መመንጠር የሚችሉ በሺ ለሚቆጠሩ የተደራጁ ወጣቶች ሥራውን በስምምነት አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ ስምምነቱም ወጣቶቹ እንዴትም ብለው ምንጠራውን በብቃት እንዲወጡና ክፍያ ሲፈጸም ግን ሰባ በመቶውን ለነባር ታጋዮች እንዲያካፍሉ የሚል ነው፡፡
ይህን ስምምነት ተከትሎ በሺ የሚቆጠሩና ራሳቸውን በ72 ማኅበራት ያደራጁ ወጣቶች ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘምተው ነበር፡፡ መቶ ሚሊዮን ብር ለሥራ ማስኬጃ ቅድመ ክፍያ የተቀበሉት እነዚህ ወጣቶቹ በከፍተኛ ሞራልና ተስፋ ወደ ስፍራው በመዝመት፣ ከአጎራባች አካባቢዎችና በተለይም ከጎጃም የጉልበት ሠራተኞችን በገፍ በመመልመል የዛፍ ቆረጣውን ሥራ ጀምረውት ነበር፡፡
‹‹በባህላዊ መንገድ ዛፎቹን መመንጠር የጀመርነው ዘመናዊ መጋዞች ከአየር ንብረቱ ጋር ስላልተጣጣሙልን ነው›› ይላል በዚህ ሥራ ተሠማርተው ከነበሩ ማኅበራት የአንዱ አስተናባሪ ለዋዜማ ሲናገር፡፡ ‹‹እውነት ለመናገር የገንዘቡን ትልቅነት እንጂ የሥራው ስፋት ሳንረዳ ነበር የገባንበት›› የሚለው ይኸው ወጣት በእድሜ ልክ የማያገኙትን ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ውሎና አዳራችንን ጫካ ውስጥ በቀለሷቸው ድንኳኖች ለማድረግ ተገደው እንደነበር ያስታውሳል፡፡
1500 ኪሎ ሜትር እስኩዌር እንደሚሸፍን የሚነገረው ይህ ደን ግድቡ ካለበት ወደ ኃላ በትንሹ 200 ኪሎ ሜትር ይሸሻል፡፡
በስድስት ወራት ብቻ 56ሺ ሄክታር ደን ጨፍጭፈን ከጨረስን በኃላ በስምምነታችን መሠረት ሁለተኛ ዙር ክፍያ ስንጠይቅ ‹‹አትቸኩሉ›› ተባልን የሚለው ይህ ወጣት የመጀመርያ ክፍያውን በዋናነት ለቁሳቁስ መግዣና ለዕለት ቀለብ ስላዋልነው ሁለተኛውን ክፍያ በጉጉት ለመጠበቅ ተገደን ነበር ይላል፡፡
‹‹ቀላል ሥራ አልነበረም፡፡ 12ሺ የጉልበት ሠራተኞች ተሳትፈውበታል፡፡ ዛፎችን ለመገንደስ ትልልቅ መጋዞች ሊቋቋሙት ባለመቻላቸው በሺ የሚቆጠሩ መጥረቢያዎች ከተገዙ በኋላ በሰው ጉልበት ነበር ሥራው ያሠራነው፡፡ 12ሺ የጉልበት ሠራተኞች ቁርስ ምሳና እራት እንዲሁም የበረሀ ድንኳን ማቅረብ፣ ሕክምናና ሌሎች ፋሲሊቲዎችን መስጠት የኛ ድርሻ ነበር፡፡ በዚህ አስቸጋሪ ሂደት ሰዎች ሞተውብናል፤ እባብ የነደፋቸው የጉልበት ሠራተኞች፣ ወንዝ የወሰዳቸው ዛፍ ቆራጮች አሉ፡፡›› ሲል ፈተናው እንዴት አስቸጋሪ እንደነበር ለዋዜማ ተናግሯል፡፡
ቃል የተገባልን ክፍያ በጣም ሲዘገይብን ግን እኛን ከቀጠሩን ታጋዮች ጋር ሆነን ከፍተኛ ባለሥልጣናትን በደብዳቤና በአካል መጠየቅ ጀመርን ሲል ሂደቱን ያስረዳል፡፡
‹‹በመጨረሻም ከጄኔራል ክንፈ ጋር ቀጠሮ ተይዞልን መነጋገር ስንጀምር ገንዘቡ ለሌላ አጣዳፊ ነገር ውሎ ሊሆን ስለሚችል ያንን እስካጣራ እናንተ ሥራችሁን ቀጥሉ እንዳሏቸው ይናገራል፡፡ ሥራችንን ምን ይዘን እንደምንቀጥል አልገባንም ነበር ይላል፡፡
ከዚያ በኋላ በነበሩ ተከታታይ ስብሰባዎች ግን ነገሮች እየተበላሹ እንደመጡና ነባር ታጋዮችና ጄኔራሉ ሊግባቡ አለመቻላቸውን ያብራራል፡፡
‹‹ለዚህ ሥራ ተብሎ 2 ቢሊዮን ብር ለሜቴክ እንደተከፈለው እናውቅ ነበር፤ ብሩ ግን ሳይባክንባቸው እንዳልቀረም›› የሚለው ይኸው ወጣት ‹‹ምክንያቱም የሜቴክ ሰዎች ሲነግሩን ብሩ እኮ የለም፣ ከየት ነው የሚከፈላችሁ? ይሉን ነበር፤ እኛ ግን አላመናቸውም ነበር›› ይላል፡፡
‹‹እንዲህ አይነት ትልቅ ብር ባከነ ሲባል ለማመን አስቸጋሪ ነበር››
ነገሮች እየተካረሩ እንደመጡ ሲያስረዳም፣ ‹‹እኔ ማኅበሩን በመወከል አልፎ አልፎ ስብሰባዎቹ ላይ እገኝ ነበር፡፡ በትግርኛ ኃይለቃል ሲለዋወጡ እንሰማለን፡፡ በተለይም በአንድ ወቅት የጄኔራሉ የቅርብ ቤተሰብ ነው የሚባል የቀድሞ ታጋይ ‹‹የዕድል ጉዳይ ሆኖ ነው አንተ እዚህ ወንበር ላይ፣ እኔ ዊልቸር ላይ የተመጥነው›› ብሏቸው ስብሰባ ረግጦ እንደወጣ አልተመለሰም ይላል፡፡
ጄኔራሉም ከዚያ በኋላ ስሜታዊ በመሆን ‹‹ይሄ አገራዊ ፕሮጀክት ነው፣ ገንዘብ ገንዘብ አትበሉ፤ እኛ ጨረታ ማውጣት አቅቶን አይደለም፤ እናንተን እናግዝ ብለን ነው የሰጠናችሁ›› ሲሉ መናገራቸውን ያብራራል፡፡
በጄኔራሉ ተስፋ የቆረጡት ታጋዮች ፖስታ ቤት ቅጥር ግቢ ወደሚገኘው የዶክተር ደብረጽዮን ቢሮ በቀጥታ በመግባት መፍትሄ እንዲፈልጉላቸው ጠይቀዋቸው ‹‹ክንፈን አናግሬው እኔ ራሴ መልስ ይዤላችሁ እመጣለሁ፣ በጭራሽ አታስቡ›› ብለው በእርግጠኝነት መልሰዋቸው ነበር ይላል፡፡ ሆኖም ዶክተሩ ቃላቸውን ባለመጠበቃቸው የኛ ተወካዮች አቶ አስመላሽ ጋር በመሄድ እንዲያሸማግሏቸው ተማጽነው ይህም ውጤት ሳያስገኝ ቀርቷል፡፡
ይህን የሰሙት ጄኔራሉ የኛን ተወካዮቹን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠርተው፣ ‹‹ስማችንን በየቢሮው እየሄዳችሁ ታጠፋላችሁ፣ ነገሩን በእልህ ለመጨረስ ካሰባችሁ እኛ እንብሳለን›› በማለት እንዳስፈራሯቸው ይናገራል፡፡
ከዚህ የተራዘመ ሂደት በኋላ ብዙዎቹ ተስፋ ቆርጠው ነገሩን እርግፍ አድርገው የተዉ ሲሆን 12 የሚሆኑ ማኅበራት ግን እውቅ ጠበቆችን በመያዝ ፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸውን ይኸው ወጣት ይናገራል፡፡ ሌሎች ማኅበራት መክሰስ ያልፈለጉት በሌላ ሳይሆን ፍርሃት ስላደረባቸው ነው ይላል፡፡ ‹‹ሜቴክን ከሰን የት እንደርሳለን›› ያሉ ነበሩ፡፡ የመጣው ይምጣ ብለው የከሰሱም ነበሩ ይላል፡፡
ወደ ፍርድ ቤት ከሄዱት ማኅበራት የተወሰኑት ጉዳዩን እንዲይዙላቸው እውቅ ጠበቆችን መቅጠራቸውንና ከነዚህም መሐል የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የአቃቢ ሕግ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ እሸቱ ወልሰማያትና ቀድሞ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩም ይገኙበታል ይላል፡፡
ኾኖም የፍርድ ሂደቱ ከሁለት ዓመት በላይ የወሰደ ሲሆን ዳኞች ጉዳዩ እያሰጋቸው ነው መሰለኝ ቶሎ ቶሎ ይለዋወጡ ነበር ብሏል፡፡
አንዱ በፍርድ ቤት ጉዳዩን አከራካሪ ያደረገው ለማኅበራቱ መከፈል ያለበት የምንጣሮ ሥራ የቦታ ስፋት መለካት ያለበት በጂፒኤስ ነው ወይስ በሜትር የሚለው ሲሆን ሜቴክ በጂፒኤስ ይለካልኝ ሲል ማኅበራቱ በሜትር ነው መለካት ያለበት የተስማማነውም በዚህ መንገድ ነው ብለው ተከራክረዋል፡፡ ምክንያታቸውን ሲያስረዱም የመሬቱ አቀማመጥ ወጣ ገባ ስለሚበዛው በጂፒኤስ ቦታውን መለካት አካባቢው ጠፍጣፋና ሜዳማ እንደሆነ ታሳቢ እንደሚያደርግና የምንጣሮውን ልፋት ግምት ውስጥ የማይከት ያደርገዋል ባይ ናቸው፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ የመጀመሪያዋ ዳኛ የኢትዮጰያ ካርታ ሥራዎች ድርጅት ሞያዊ አስተያየት እንዲልክ በማዘዛቸው የከሳሽ ጠበቆች ቦታው በሜትር መለካት እንዳለበት የሚያስረዳ ደብዳቤ ከዚሁ መሥራያ ቤት አምጥተው ለውሳኔ ቀጠሮ ሊሰጥ ሲል የሜቴክ ጠበቆች ከተመሳሳይ መሥሪያ ቤት ቦታው በጂፒኤስ መለካት እነዳለበት የሚያስረዳ ሌላ ተጻራሪ ደብዳቤ አጽፈው በማምጣት መቻላቸው ፍርድ ቤቱን አስገርሟል፡፡ ሁለቱም ደብዳቤዎች የተፈረመባቸው በተመሳሳይ ሰው መሆኑም ሌላ አግራሞትን ፈጥሯል፡፡
ችሎቱን የምታስችለው ዳኛ በጉዳዩ በመደመም ችሎቱን ድንገት በትና የወጣች ሲሆን ከዚህ ዕለት ጀምሮም ችሎቱን የሚያስችሉት ዳኛ መቀየራቸው ተነግሯል፡፡ ዳኛዋ ከዚህ ውሳኔ ያደረሳቸው ምናልባት ቀደም ብለው የሜቴክ ኃላፊዎች መጥተው እንዲመሰክሩ የሚለው ትእዛዝ ሊከበርላቸው ስላልቻለ ሊሆን ይችላል፡፡
እኚህ ዳኛ ለማኅበራቱ የሚያደላ ውሳኔ ሊወስኑ ይችላሉ በሚል ለውሳኔ ቀጠሮ ከመሰጠታቸው ቀደም ብሎ የሜቴክ ጠበቆች ‹‹የኛ ሠራተኞች ጉዳይ የሚታየው በጦር ፍርድ ቤት ነው›› የሚል ነገር ለችሎቱ ማሰማታቸው ዳኛውን ሳያስቀይማቸው እንዳልቀረም ይገመታል፡፡
ሜቴክ በኮንትራት ለሚሰጣቸው ሥራዎች በጊዜውና ተገቢውን ክፍያ መክፈል ባለመቻሉ ተደጋጋሚ ቅሬታዎች ይቀርቡበታል፡፡
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ በስተምዕራብ 600 ኪሎ ሜትር በኦሮሚያ ክልል ኢሉ አባቦራ፣ ያዩ ወረዳ የድንጋይ ከሰል እያወጣ መሸጡ የሕዝብ ቅሬታን በመፍጠሩ በተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄን አስነስቶ ነበር፡፡
በሌላ ዜና የብረታ ብረት ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን መስርተው ለስምንት ዓመታት ያስተዳደሩት ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኜው ሰሞኑን የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ሳምንታዊው የቢዝነስ ጋዜጣ ፎርቹን ዘግቧል፡፡

Saturday, February 3, 2018

ለትግሉ ወገናዊ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ፣-የአርበኞች ግንቦት ሰባትና የደሚሂት የጋራ መገለጫ በሚመልከት


 1. ማናቸው ድርጅት አርበኞች ግንቦት 7 ጨምሮ ከአባላቱም ፣ከደጋፊዎቹም። ከህዝብም የሚመጣ ትችት መቀበል የግድ ነው (ግዴታው ነው)። ፍጹም ሰው እንደሌለ ሁሉ ፍጹም ድርጅት ሊኖር አይችልም። የሚሰሩ ደግሞ ይሳሳታሉ። ስህተቶችን በአግባቡና ገንቢ በሆነ መልኩ በልዩ ልዩ መስመሮች ሲገለጽ አንድን ድርጅት የሚማርና ስህተቶቹንም እየረመ የሚሄድ ያደርገዋል። በዚህ አመለካከት ያለውን ለትግሉ ወገናዊ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይስማማሉ ብዬ እገምታለሁ።


2. ሰሞኑን የወጣውና ብዙ ውዝግብ ያስነሳው የአርበኞች ግንቦት ሰባትና የደሚሂት የጋራ መገለጫ በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ እንደ ሆነ ምንም የሚያጠያይቅ አይደለም። ስርዓትን መለወጥ ብቻ ሣይሆን የተረጋጋ ሐገር ለመፍጠር እንደሚንቀሣቀስ የፖለቲካ ሃይል በበደል ብዛት የተቆጡ ኢትዮጵያውያን ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት ዉስጥ እንዳይገቡ ማሣሠቡ ተገቢ ይሆናል።በመግለጫው እንደተቀሠው ሠማን እንጂ አረጋገጥን ተብሎ አልተጻፈም፤ በሐገሪቱ ክልሎች የሕወሐት አባላትና የሕወሐት መልዕክተኞች መኖራቸውንም በመግለጫው በግልፅ ያመለክታል፤ በአጠቃላይ የመግለጫው ይዘት ትናንት ከተከሠተው ይልቅ ሥለነገው የሚጨነቅ መሆኑንም ማስታወሡ ተገቢ ነው፡፡ የመግለጫው ዓላማ ይህ ቢሆንም በአንድ በተሻለና እወነታውን በተጨባጭ ከማሳየት ይልቅ አሻሚ በሆነ ቋንቋ በተጻፈ አንድ አንቀጽ ( በአንዱ ዛፍ) .ጫካው በመሸፈኑ ውዥንብር ተከስቷል፡፡

3. በዋናው ጭብጥና መንፈስ (በጫካው) ወስጥ የተካተተው መልክት ሕዛብዊ ወያኔ አርነት ትግራይ (ህወአት) በአልሞት ባይ ተጋዳይነት ኢትዮጵያን ካልገዛሁ ኢትዮጵያን አፈርሳታላሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ፣ ይህንንም ተግባራዊ ለማድርግ የትኛውንም ስልት ከመጠቀም ወደሁዋላ እንደማይል፣ ከነዚህም መሰሪ ስልቶቹ ወስጥ በዋነኘት የትግራይን ህዝብ ምሽግ ለማድረግ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ማናከስና ወደ የማይታረቅ ቅራኔ ወስዶ የትግራይን ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያ ህዝብ መነጠል ብሎም መገነጠል በመሆኑ
ሀ) “የትግራይ ህዝብና ህወአት አንድና የማይነጣጠሉ ናቸው” የሚለውን የ 26 አመታት የወያኔ ትረካና ፕሮፕጋናዳ መናድ፣ ማፍረስ ወሳኝ የትግሉ አካል መሆኑን ።
ለ) የትግራይ ህዝብ ፣ የትግራይ ምሁራን፡ የትግራይ ድርጅቶች የዚህ የወያኔ መሰሪ ተግባር ሰለባ እንዳይሆኑ እንዲያውም ትግሉን ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመሆን እንዲያቀጣጥሉ ጥሪ ማቅረቡ።
በትክክሉ፡ በጥልቀትና በረጅሙ በማሰብም የኢትዮጵያ ሀገራችን የወደፊት ሰላም ፣ ሀገራዊ አንድነት፡ የህዝቦች አብሮ መኖር መጻኢ እድል ለሚያስስበው ማናቸውም ቅን (ቅንን የሚለው ይሰመርልኝ) ኢትዮጵያውያን ሁሉ ይህ መልክት ወቅታዊም አንገብጋቢም መሆኑን ሊያጡት አይችሉም ።
4. የወያኔ ፋሽስቶች የትግራይን ህዝብ ምሽግ አድርጎ የአምባገናዊ የዘረፋና የዘረኘነት ስረአቱን ለማሰቀጠል የሚያደርገውን የአልሞት ባይ ተጋዳይ እንቅሳቃሴ ለማምከን የኢትዮጵያ ህዝብ የጀመረውን ሁለ ገብ ትግሎችና ከወያኔ ፋሽስቶች ጋር የሚያድርገውን ትንንቅና ፍልሚያም በሚያፋፋምበት በአሁኑ ሰአት በሁሉም አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦችና ታጋዮች ሁሉ (በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ የኣርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮችን ጨምሮ) የህወአትን ሰላዮችና ገዳዮች ከስርአቱ ጋር ምንም ቁርኘት ከሌላቸው የትግራይ ተወላጆች ነጥሎ መመታት አስፈላጊና ፡ ህዝቡም በትግሉ ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው ነው በመግለጫው የተገለጸው።
5. ሌላው የመገለጫው ጫካ ዋና መንፈስ የአግ7 ንቅናቄ በወያኔ ፋሽቶች የአልሞት ባይ ተጋዳይነት ተንኮልና መሰሪነት ሊመጣ የሚችለውን የእርስ በእርስ ጦርነት ከፍተኛ ስጋት እንዳለው ነው የተገለጸው። በዚህ ፋሽታዊው ሕወአት በሸረበው ወጥመድ ውስጥ ታጋዩ ማህበረሰብ እንዳይገባ፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ነው ያሰመረበት፡ እነዚህ ዋና ዋና መልክቶች መግለጽ ሃላፊነት ከሚሠማው የፖሊቲካ ድርጅት የሚጠበቁ ተግባራት ናቹው፡፡

6. በእርግጥ በዚሁ ብዙ አነጋጋሪ በሆነው መግለጫ ላይ የተጻፈው አንድ አንቀጽ (አንድ ዣፍ) የሚሰጠው ትርጉም ከላይ በስተመጨረሻ #5 ከተጻፈው የተለየና ብዙዎች በሌላ መልኩ እንዲረዱት ማድረጉ ለተነሳው ውዝግብ መንሴኤ ሆናል።
7. በብዙሃን ቅን ኢትዮጵያውያን (አባላት፡ ደጋፊና፡ ለትግሉ ቀናዊ ከሆኑ) ኢትዮጵያውያን ወንድሞችና እህቶች አወዛጋቢዎችን አንቀጽ በሚመለከት የተነሱ ጥያቄዎች፣ ገንቢ አስተያየቶችና ፡ እርምት እንዲደረግና ንቅናቄው መልስ እንዲሰጥበት ከሚያስስቡ መልክቶች ሁሉ እንደተጠበቁ ሆነው ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ከወያኔ ይልቅ ትግላቸውን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ጋር ለማድረገ የወስኑ ክፍሎችን በተመለከተ በአጭሩ ለማለት የምፈልገው በእርግጥ የሕዝቡ ሥቃይ ይሰማችኃልን ? በእርግጥ ከተሰማችሁ ሕዝብን ከሚያሠቃየውና ከሚጨፈጭፈው ሕወሐት ይልቅ ሕወሐትን የሚታገለው አርበኞች ግንቦት 7 እንዴት ዋነኛ ጠላታችሁ ሊሆን ቻለ? .መልሡን በቅንነት ለሚዳግፏቸው ወገኖቻችን እንደሚሰጡ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
8. የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ምንም ሳይደርስባቸው ገና ከጅምሩ በጠላትነት ፈርጀውት ከወያኔ ይልቅ ዱላቸውን በሙሉ ጊዜና ህይል ሳይቆጥቡ ለዚህ የጎንዮሽ ልፊያና ጠለፋ የሰጡ፣ ነገር ግን ለዚህ ውስብስብና ብዙ አቀበትና ቁልቁለት ለበዛበት ትግል ምንም ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ የማያደርጉ ግለሰቦችና ቡድኖች ማህበራዊ ሚዲያውን አጨናንቀውት እያየን ነው፡
9. በአንጻሩ ይህን ትግል ዳር ለማድረስ ምን ያህል መስዋእትነት እየተከፈለና በተግባርም ብዙ ብዙ ተግባራዊ ስራዎች በሀገር ውስጥም በውጭም እየተሰሩ እንደሆነ የሚያውቁ፣ የሚረዱ፣ ለትግሉም ቀናኢ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የዚህ መሰሪ አካሄድ ሰለባ ላለመሆን ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግና ፡ በስሜት ሳይሆን በአምክንዮና ለትግሉ የሚጠቅመውን፡ የወያኔን ፋሽታዊ አገዛዝን የሚያስጨንቀውና የሚያዳክመውን፣ የኢትዮጵያን ህዝብ ለድል የሚያደርሱ፣ የሚያበቁ ፣ ለሀገራችን ኢትጵዮጵያ ትንሳኤን የሚያፋጥኑ ተግባራት ላይ ማተኮር ይገባል። በሰከነ አእምሮ ማሰብ የሚያስፍልግበት ስሱ ወቅት ስለሆነ፡ ቆም ብለን ፡ ትንፋሽ ወስደን በረጅሙና ከፊታችን በተደቀነው ተግባሪዊ ትግል ላይ አይናችንን እንዳናነሳ ማድረግ ያስፈልጋል። ጥንቃቄ እንዳርግ በሚል በትህትና ለማሳሰብ እወዳለሁ።
ነአምን ዘለቀ

Monday, October 30, 2017

ህወሃት ጣእረሞት ባጭሩ ሲዳሰስ (መስቀሉ አየለ ,October 24, 2017)


Meles Zenawi on fireለዘር ፖለቲካ የበላይነት በመስጠት ኢትዮጵያዊነትን ለማዳከም የቋንቋ ባቢሎን ገንብቶ ክልላዊ አድረጃጀትን ሲገነባ የኖረው ወያኔ የዘራው ዘር ፍሬ አፍርቶ ዛሬ የሱን ልሳን የሚናገሩ ሚሊዮኖች በየአቅጣጫው እንደ እንጉዳይ መፍላት ጀምረዋል። በዚህም የተነሳ ማእከላዊ መንግስቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ግባተ መሬቱ ተፈጽሟል ማለት ይቻላል።
በመሆኑም ከታሰበላቸው አቅም እጅግ አልፈው በመሄድ ለራሱ ለህወሃት የማይበጁበት ብቻ ሳይሆን የህልውናው ስጋት ወደ መሆን ደረጃ የደረሱትን ክልሎች እንደገና በማዳከም ብሎም ማእከላዊ መንግስቱን በተወሰነ ደረጃ በማጠናከር የህወሃትን የበላይነት መልሶ ለማስጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት መቀሌ ከትሞ የከረመው የትግራዩ ገዥ ጉጅሌ አንድ እስትራቴጅ ይዞ ወጥቷል።
ይኸውም በለማ መገርሳ፣ ዶር አቢይና አዲሱ አረጋ በኩል የታየው መቀናጀት፣ በተሾሙ በአጭር ግዜ ውስጥ ያገኙት የህዝብ ተቀባይነት እንዲሁም ከብአዴን ጋር የጀመሩት የጎንዮሽ ግንኙነት ቀጣዩን አደጋ ቁልጭ አድርጎ ያሳየው በመሆኑ በእድገት ሽፋን ወደ ፌደራል መንግስቱ አምጥቶ ከህዝብ በመነጠልና ሽባ በማድረግ እነሱን የተሻለ ሎሌ ሆነው ሊተኩ በሚችሉ አዳዲስ አሽከሮች ለመተካት ከስር ሰዎች አዘጋጅቶ የጨረሰ ሲሆን ሂደቱም ሃይለማርያም ደሳለኝን በራሱ በለማ መገርሳ እስከመተካት ድረስ ዘልቆ ሊሄድ እንደሚችል ፍንጮች መታየት ጀምረዋል።
ነገር ግን ይህ አካሄድ የማያዋጣ እና ህዝባዊ ተቃውሞውም የሚቀጥል ከሆነ “ማእከላዊ መንግስቱ ሃላፊነቱን ባለመወጣቱ የአገሪቱን ህልውና ሊያስጠብቅ ስላልቻለ በህዝቡ ላይ ያንዣበበውን አደጋ ለመቀልበስ መከላከያው ላልተወሰነ ግዜ አገሪቱን የመምራት ሚናውን እንዲወጣና ጸጥታ እንዲያስከብር ሃላፊነቱን ወስዷል” በሚል አጭር የማርሻል አዋጅ ቤተመንግስቱን በታንክ በመክበብ የሃይለ ማርያምን ካቢኔ ጠራርጎ በማውረድ በኩዴታ ስልጣኑን ለሳሞራ የኑስ ወደማስረከቡ ይሄዳል ማለት ነው።
የመጀመሪያው አማራጭ የማይሰራ ከሆነና ወደ መፈንቅለ መንግስቱ መሄድ የግድ ከሆነበት ደግሞ ለዚሁ እርምጃ እንደዋና ግብአት ይሆነው ዘንድ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ዘር ተኮር የሆኑ ግድያዎችና ዘረፋዎች በስፋትና በተቀናጀ መልኩ በተጏዳኝ እንዲካሄዱ ህወሃት ያለውን አቅም ሁሉ አሟጦ እየተጠቀመ ነው። እዚህ ላይ ወያኔ አሁን ባለው የዘር ክፍፍልና ውሱን አቅም እንደ ግብጹ ሴሴ መፈንቅለ መንግስት አደርጋለሁ ቢል ይሳካለታል ብሎ ማሰብ አይቻልም። ይልቁንም ለህወሃት እንደዳይኖስረስ እራሱን በራሱ በልቶ ለመጨረስ የመጨረሻው ደወል መሆኑ አይቀርም።
በመሆኑም በተለያዩ የኦሮሞያ ግዛቶች ሰሞኑን በከፋ መልኩ ሲፈጸም እያየነው ያለው ከኢንተርሃሞይ የማይተናነስ የዘር ማጽዳት ከጌታቸ አሰፋ እየተቀበለ የሚያስፈጽመው ሰው ረዳት ኮሚሽነር ደመላሽ ገ/መስቀል ይባላል። ይኽ ሰው የኦሮሚያ ክልል የአስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ነው።የትውልድ ስፍራው ምእራብ ሸዋ ዞን፣ የትምህርት ዝግጅት፦ በፖሊስ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በአመራር ሳይንስ እና በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን ሁለተኛ ዲግሪ ሲኖረው የስራ ልምዱ በኦሮሚያ ክልል ከወረዳ አንስቶ እስከ ክልል የፖሊስ አመራር፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።እዚህ ድረስ የደረሰው ለህውሓት ታማኝ በመሆኑ እና በጣም ጨካኝ እንደሆነ ይነገራል።

ESAT News (October 30, 2017)
A member of the European Parliament who is a fervent critic of the TPLF said current political developments in Ethiopia could lead to conflict with tremendous consequences to the Horn of Africa.
Speaking to ESAT on the phone, the Portuguese politician said she fears that the ongoing conflicts in various parts of the country will go out of hand with serious ramifications to the region and even to Europe.
Ana Gomes, who was an observer for the rigged 2005 election in Ethiopia, said the 2015 election in the country was a farce and no one came to observe it. As a result, the MP said the Ethiopian regime has no legitimacy. She wonders why the U.S. and EU still continue support the regime.
“It is really shocking to me that powers such as the U.S. and the EU and its member states know very well that TPLF has no legitimacy and democratic bases in Ethiopia and still continue to support under the pretext that it is an ally against terrorism,” Gomes said.
She said recent resignation by officials of the government and members of the army show that there is “tremendous fragmentation” and “lack of coherence with in the TPLF.”
“It shows that the situation is fast unravelling.”
“Those in U.S. and Europe used excuses to turn a blind and have neglected the democratic aspiration of the people of Ethiopia. The fact that they have supported and turn a blind eye to the totalitarian regime of the TPLF is going to provoke an uncontrolled explosion in Ethiopia. I am very very worried for Ethiopia as well as the Horn of Africa and Europe too because it has an implication for Europe,” Gomes added.
Speaking about Bereket Simon, who recently announced his resignation, and an official whom she dealt with during the 2005 election, the Member of Parliament described him as “cynical, cruel and despicable.”
“After Meles, he was the most despicable character i had to deal with.
He has a murky character. He could be operating from behind. I had always been extremely suspicious about him.”.
She also talked about Dr. Tedros Adhanom, the Ethiopian Director General of the WHO who was recently under fire for nominating Zimbabwe's Robert Mugabe. She said Dr. Tedros is “a member the TPLF and responsible for crimes committed by the criminal organization.”
She advised that change in Ethiopia will occur if Ethiopians come together and take matters in their own hands.
“They should not expect someone else come and make changes in the 

Ethiopia: 'Red Terror' war crimes trial begins at The Hague



An Ethiopian soldier stands inside the Martyrs Memorial to the "Red Terror" at the Holy Trinity Church in Addis Ababa, Ethiopia on 24 February 2004.
Image copyright Getty Images
Image 
caption Eshetu Alemu is accused of ordering the execution of 75 people during Ethiopia's "Red Terror"

The war crimes trial of an aide to Ethiopia's former communist ruler has begun in the Netherlands.
Eshetu Alemu, 63, is accused of ordering the execution of 75 people during Ethiopia's "Red Terror" purges in the late 1970s.
The former aide to then ruler Mengistu Haile Mariam is also accused of torture and inhumane treatment. He denies all the charges against him.
More than 300 victims have been named in four war crimes charges.
Ethiopia has sentenced him to death in absentia.Read more about Ethiopia
Prosecutors allege that Alemu, a dual Ethiopian-Dutch national, was a henchman for Mengistu in the north-west Gojjam province.
As his trial opened at a domestic court in The Hague, Eshetu Alemu said that prosecutors had "the wrong person".
"I was really shocked when I heard what prosecutors are accusing me of doing, that I could behave like that as a human being. I deny the charges against me," he told the four judges.

The Mengistu regime and the Red Terror



Image copyright Getty Images
Image caption Mengistu Haile Mariam governed Ethiopia between 1977 and 1991
Marxist strongman Mengistu Haile Mariam ruled Ethiopia between 1977 and 1991 following the overthrow of Emperor Haile Selassie in 1974.
There was significant repression under his communist regime. This became known as the "Red Terror".
Mengistu was ousted in 1991 after a series of revolts by insurgent groups. He then fled to Zimbabwe where he still resides.
In 2007, Mengistu was found guilty in absentia of genocide.

In a statement, prosecutors said that Alemu "allegedly ordered the killing of 75 young prisoners" in a church.
The bodies were then dumped in a mass grave, they said.
Alemu is also accused of "arbitrary detention and cruel and inhuman treatment of civilians and fighters who had laid down their arms" .
It is alleged that he tied prisoners up, suspended them in mid-air and beat their bare feet with sticks.
It is expected that a number of his alleged victims will give evidence during the trial.

'Terrible things happened'

Alemu testified in Dutch and told judges that he was a senior member of the Marxist-Leninist regime which governed the country. He said he was "responsible for propaganda" and had been targeted for assassination by other political groups.
In a statement read by presiding judge Mariette Renckens, Alemu said that "terrible things happened". He responded "no" when asked if he had "ever signed an execution order".
But the judge told Alemu that his signature was on an August 1978 order saying that "revolutionary measures" had to be be taken against more than 70 prisoners.
Orders of this kind, she said, usually meant "execution without trial".
Alemu denied giving the order, saying he lacked the authority to do so. "I was never there," he said.

Most big names already tried

Analysis by Tibebeselassie Tigabu, BBC Amharic service
People in Ethiopia are only really interested in this case because it is happening in The Hague.
Alemu is not a well-known figure from the Mengistu regime. Most of the big names have already been tried - and pardoned - over the past few years.
The trauma of the genocide is still felt among the people because it touched every house across the country.
The thing that interests and troubles people most is the fact that the late president Mengistu Haile Mariam is still at large in Zimbabwe, despite the fact that he has been sentenced to death in absentia.