Sunday, February 23, 2014

ለ አብራሪው ( በ ይግዛው እያሱ)



ቢመረው ቢከፋው ግፍ አላይም ብሎ 
ጨርቄን ማቄን ሳይል ካገር ወጣ ጥሎ።
ለሙያው ሊታመን ምሎ ቢቀጠርም
ስራን በነጻነት ሊያገኘው አልቻለም።
የህዝብ ብሶት መከራ በሱ ተመስሎ
ላይመለስ ሸኘው ድምጽ አሰማ ብሎ።
ይህ የህዝብ ድምጽ ነው የአንድ አገር ዜጋ
በግፍ የሚገረፍ በወያኔ አለንጋ።
22 ዓመት ህዝብ ከህዝብ ከፋፍለው
አንዱን ባንዱ አዝምቶ አንገት የሚያስደፋው
የወያኔን መንግስት የግፍ አገዛዙን
ለዓለም ሊያሳውቅ ነው በመጥላት እራሱን።
በጣም በተሻለ መኖር እየቻለ
ለሆዱ ሳያድር ነጻነቴን ያለ
የቁርጥ ቀን ጀግና እንደ ሀይሌም የለ። (ሀይለመድህን)
የዓለም መንግስታት ይህን ይወቁልን
ለሀይለመድህን አበራ ጥሩ ፍርድ ይስጡልን።
ወያኔ እንደሚለው አሸባሪ አይደለም
ወያኔ እንደሚለው አገሩን አልከዳም
ወያኔን ግን ከድቷል ህዝብን አስቀድሞ
ራሱን ሻማ አርጎ የወገን ድምጽ ሆኖ።
ቢሞትም አይቆጭም ቢያስሩትም ይፈታል
ያጎነበሰን ህዝብ አንገት ቀና አድርጓል።
ለተበደለው ህዝብ ድምጹን አሰምቷል።
ሞት አዲስ አይደለም በኢትዮጵያ ምድር
ሁሉ ሚከፍለው ነው ለወያኔ ግብር።
የሱም ተራ ደርሶ ለእርድ ሳይዘጋጅ
በሰማይ እያለ እግዚአብሔር እረድቶት
እራሱ አመቻችቶ ዘዴ ፈጠረለት
ህዝብን አድን አለው ሂድና ጩህለት።
ቃሉን ተቀብሎ ለራስ ሳያዳላ
ጄኔቭ ገባ ሀይሌ ለመፈለግ መላ።
መላ ባንተ ይገኛል ድካምህ አይቀርም
የዓለም መንግስታት ይህን ዝም አይልም።
በቅርብ ታየዋለህ ካንተ ፍርድ ጀምሮ
የኢትዮጵያ አምላክ አይጥልህም ጥሎ።

maleda times | February 21, 2014 at 8:16 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-3DX

Monday, February 3, 2014

9.34 kilos of cocaine in stomach; tummy-ache leads police to 5


Nigerians caught with 441 cocaine capsules in transit lounge of Abu Dhabi AirportBy Mohammed El Sadafy
maleda times | February 3, 2014 at 9:10 am | URL: http://wp.me/p2gxmh-3kH


The give people arrested at Abu Dhabi Airport for drug trafficking and the capsules of cocaine found in the stomachs and intestines.
Five Nigerians have been arrested at Abu Dhabi International Airport during the past 12 days for trying to smuggle 441 capsules weighing a total of 9.34kg of cocaine in their stomachs.
Police said the five men were seen very tired and confused in the transit lounge of the airport.  One of them was suffering from stomach pain.
Colonel Dr Rashid Mohammad Bu Rasheed, Director of Criminal Investigation, said the arrested people had arrived in Abu Dhabi from Sao Paulo in Brazil and Lagos, Kano and Abuja in Nigeria. They tried to change their flight to mislead the police, he added.
He also said the drug traffickers intended to leave the pills in their stomach for more than 24 hours. Their lives could have been at risk even if just of the capsules burst inside their bodies, he added.
Comment   See all comments

በሀገራችን የሉዓላዊነት ጉዳይ እንኳን እሥራት ሞትም ይምጣ(ጌታቸው ዘብ-ጎ )


አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንደሚባለው አበዋዊ የአነጋገር ዘይቤ ሰሞኑን የሰላማዊ ፓርቲ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ያለው ሥርዓት ገዥ ኃይል(ህወሃት) የኢትዮጵያ ሀብት የሆነውን ለሙንና ውሃ ገቡን በአጭር ጊዜ ምርት አምርቶ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ችግር ሊቀርፍ የሚችለውን በርካታ የማሽላ አይነቶች፤ሰሊጥና ኑግ፤ጥጥና የሙጫ ዛፍ በብዛት የሚገኝበትን ለሀገር ውስጥ ፍጆታም ምሰሶ የሆነውን ሕዝብ እንደ መተንፈሻ ሳንባው የሚተማመነውንና እንደ ዐይኑ ብሌን የሚመለከተውን ሰፊውን የምዕራብ ኢትዮጵያ ክቡር ግዛት ለሱዳን ለመስጠት ከሕዝቡ በስተጀርባ በድብቅ ድንበር ማካለል ፊርማ በመፈራረሙ ምሥጢሩን ለህዝብ እናጋልጣለን በማለት የሰላማዊ ፓርቲ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይደናቀፍ በመስጋት ስከታተል ነበር። ትዕይንተ ሕዝቡን ለማካሄድ የሚደረገውን ቅስቀሳ በማዎክ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ላይ ይህ ነው የማይባል ወከባ እሥራት ተፈጸመ። ሕዝብ በዚህማ አትምጡብን አይቀሬ ነው ብሎ ከወጣ በኋላ መንገዶችን ከመስቀል አደባባይ ወደ አራዳ ፤ከመስቀል አደባባይ ወደ ብልኮ ፤ ከመስቀል አደባባይ ወደ ቼቸላ በትራፊክ በመዝጋት ሕዝብ ታግቶ እንደዋለ ከዘ-ሐበሻ ዘገባ ለመረዳት ችያለሁ። ዘ- ሐበሻ ትልቅ ታሪክ ሰርታለች ሁላችንም እናመስግናት። እናም ሰሞኑን ርቄ የምገኝ ብሆንም ከዚህ የተፈረደበት ሕዝብ አብራክ የተፈጠርኩ በመሆኔ ወላጆቼ ጥሬ ቆርጥመው አስከብረው ያቆዩዋትን ሀገሬን የበሉበትን መሶብ የሚደፉ ሰብአዊነትና ርህራሄ የበማይሰማቸው እምብርት የለሽ ሆዳሞች የተፈጸመው ተግባር እጅግ አሳዝኖኛል። በመሠረቱ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲወጣ የተደረገው በደሙና በጥንቱ አስከብሮት የኖረው መሬቱ ታሪካዊ ጠላት ለሆነችው ሱዳን በድብቅ ሊሰጥ በመሆኑ እንጅ ድንጋይ ለመወርወርና ጥይት ለመተኮስ ቢሆንማ መንገዱ ይህ አልነበረም። ያን ህወሃቶች ከዚህ አሳፋሪ ተግባራቸው የማይመለሱ ከሆነ ወደፊት የምናየው ይሆናል።
በህዝብ ላይ ለተፈጸመው ድርጊት ኃላፊነቱን የሚወስዱት እነማን እንደሆኑ ጠንቅቄ ስለማውቃቸው ጊዜውን ይጠብቅ በማለት የቀድሞ የደርግ ፖሊስ የነበሩ ደርግ ከወደቀ በኋላ አዲሶቹ ገዥዎቻችን ቦታውን ሲሸፍኑ ፖሊስ ከጨዋታ ውጭ ሆኖ ነበር። የኦሊሶችና የቤተሰቦቻቸው ሁኔታ ታይቶ በሕዝብ ላይ ግፍ ያልፈጸሙትን እየተገመገሙ እንዲመለሱ ሲደረግ ከክልል አንድ ሰው ጋር በመሆን የደርግ ፖሊስ የነበሩትን በጎንደር ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲመለሱና የድሮ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ካደረጉት አንዱ ስለነበርኩ ፖሊሶች ሕዝቡን መተባበር ሲገባቸው አግቶ ማዋልና የህዝቡ ስሜት እንዲታፈን ማድረግ ከትናንትናው አለመማር ይሆናል። እንኳን ይህ ውስጡ የነቀዘ ምስጥ እንደበላው አገዳ ባዶውን የቀረ ቅጥረኛ ገዥ ቡድን ማንም ቢሆን የህዝቡን ስሜት በኃይል አፍኖ በመያዝ የሥልጣን ዘመኑን ማራዘም አይችልም።!! «ለዚያውም ህወሃት ህወሃት እኮ እንኳን ዘንቦብሽ እንዲያውም የተባለ ነው።»ከዚህ ላይ አንድ የሚያሳዝነኝ ነገር ቢኖር የጎንደር ሕዝብ ሩህሩ ፤ትዕግስተኛ ፤ አርቆ አሳቢ ፤ለጋስና ተካፍሎ የሚያድር ሕዝብ ነው። ለምሳሌ ዛሬ ተመልሰው መጥተው ሊሰፍሩ ኤርትራውያን ውጡ በተባለበት ወቅት ሁሉም ኤርትራዊ ታፍሶ ፖሊስ መምሪያ ግቢ ውስጥ ነበር። ጎንደሬዎች ኤርትራዊ ወገኖቻቸውን ወደ አዲሲቱ አገር ለመሸኘት የመጡት ድንጋይ ይዘው አልነበረም። እንጀራ በመሶብ፤ወጥ በትልቅ መገፈጅ፤ ጠላ በመንቀልና በገንቦ ተሸክመውና አሸክመው እያለቀሱ ነበር ኤርትራዊ ወገኖቻቸውንና አብሮ አደጎቻቸውን የሸኙዋቸው። ታሪክ ለመተረክ ፈልጌ ሳይሆን በአይኔ ያየሁትና በቦታውም ስለነበርኩ ነው። በአጋጣሚ አንድ የአክስቴ ልጅ የተባበሩት መንግሥታት ውስጥ የሚሰራ ሌረፍት መጥቶ እዛው ፖሊስ መምሪያ ፊት ለፊት አብረን ቆመን የተመለከትነው ሁኔታ ነበር።
አለመታደል ሆኖ የትኛውም ገዥ ኃይል ሲመጣ ለዚህች ታሪካዊ ክ/ሀገር የሚሾሙ ባለሥልጣናት ቀዳሚ ተግባራቸው ዘረፋ ነው። ክፍሌ ዳዲ ይጠቀሳል።መላኩ ተፈራ የጎንደር ተወላጅ ሆኖ የፈጀው የጎንደርን ወጣት ነው። የዛሬዎቹ የህወሃት ነጭ ለባሾችና እንባ ጠባቂዎችም ይህን ሕዝብ የሚመለከቱት በጠላትነት ፈርጀው ነው። በረከት ስሞኦን ( መበርኻቱ ገበረእግዚአብሔር) ወላጆቹ እነማን እንደሆኑ ቢታወቅም ተወልዶ ያደገው ጎንደር ነው። በረከት ግን «ጎንደሬዎች ወሬ እንጅ ሥራ አያውቁም » ብሎ መተቸቱን ከአንድ ለገዥው ቡድን ቅርብ የሆነ ሰው አጫውቶኛል። አቶ በረከት የትኛውን የሥራ እድል ፈጥሮ ነው ጎንደሬዎች ሥራ እንደማናውቅ የከሰሰን? ሥራ ለመያዝ የድርጅት አባል መሆን መመዘኛ ሆኖ በሚሰራበት እንዴት ብሎ?ለማን ሲባል ምን ለማትረፍ? ሰሞኑን የአማራ ክልል ካድሬዎችን ሰብስቦ ስለ አማራው ሥነ-አእምሮና አመለካከት ገለፃ ያደረገው አለምነው መኮንን የተናገረውን በኢሳት ቀርቦ ተደምጧል። ለማረጋገጥ እንደቻልኩት ሁሉም ሰምቶታል። ይህ አሳዛኝ ፍጡር የሰደበው ራሱን ሲሆን የሚገርመው ደግሞ የዚህ የሚንቀው ሕዝብ ክልል ምክትል ሊቀመንበር ሆኖ ነው። አይ ! ነገን መርሳት ሆዳም! ይሏል ይህ ነው። የታደሰ ካሳ(ታደስ ጥንቅሹ)እና የሕላዊ ዮሴፍ፤ የተፈራ ዋልዋ ኮፒ እነሱ አዘውትረው የሚናገሩት ይህን ነበር። ታደስ አንድ ቀን እኔን ለማናደድ የአማራ ደም ቢመረመር ውጤቱ ትምክህትን እናገኛለን ነበር ያለው። እንግዲህ የአማራው ክልል እንደዚህ በመሰሉ ገፈፎች ነው የሚተዳደረው። በቅርቡ አንድ ከዚህ ጋር የሚያያዝ ሰፋ ያለ ጹሑፍ ለማቅረብ እየሰራሁ ስለሆነ ዛሬ የጎንደሩ ሰላማዊ ሰልፉ እንደ 1969ኙና በአባአምሃ ኢዮሱስ ወቅት የፈሰሰው ደም አይነት አለመፍሰሱ ተመስገን ለማለትና ስለተሰማኝ ሁኔታ ለመግለጽ ነው አመሰግናለሁ።
በቀጣይ እስከምንገናኝ በደህና ያሰንብተን።
የኢትዮጵያ ዳርድንበር ላለማስደፈር አንድ እንሁን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘልዓለም በክብር ትኑር!!
maleda times | February 2, 2014 at 8:57 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-3kb
Comment   See all comments

Tuesday, January 28, 2014

ጌዜ መስታወቱ!! ተስፋዬ ገብረአብ ማነው? ቁጥር ሁለት


ማሳሰቢያ፦የእጅ  ጹህፍን  ይንን ሊንክ በመ ጫን  ያንብቡት:http://www.zehabesha.com/amharic/archives/12324

ተስፋዬ ገብረአብ
ውድ አንባብያን፣ ይህ ጽሁፍ ከዚህ ቀደም ከዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ጋር ተስፋዬ ገብረአብን
አስመልክቶ አወጥተን ከነበረው ሪፖርት ጽሁፍ ተከታይ ነው። በዚህ መሰረት ከተስፋዬ ገብረአብ
ጋር አብረን ስንኖር እጄ ላይ ከወደቁትን መረጃዎች መሃከል የመጀመሪያው ጽሁፍ ተከታይ
ይሆናል ብዬ የመረጥኳቸውን ቃል በገባሁት መሰረት ከነማብራሪያቸው አቀርባለሁ።
ለዛሬ የማቀርበው መረጃ ተስፋዬ ገብረአብ እንደ ሸፋን ከሚጠቀምበት የደራሲነት እና
የጋዜጠኘነት ስራ ባሻገር ለማመን በሚያዳግት ይሰራ የነበረውን የወንጀል ድርጊት ፍንትው አድርጎ
ያሳያል።
ከዚህ በታች አባሪ ተደርጎ የተያያዘው በእጅ የተጻፈ መረጃ፣በእጄ ላይ ካሉ መረጃዎች መሃከል
ትኩረቴን የሳበው ነው።እንደምትመለከቱት በራሱ በተስፋዬ ገብረአብ እጅ የተጻፈ ነው።ከሌሎች
መረጃዎች ለየት የሚያደርገው ደግሞ፣እንደሌሎች መረጃዎች በፎቶኮፒ እጄ ላይ የቀረ ሳይሆን፣
ዋናው (ኦርጅናል)መሆኑ ነው። ምክንያቱም በቀጥታ ወንጀል የተጻፈበት ሆኖ ስለታየኝ ነው።ከእጅ
ጽሁፉ ላይ እንደምትመለከቱት፣መኩሪያ መካሻ ከተባለ ግለሰብ ጋር ድብቅ(ህቡእ) ስራ ለመስራት
ጀምረው ነበር።እንደኔ ግምት የኤርትራ መንግስትን ጥቅም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስፈጽማል
ብለው ያሰቡትን ተልእኮ ለመፈጸም አሲረው ነበር፡፡እንደ መረጃው ከሆነ መኩሪያ መካሻ የተባለው
ግለሰብ ከፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ በኋላ ፈርቶ ይሁን ሌላ ባይታወቅም፣ከተስፋዬ ጋር ያለውን
ግንኙነት አቋርጧል።የፒያሳው የቦንብ ፋንዳታ ብሎ የተገለጸው ደግሞ ሌላ ሳይሆን በ2002 እኤአ
በትግራይ ሆቴል ላይ የደረሰው ፍንዳታ ነው።
የእጅ ጽሁፉን ሙሉ ይዘትና ለአንባቢ ይመች ዘንድ የተየብኩትን ይመሳከር ዘንድ እንደሚከተለው
አቅርቤዋለሁ።
አሰሪ መሆንና በቀጥታ ከእሳቱ ጋር መጋፈጥ ልዩነት አላቸው መኩሪያ መካሻ የተባለው ሰው ጥሩ ጀምሮ
ነበረ።ፒያሳ ላይ ቦምብ ሲፈነዳ ከእኔ ጋራ ያለንን ግንኙነት አቁዋረጠ።በጣም ጉዋደኛየ ነበር ለስራው
ስል ሰዋሁት። ጉዋደኛን መሰዋቴ ትልቅ ነገር አይደለም።ህይወታቸውን የሰዉ፣ክቡር ዜጎች ያሉበት ሃገር
ሰው ነኘና። እዚህ ላይ በትክክል ማሰብ እችላለሁ።አስቃቂውን ስሜቴን ግን ለመግለጽ ያህል ነው።
ያሸማቅቁሃል ሲሳካልኝ በደስታ መጠጣት፣ሲከሽፍብኝ በንዴት መጠጣት፣ልምድ አደረግኩት።ደረጀ
ደስታ እራሱ ከገፋፋኝ በሁዋላ መልሶ በኢትኦጵያ የማምን ኢትዬጵያዊ ነኝ ሲለኝ ምን እንደሚሰማ ገምቱት።
ሚኒስትር የነበረው ደስታ ወልደማርያም ጋር ለዘላለሙ ተለያይቻለሁ።እነዚህ ሰዎች ለወያኔ ነግረው ምን
ያስፈጽሙብኝ ይሆን የሚል ስጋት አለብኝ።ያድዋን ወረዳ ያበላሸው ………… የደረሰበትን ታሪክ
እያሰብኩ መሰቃየቴን አልተውኩም።



ከብብቱ ፈልቅቄ ካስቀረዋቸው መረጃዎች ከዚህ በታች እንደምታዩት በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ላይ
የኢትዬ-ኤርትራ ጦርነት በሁዋላ እሱም እንዳለቆቹ እንዳቄመ ነው የምናየው።እስከጦርነቱ መጀመሪያ ድረስ
ግን፣የህወሃት አባልነቱን ግዴታ ለመወጣት በአለቆቹ ታዞ ይሁን በራሱ ተነሳሽነት የአማራንና የኦሮሞን
ህዝብ ለማጋጨት ነበር ስራዬ ብሎ የተያያዘው።አሁን ደግሞ በኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት
ፕሮጀክት ተቀርጾለት የትግራይ ህዝብንም የትኩረታቸው መነሻና መድረሻ አካተው በተቀረው የኢትዬጵያ
ህዝብ ለማስጠላትና ለማሸማቀቅ፣የተስፋዬ ገብረአብን ብእር እንደዋነኛ መሳሪያ እየተጠሙበት እንደሆነ
በግልጽ ማየት ይቻላል። ከላይ እንደገለጽኩት መስሪያ ቤቱ በሃገራችን ህዝቦች መሃል ያለውን መተማመን እና አንድነት ለማትፋት
ፕሮጀክት ተቀርጽለት ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት በዚህ ግለሰብ ኣማካኝነት እየተፈፀመ የከረመው እና
ሊፈፀም እየቴሰረ ያለው ሤራ እንደሚከተለው ይሆናል፥፥
አጠቃላይ የግቡ አላማ የኢትዮጵያን አንድነት ማዳከም ነው፥፥ ስልታዊ አካሄዳቸው ድግሞ አንዱን
ብሄረሰብ ከሌላኛው ጋር እርስ በእርስ እንዳይማመኑ በማድረግ በመሃላችን አንድ ሃገራዊ አጀንዳና እሴት
እንዳይኖረን ማድረግ ነው፥፥
ለዚህ ማጠናከሪያ የሚሆነው፣የአማራ፣የኦሮሞ እና የትግራይ ብሄረሰቦችን ለምሳሌ ያህል ብንወስድ
አንድ የኦሮሞ የዘር ሃረግ ያለው ግለሰብ፣አማራ ከሆነ ግለሰብ ጋር አብረው በጓደኝነት፣በጋብቻ
ሊኖሩ የሚችሉበት የግኑኝነታችው መሰረት አንድና አንድ ብቻ እንዲሆን ነው የሚፈለገው፡፡ ያም
የትግሬ ጥላቻ ነው።በተቀረው ሁለቱ ግለሰቦች የጋራ የሆነ ሃገራዊ አጀንዳ እና እሴት ቀርጸው
ስለዲሞክራሲ፣ፍትህ፣ልማትና የሰብአዊ መብት መከበር እንዲሁም ሌሎች ሃገራዊ አጀንዳዎች
እንዲያግባቧቸው ፈጽሞ አይፈለግም።የወዳጅነታቸው መሰረት አንድ ብቻ እንዲሆን ነው
የሚፈለገው፣እርሱም የትግሬ ጥላቻ ብቻ ነው። በሌላኛውም መአዘን የትግራይና ኦሮሞ ብሄር
ተወላጆች የወዳጅነታቸውና ያብሮነታቸው መሰረት መሆን ያለበት፣የአማራ ጥላቻ ብቻ እንዲሆን
ነው እቅድ ወጥቶለት ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦለት በተግባር ላይ እንዲውል እየተደረገ ያለው።
ይህንን ለምሳሌ አነሳን እንጂ ሁሉም የሃገራችን ብሄሮች በተገኘው አጋጣሚና እድል በዚህ መልክ
በጎሪጥ እንዲተያዩ በማድረግ እንደሰው ወይንም እንደ ኢትዬጵያዊ ማሰብ አቁመን ሳንፈልግ
በመረጥነው የብሄር ማንነታችን ላይ አትኩረን ስንኩላን እንድንሆን የተሸረበ ሴራ አካል ነው።
እዚህጋ በኤርትራ የደህንነትና መረጃ መስሪያቤት ሙሉ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በመታገዝ
የተስፋዬ ስነ-ጽሁፍ የበኩሉን የማናከስ ሚና በመጫወት ሃገራችንን ወደማያባራ ጦርነትና እልቂት
ለመክተት የራሱን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

ሁለት አመት ለሚቆጠር ጊዜ ቤቴ አስጠግቸው ሲኖር ከሚያደርጋቸው የስልክ ልውውጦች
እንደተረዳሁት ከሆነ በተስፋየ ገብረአብ ስም ይወጡ የነበሩ ጽሁፎች በአብዛኛው ማለት ይቻላል
ከኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የፕሮፓጋንዳ መልእክቶች እንደነበሩ ህያው ምስክር ነኝ።
ይህ ማለት ተስፋየ በጋዜጠኝነት ወይንም በደራሲነት ሽፋን የመረጃ መስሪያቤቱ የፕሮፓጋንዳ
ማስተላለፊያ መሳሪያ በመሆን ለኤርትራን ብሄራዊ ጥቅም የሚውል ስራ ይሰራ የነበረ መሆኑን
አስረጂ ነው።ለምሳሌ ከደህንነት መስሪያቤት የላኩለትን ምንም ለውጥ እንዲደረግበት ሃሳብ
ሲያቀርብ፣እነሱም ሃሳቡን ሳይቀበሉት ሲቀሩ በር ዘግቶ በስልክ ሲጨቃጨቅና ሃሳቡ ሲሸነፍ
በተደጋጋሚ መስማቴን አስታውሳለሁ።

እንደ እኔ እምነት ከሆነ ራሱ የኢትዬጵያ መንግስት እያራመደ ያለው የተንሸዋረረና የከረረ የዘር
ማንነትን ብቻ ማእከል ያደረግ የፖለቲካ ስርአት፣ከውጪ ሊመጣ ለሚችል እንዲህ አይነት
የማጋጫት ወይንም ሃገር የማፍረስ ጣልቃገብነት በር እንደሚከፍት ለመተንበይ አዳጋች አይሆንም።

ወደ ነጥቤ ልመለስና ከላይ በጠቀስኩት መሰረት፣አማራን ከተለያዩ የሃገሪቱ ብሄሮች ጋር እንዴት
ሲያላትም እንደነበረ፣ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ጋር በክፍል አንድ ሪፖርታችን ላይ በሰፊው
ሄደንበታልና አሁን አልመለስበትም። ከዚህ በታች ደግሞ የትግራይ ብሄር አባል በሆኑ ግለሰቦች ላይ
ማህበራዊ ፤ የስነልቦና የአካል ጥቃት መፈጸሙ፤ የሱ መጽሃፍ ስኬት ውጤት እንደሆነ ለኤርትራ የመረጃና ደህንነት መስሪያቤት የቅርብ ተጠሪው ለሆኑት አቶ ዓለም እንዲህ በማለት በጽሁፍ
ያስተላልፍ እንደነበረ ከሚከተለው የፋክስ መልእክት ረቂቅ (ድራፍት ) መረዳት እንችላለን፡



የአምስተርዳም በአል ላይ አንዱ የመለስ ደጋፊ የመለስን ፎቶግራፍ ለብሶ ሲገባ፣እኔ እዚያው
በአሉ ላይ ነበርኩ እንደ እንደማርያም ጠላት እየተቀባበሉ ቀጠቀ።የአምስተርዳም በአል ላይ
የተፈጸመ ሌላ ታሪክ ልንገራችሁ።አንዱ ወጣት ትግርኛ ይዘፈን፣ትግርኛ ብሎ ይረብሻል።ቢራ
ጠጥተው ሞቅ ያላቸው ወጣቶች እየተንደረደሩ ያንቁታል፣ልጁ ክጃቸው ያመልጥና መሮጥ
ይሞክራል።ተከታትለው ሲይዙት ኤርትራዊ ነኝ ብሎ ይጮሃል።

ባለፈው እሁድ የልደት በዓሌን አከበርኩ።42ዓመት ሆነኝ።አዲስ አበባ ተወልዳ ያደገች፣አንዲት
የትግራይ ልጅ ጉዋደኛ አለችኝ።ደቡብ አፍሪካ ፕሮቶሪያ ዩኒቭርሲቲ ለትምህርት መጣታ ሳለ ነበር
የተዋወቅኩዋት። አሁን አዲስ አበባ ተመልሳለች።ሰንገናኘ የልብ የልባችንን እንጫወታለን፡፡እናም
ስንጨዋወት እንዲህ አለችኝ።እናቴ እንደቀድሞዋ የትግሬ ሹሩባ መሰራት ትታለች፣በወር አንድ
ግዜ በሹሩባዎቹዋና በወርቁዋ ማጌጥ ትወድ እንዳልነበረች፣አሁን ሰርግ ላይ እንኩዋን፣ሹሩባ
መሰራቱ አሳቁዋታል።ሰው ሁሉ የሚጠቁዋቆምብኝ ይመስለኛል ብላ ነገረችኝ ትላለች።

ከሰጠሁት ጥቆማ በላይ ግን በሁለቱ መጽሃፍት- እነዚያን ጥቆማዎች ለማድረግ በተደረገ
እንቅስቃሴም።…… እነዚህ ሁለት መጽሃፍት (የጋዜጠኛው ማስታወሻ እና የደራሲው ማስታወሻ )
ለመጻፍ ችያለሁ።እነዚህ ሁለት መጽሃፍት ያስገኙት የፖለቲካ ፋይዳ በአንድ ባለሙያ ማስጠናት
ብቻ በቂ ነው።
ያለፈውን ገድል በማንሳት ጉራ መንዛትም ብቻ ግን ዋጋ የለውም።ወደ ሚቀጥለው ተግባር
መሸጋገር ያስፈልጋል።

ከግማሽ ሚልዬን በላይ ህዝብ እነዚህን መጽሃፍት በማንበብ ከፍተኛ ግንዛቤ አግኝቶአል።


ተስፋዬ ገብረአብ ስነ ጽሁፍን እንዴት ለፖለቲካዊ አላማው እየተጠቀመ እንደነበረ በራሱ እጅ
ጽሁፍ እንደሚከተለው ያብራራል።

ለዓለም፣
አንዳንድ ማስታወሻዎች፣

የዚህ መጽሃፍ ፋይዳ ከቀዳሚዎቹ ሁሉ የላቀና ልዩ ትኩረት የሚያሻው ነው።የነዚህ ማስታዎሻዎች
ተከታታይ መጽሃፍትን ሃሳብ የጠነሰስከው እኔም ኢትዬጵያዊ ሆኜ ድራማ እንድሰራ ያዘዝክ (ሰርዞት)
ያግባባህኝ ራስህ (አበበ)በመሆንህ ይህ ፕሮጀክት የመስሪያ ቤታችን የስራ አካል ተደርጎ እንዲታይ
ምኞት አለኝ።ምክንያቱም የተጀመረ ፕሮጀክት እንደመሆኑ፣ልገፋበት የግድ ነው።ከኢትዬጵያ ህዝብም
ከፍተኛ ግፊት አለብኝ።ቢያንስ ከአራት መቶ ሺህ በላይ ኢትዬጵያውያን አንባቢዎች እንዳፈራሁ
ይገመታል።እነዚህም አንባቢያን የከተማ ሰዎችና ለፖለቲካው ቅርብ የሆኑ እንደሆነ ማረጋገጥ ይቻላል።

አሁን የሆላንድ የመኖሪያ ፈቃድ አግኝቻለሁ።ቀጣዩን መጽሃፍ እዚሁ ሆላንድ ሃገር ሆኜ ለመጻፍ
እየሞከርኩኘ ነበር።እየሰራሁትም ነው።ሆኖም እየተሳካልኝ ነው ማለት አልችልም።የተሳካ ስነ-ጽሁፍ
ለመስራት ያካባቢ ሁኔታ ወሳኝ ነው።የጋዜጠኛው ማስታወሻ እና የደራሲው ማስታወሻን የሰራሁት
አስመራ ሆኜ መሆኑን ታውቃላችሁ።የስደተኛን ማስታወሻ ሆላንድ ሆኜ መስራት አልቻልኩም።መስራት
ካለብኝ ኤርትራ መመለስ አለብኝ።ኤርትራ ከተመለስኩ ያገኘሁት የሆላንድ ዜግነት ሊቋረጥ ይችላል።
ምክንያቱም በሆላንድ ህግ መሰረት ከሆላንድ ውጭ መቆየት የሚፈቀድልኝ፣ለሶስት ወር ብቻ ነው።
ጥቅምና ጉዳቱን ስመዝነው ግን፣ሆላንድ ላይ ያገኘሁት ዜግነት ተሰርዞ ወደ ኤርትራ ብመለስ የተሻለ
ነው።ምክንያቱም እኔ ሆላንድ ላይ ከመቆየቴም በላይ የስደተኛው ማሰታወሻ መታተም፣ፖለቲካዊ
ፋይዳው የላቀ ነው።ይህን ሃሳብ ያቀረብኩት በርካታ ጥቅምና ጉዳቶችን ግራና ቀኝ ተመልክቼ ነው።

ከላይ ያቀረብኩት ሃሳብ፣ለማጠቃለል ያህል።መንግስት የሰጠኝን የመኖሪያ ፈቃድ ለአንድ ዓመት ያህል
ወደውጭ እንድቆይ የሚፈቅድልኝ ከሆነ እሞክራለሁ።ካልተቻለ የመኖሪያ ፈቃዳቸውን መልሼላቸው
ጥቅምት 15፣2010 ዓም.ላይ የመመለሻ ትኬቴን በመጠቀም ወደ ኤርትራ እመለስ ዘንድ ሃሳብ
አቀርባለሁ።ለዚህም የናንተ ውሳኔ ያስፈልጋል።

ወደ ኤርትራ ከተመለስኩ በኋላ መስሪያቤታችን ገለል ያለ ቦታ ሆኜ 44 ምእራፍ 600 ገጾች ያሉትን
የስደተኛው ማስታወሻ ጽፌ፣መጨረስ እንድችል መስሪያቤታችን አንድንድ ሁኔታዎችን
እንደሚያመቻችልኝ እመኛለሁ።እነዚህ ነገሮችም፣ለአንድ ዓመት ጊዜያዊ መኖሪያ ቤትና የመጻፊያ ቢሮ
ናቸው።በ2011 የሚታተመው ይህ መጽሃፍ ከቀዳሚዎቹ ሁሉ የላቀ እንደሚሆን ቃሌን አምናችሁ
ይህን ታደርጉ ዘንድ እመኛለሁ።ሻቢያ በቀጣይ (መስሪያቤታችን)ከሚያስመዘግባቸው የስነልቦና
ጦርነቶች ሁሉ ይህ ቀዳሚ ስፍራ እንደሚኖረው ለማረጋገጥ እጥራለሁ።


የሆነው ሆኖ የሀገሬ አንድነትና የህዝቤን የፍቅር ሰንሰለት ለመበጠስ፣ የኢህአዴግ አስተዳደር ባነበረው
የዘውግ ፌድራሊዝም ሾልከው የሚገቡትን ሴራኞችን ማጋለጥ የኢትዮጵያዊነት ግዴታዬ ነውና በቀጣዩም ሌሎች
ያገኛኋቸውን መረጃዎች በተከታታይ አቀርባለሁ፡፡

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥበቃ ለዘላለም ትኖራለች!!!
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/12324

Saturday, November 23, 2013

ኦባንግ – ከዓለምአቀፍ ተቋማት ጋር እየሠራሁ ነው አሉ የሳዑዲ ልዑል አንጋቾቻቸውን አወደሱ


obang-o-metho-hearingበሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ፈር የለቀቀ አስነዋሪ ግፍ ዓለምአቀፍ ይዘት እንዲኖረው ለማድረግ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ጋር እየሠሩ መሆናቸውን አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ተናገሩ፡፡ የሳዑዲ ልዑል ሰብዓዊነት የረገፈበትንና በግፍ የተሞላ የወሮበላ ተግባር የሚፈጸምበትን አሰቃቂ ተግባር የሚከናውኑትን አንጋቾች አሞካሹ፡፡
ያለ አንዳች ልዩነት ኢትዮጵያውያን በኅብረት ድምጻቸውን በማሰማት እየተቃወሙት ያለውን ኢሰብዓዊ ተግባር አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ይፋ ከሆኑት በተጨማሪ ድብቅ መረጃዎች እየተሰበሰቡ መሆናቸውን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አስታውቀዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ የጋራ ንቅናቄው ከዓለምአቀፍ የመብት ተቋማት ጋር በቅርበት እየተሰራ ስላለው ዝርዝር ጉዳይ ግን ከሁኔታው ምስጢራዊነት አኳያ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
“አልዘገዩም” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም “አኢጋን ችግር በተከሰተ ቁጥር የሚቋቋምና የሚፈርስ የዕቁብ ይዘት ያለው ድርጅት አይደለም፡፡ ወይም እሣት ሲነሳ ድምጽ እያሰማ እንደሚከንፍ የእሣት አደጋ መኪና የሚመሰል ድርጅት አይደለም” በማለት የጋራ ንቅናቄውን የተጠና አካሄድ በመጠቆም የመለሱት አቶ ኦባንግ ይህ ችግር እንደሚከሰት አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡
ችግሩ አስቀድሞ እንደሚከሰት ቢታወቅም ምላሽ የሚሰጥ ብቃት ያለው አካል ባለመኖሩ አንገት የሚያስደፋና ኃፍረት የሚላብስ፤ “አገር አለኝ ወይ?” የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ በኢትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶና ታይቶ የማይታወቅ ኃፍረት ሊደርስብን ችሏል፡፡ “ይሁን እንጂ” አሉ ኦባንግ “ይህ መራር ዜና ከተሰማበት ሰዓት ጀምሮ የጋራ ንቅናቄው የበኩሉን” ሲያደርግ መቆየቱን አመልክተዋል፡፡
“ከተለያዩ ዓለምአቀፋዊ ተቋማት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች፣ አግባብ ካላቸው መንግሥታዊ አካላትና በተለያየ ደረጃ ላይ ከሚገኙ የሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግረናል” በማለት አቶ ኦባንግ ተናግረዋል፡፡ ለዓብነት ያህልም የሳዑዲ ም/ጠ/ሚ/ር እና የመከላከያ ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚ/ር፣ የፍትሕ ሚ/ር እና ሌሎች ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን የመንግሥት መ/ቤቶችን ጨምሮ በአውሮጳና በሰሜን አሜሪካ የሚገኙትን የሳዑዲ ኤምባሲዎችን እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ኮሚሽነርን፣ የአፍሪካ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ACHPR)፣ ወዘተ ማነጋገራቸውንና በየደረጃውም ምላሽ ማግኘታቸውን አመልክተዋል፡፡
በመላው የመካከለኛው ምስራቅ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ዕረፍት የሚሰጥ እንዳልሆነ የጠቆሙት “ጥቁሩ ሰው” ሳዑዲ ካላትና ከምትከተለው “የበርህን ዝጋ ፖሊሲ” አንጻር በአካል በቦታው ላይ ከመገኘት ይልቅ አቅም ካላቸው ዓለምአቀፋዊ አካላት ጋር በአፋጣኝና በቅርበት መሥራቱ ድርጅታቸው የወሰደው አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የሎጂስቲክሱ ጉዳይ መስመር ሲይዝም የጋራ ንቅናቄው ከዚህ በፊት በየአገራቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ ሲያስፈጽምበት የነበረውንና በውጤታማነቱ የሚታወቀውን አማራጭ እንደሚተገብር ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ኢህአዴግ አገርን እንደሚያስተዳድር ድርጅት በዜጎቹ ላይ እየደረሰ ያለውን አስነዋሪ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ አለመመከቱ ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ ይህንኑ አስመልክቶ አቶ ኦባንግ ሜቶ “ወገኖቻችንን ድንበር በማሻገርና ኤጀንሲ ከፍተው ወደ አረብ አገራት ሲልኩ የነበሩት ሁሉ ሕግ ፊት ቀርበው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ የተለያዩ ተግባራት” እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
alamudi-ሼክ መሐመድ አላሙዲ የሠራተኛ ኃይል ወደ ሳዑዲ እንዲላክ ከኢህአዴግ ጋር በይፋ ስምምነት ማድረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ ከሚፈልጉበት ክልል መሬት ለመውሰድ፣ ከሚፈልጉበት ባንክ ኮሪደር ገንዘብ ለመበደር ገደብ የሌላቸውና በሞቀበት ሁሉ ባለመጥፋት በጀት መድበው በሚያስተዳድሯቸው ሚዲያዎች እንዲሁም አንደበታቸውን በሙስና ላሰሯቸው ባለሥልጣናት “ኢትዮጵያዊ ነኝ” እያሉ በተገኙበት ቦታ ሁሉ ለሚዲያ ፍጆታ የሚደሰኩሩትና ግጥም የሚያስደረድሩት ሼክ መሐመድ አላሙዲ፣ “ወገኔ” የሚሉት ሕዝብ በአባታቸው አገር ወሮበሎች ሲያልቅና ሲጨፈጨፍ ዝም ማለታቸው ኢንቨስትመንቶቻቸውን ጥያቄ ውስጥ ከትቷል፡፡
አንዳንዶች እንደሚሉት ይህ አሰቃቂ ድርጊት መስመር ለቅቆ ከመውጣቱ በፊት የሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ከርስ እንዲሞላ በኢትዮጵያ የተቋቋመው ሳዑዲ ስታር ኩባንያ በገንዘብ እጥረት ሊዘጋ እንደሚችል መዘገቡ የሚታወስ ነው፡፡ በወቅቱ ሪፖርተር ባወጣው ዘገባ ሳዑዲ ስታር በኪሣራ ወደ መዘጋት መድረሱ የኩባንያው “ባለቤት የሆኑትን ሼክ ሙሐመድ አል አሙዲንና የሳዑዲ ዓረቢያን ስም የሚያጎድፍ ከመሆኑም ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ እስኪታክት የተወራለት ይህ ፕሮጀክት መና መቅረቱ ሁለቱን አካላት በሕዝቡ ዘንድ ለከፍተኛ ትችትና ወቀሳ እንደሚያጋልጣቸውም” ጠቁሞ ነበር፡፡
mohammed bin nayef
ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ
በአሁኑ ጊዜ “ሕገወጥ ናችሁ” በሚል ሰብዓዊነት የጎደው እርምጃ እየተወሰደባቸው ያለው የበርካታ አገራት ዜጎች በተለይም ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጸመውን ሰቅጣጭ ተግባር ሕገወጦችን የማባረር “ዘመቻ” በማለት ያቃለሉት የሳዑዲው አገር ውስጥ ሚ/ር ልዑል ሞሐመድ ቢን ናይፍ ወንጀለኛ ሬንጀር ለባሾችን፣ ፖሊሶችንና ወሮበሎቹን ሸባቦች አደፋፍረዋል፡፡ “ዘመቻው ይቀጥላል … በተወሰነ ጊዜ የተገደበ አይደለም” በማለት “እስክንጨርስ እንጨርሳችኋለን” የሚመስል የማፊያ መሪ መሰል መልዕክት ለአንጋቾቻቸው አስተላልፈዋል፡፡
አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን በሕጋዊነት የሚኖሩትም ጭምር በሳዑዲ ያለው ሁኔታ አሳሳቢነት ወደፊት ችግር ውስጥ ሊከትታቸው እንደሚችል በመገመት ወደ አገራቸው መመለስ ይፈልጋሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ለከፍተኛ ሰቆቃ የተጋለጡት ኢትዮጵያውያን “ቤት አለን ቤታችን መልሱ” እያሉ የሰቆቃና የድረሱልን ጥሪ በሚያስተላልፉበት ወቅት ሰብዓዊነት የጎደላቸው የኢህአዴግ መሪዎች ይህ ነው የሚባል አፋጣኝ ምላሽ መስጠት አለመቻላቸው “በእርግጥ ኢትዮጵያውያን አገር አላቸው?” ብሎ የሚያስጠይቅ እንደሆነ በርካታዎች የሚጋሩት ነው፡፡
አቶ ኦባንግ በበኩላቸውም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአንድ ሳምንት ሥራውን አቋርጦ እንኳን ቢሆን ስደተኞቹን ባፋጣኝ የማመላለስ ተግባር መፈጸም ይገባው ነበር በማለት ቁጭታቸውን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ህይወታቸው እየተቀጠፈ “3ሺህ ዛሬ ገቡ … ድምሩ 10ሺህ ሆኗል …” የሚል የሞላ ጎደለ ቁማር ዓይነት ጨዋታ በትዊተር መጫወት የቴድሮስ አድሃኖምን ዘመነኛነት ሳይሆን ለሰውልጅ ህይወት ያላቸውን ደንታቢስነት የሚያሳይ መሆኑን ሁኔታው ያስቆጣቸው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አቶ ኦባንግም “ቤቴ መልሱኝ” ብሎ ለሚለምን አንድ ዜጋ የተከፈለው ተከፍሎ ትራንፖርት በማቅረብ ክቡር ህይወትን በአስቸኳይ ለመታደግ አለመቻል ለትውልድ የሚተላለፍ የታሪክ ጠባሳ መሆኑን በአጽዕኖት ተናግረዋል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Monday, November 11, 2013

በሳኡዲ አረቢያ የሚፈጸመው ግድያ እና የኢትዮጵያ መንግስት ሴራ



999410_10201428110199302_1866404023_n
ባሳለፍነው ወር ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት በሳኡዲ አረቢያ የሚጓዙ ስደተኞችን አግደናል ሲል ለመገናኛ ብዙሃኖች መጠቆሙ የሚታውስ ሲሆን ያንን ተከትሎም ሆነ ከዚህ ቀደም ይደረጉ የነበሩ አንዳንድ ሁኔታዎችን ተመልክቶ አንዳንድ ምልከታዎችን ለመጠቆም ወደድን ።
የኢትዮጵያ መንግስት በሃገር ውስጥ የሚገኙትን ለኡምራ ጉዞ በሚል ፈቃድ በማግኘት እስከ አረብ አገራት ድረስ በመደለል ስራ እናስገባቿለን በማለት ሴት እህቶቻችንን እና ወንድሞቻችንን ጉዞአቸውን ወደዚያው እንዲያመሩ አቅጣጫቸውን እየቀየሩ ህብረተሰቦችን ወደ አልተፈለገ ጉዳት ውስጥ ሲጥሉአቸው እንደነበር በተለያዩ ጊዜያቶች ይነገሩ የነበሩ የረጂም ጊዜ ታሪኮች ናቸው ።ይባስ ብሎ እነዚህ ደላላዎች በሃገር ውስጥ ተቀምጠው ከአሰሪዎቻቸው ጋር በመነጋገር ገንዘብ ወደ ደላላዎቻቸው ብቻ እንዲላክ እንጂ ለሰራተኞቹ በእጃቸው እንዳይደርሳቸው በማድረግ የብዙሃኑን የድሃ ቤተሰብ ልጆች ደም ሲነጥቁ መክረማቸውም ሌላኛው ግልጽ ዘረፋ የተካኑት ግለሰቦች መሆናቸውን ማንም ሰው የሚረዳው ጉዳይ ነበር ።ሆኖም እንዲህ አይነቱ ክስተት ተፈጠረ ሲባል እኛ አናውቅም አሰሪዎቻቸውንም ሆነ በአረብ አገራት የሚገኙትን ደላላዎች አናውቅም በማለት የብዙዎችን ደም ደመ ከልብ ያደረጉት እነዚሁ የግል አስጎብኝ ድርጅት ኖሮአቸው ዜጎቻቸውን በህገወጥ እና በቀላሉ ልጥቅም ብለው በአረብ አገራት ላሉት ባለሃብቶች የሸጡአቸው ዜጎች መሆናቸውን ሳልገልጽ አላልፍም ።ለዚህም ሁሉ ጥፋት ተጠያቂ እነዚህም ወገኖች በህገ ወጥ ስራቸው ብቻ ሊጠየቁበት የሚገባው ዋነኛው ጉዳይ ሆኖ ሊታይ ይገባዋል ።
ከዚህም ባሻገር ለዘመናት እንዲህ ዜጎቻችንን ለርካሽ ባርነት የላኳቸውን ወገኖች ዘወር ብለው ያላዩአቸውን እንዚህን ደላላ ተብዬዎች ከባለፉት ሁለት አመታት ጀምሮ መንግስት እና እንዲሁም ጥቂት የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ባለስልጣናት ደጋፊ የሆኑ ሰዎች ይህንን ስራ በህጋዊ መልኩ አድርገን እንሰራለን በማለት በወር ወደ 45.000 የሚጠጉ የቤት ሰራተኞችን እንልካለን በማለት ከባለሃብቱ ሼክ መሃመድ አላህሙዲ ጋር የሚሰራ አንድ ትልቅ የጉዞ አስጎብኝ ወኪል በመፍጠር ለሳኡዲ መንግስት ሴትም ሆነ ወንድ ሰራተኞችን ሊያቀርቡ እንደሚችሉ መፈራረማቸውን በይፋ መግለጻቸውን እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህገ ወጥ የሚሰሩትን ድርጅቶች ቀስ በቀስ እያመነመኑ እንዲዘጉ ማድረጋቸው የሚታወቅ ሲሆን ..ለህዝባችን በተወሰነ መልኩ እፎይታን ቢሰጥም በእጅ አዙር እራሳቸው ስራውን ሊሰሩት ማሰባቸውን እና ሃሳቡን መቀልበሳቸው በሰፊው የተጋለጠባቸው ግን አሁን መሆኑን ሁሉም ሰው  ተረድቶታል ።መንግስት በህጋዊ መንገድ አቀርባቸዋለሁ ያላቸውን ሰራተኞች እራሱ ጉዳዩን ፈጽሞ እራሱ ልኮ ጠበቃ ነኝ ብሎ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘው ቆንጽላ በጥቃታቸው ጊዜ ጉዳታቸውን እንዲሰማላቸው አደርጋለሁ ሲልም መናገሩ አይዘነጋም ።
ዛሬ ደግሞ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ  በቃል አቀባይነታቸው መሰረት
በሳዑዲ በመከራና ስቃይ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንን አስመልክቶ የመንግስት ቃል አቀባይ  የተባሉት የቁጭ በሉ ሰው ዲና ሙፍቲ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፦”እየተባረሩ ያሉት ህጋዊ ያልሆኑት ናቸው” ብለዋል ተናግረዋል ።ዲና  በሌላም በኩል  ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ፖሊሶች ስለመገደላቸው የተረጋገጠ ማስረጃ እንደሌላቸው አስረግጠው ገልጸዋል  ሆኖም የሃገሪቱ መንግስት በመገናኛ ብዙሃኑ የተገደሉትን ዜጎች እያሳየ መዋሉን ሲ ኤን ሲ የተባለው የቻይና ቴሌቪዥን ሲያሳይ ቆይቶአል ። ሆኖም የ ዲና ሙፍቲ አነጋገር የሁሉንም ቀልብ ስቦአል ምክንያቱም የሃገሪቱ ተወካይ ሳይሆኑ የሳኡዲ ቃል አቀባይ መስለው መታየታቸው ነው ።
የዲና ሙፍቲ ጉዳይ ወደ ኋላ ተወት እናድርገው እና አቶ ቴዎድሮስ አድሃኖም በሰሞኑ በተጠመዱበት ቲዊተር ስለ ህዝቦቻቸው ሲናግሩ ከአረብ መንግስታቶች ጋር በመምከር ላይ እንዳሉ እና መፍትሄ ሊያመጡ እንደሚችሉ ገልጸዋል ።በትላንትናው እለትም በመንግስት ሃይሎች የሚመራው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም እንደዚሁ ጅብ ከሄደ ጩኸቱን አስምቶአል ።
ከ16500 በላይ ኢትዮያውያኖች በመካ አቅራቢያ ፣በየመን ዳር ድንበር እና እንዲሁም በሳኡዲ አረቢያ ከተማ በሚገኙ እስርቤት ውስጥ ተጉዘው በእስር ስቃይ ላይ እየማቀቁ ይገኛል ።እንደ ሃገሪቱ ናሽናል ቴሌቪዥን ዘገባ ከሆነ እያንዳንዱ እስረኛ ከ500 እስከ 1000 የአሜሪካን ዶላር የሚደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል ይህንን የማይፈጽም ከሆነ ደግሞ እስሩን ጨርሶ ሊፈታ እንደሚችል እና ዳግመኛ ወደዚያች ምድር እንዳይመጣ በሚያደርግ የአሻራ ፊርማ አስወጥተው ሊያባርሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል ። ታዲያ ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው ከኢትዮጵያ መንግስት በተሰጠን  ትእዛዝ ነው ብለው ተናግረዋል የሚሉ መረጃዎች ከወደ ሳኡዲ እየተሰማ ይገኛል ፣ሆኖም ግን ይህ ምን ያህል እውነታ እንደሆነ ማረጋገጫው ባይኖረኝም ይህንን የጻፈውን ብሎግ ግን ማቅረብ መቻሌን ውሸታም አያሰኘኝም ስለዚህ ሙሉውን እንዲህ ይነበባል
ከዚህ ቀጥሎ ከክሊክ ሃበሻ የተዘገበውን ዜና አንዲህ ተቀናብሮ የተቀመጠ ሲሆን እኔም በዚህ መልኩ  ጽሁፉን አስቀምጠው እና ከዚያም ሊንኩን አያይዤ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ ። “ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥ ኢትዮጵያውያን እንዲያዙ የተስማማበት ሰነድ አለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
 | 10 בNovember 2013 | 0 Comments
በሪያድ የዛረው ሰልፍየሚመጣውን አደጋ በመፍራትተበትኗል::
“ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥኢትዮጵያውያን እንዲያዙየተስማማበት ሰነድአለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
አምስተኛ ቀኑን የያዘው የሳኡዲጸረ ኢትዮጵያውያን ዘመቻእንደቀጠለ ሲሆን ሁኔታዎችንለመፍታት የተደረጉ ጥረቶችከዚህ
ቀደም የኢትዮጵያመንግስት እና የቆንስላውዲፕሎማቶች በሰርኡት ስህተትመስመር ሊይዝ አልፈለገም::
እንደ ሳኡዲ ባለስልጣናትአነጋገው የውጪ ጉዳይሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም ባደረጉት ጉብኝት ሃገራቸው ህገወጥ ኢትዮጵያውያንን እንዲያስወጣ እና በምትኩ40,000 ህጋዊ ስደተኞችን እንደሚልኩ የፈረሙበትን ማስረጃ ይዘዋል::
በሪያድ መንፉሃ ወደ ሃገራችን ስደዱን በሚል መንፉሃ ባንክ አልራጅህ አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያውያን መንግስትየወሰደውን እርምጃ ተቃውመው ሰልፍ መውጣታቸው ተሰማ። እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ መሰረት በሰልፈኞችበተወረወሩ ድንጋዮች አንድ የሳውዲ ዜጋ መሞቱንም ዘግቧል።
እነዚሁ በነዋሪዎች ድብደባና በደል የደረሰባቸው ኢትዮጲያውያን ወደ ሪያድ ኢምባሲና ኮሚኒቱ መስሪያ ቤትበእግራቸው ያመሩ ሲሆን መንፉሃ አካባቢ የቀሩት ከፖሊስ ጋር ባደረጉት ግጭት አንድ የፖሊስ መኪናእንደተሰበረ የአይን እማኞች ገልጸውልኛል።http://www.clickhabesh.com/?p=103630
ታዲያ እንዲህ ከሆነማ ሴራውን የጠነሰሱት የራሳችን ወገኖች ከሆኑ ለዚህም ተጠያቂው እራሳቸው ስለሆኑ ፣በወጥመድ ውስጥ እራሳቸውን አሾልከው ላለማስገባት ባደረጉት ጥረት ሸፋፍነው ማለፍን ስለፈለጉ የህዝባቸውን ሰቆቃ እያዩ ዝም ማለትን መርጠዋል ፡፤ይህንንም ሰቆቃ እና ግፍ ግድያ እንዲሁም የሴቶችንም ሆነ የወንዶችን አስገድዶ መደፈር እንዲመጣ ያደረጉት እንዚሁ ጨካኝ የሆኑ ገዢ መደቦቻችን ናቸው ማለት ነው። በነገራችን ላይ በመካ መዲና አካባቢ የተወሰዱት እስረኞች በሙሉ ፣የታሰሩት ወገኖች በግብረ ሰዶማውያን በታሰሩበት እስርቤት እንደሆነ ለመጠቆም እወዳለሁ ።
ይህ ቦታ ከፍተኛ ሙቀት ያለው አካባቢ ከመሆኑ የተነሳ የሰው ልጆችን ለመቅጣት ሆን ተብሎ የተዘጋጀ እና ማኛውም ሰው በተፋፈነ ክፍል ውስጥ አይደለም ለቀናት ለሰአታት መቀመጥ የማይችልበት እስርቤት ሲሆን ከዚህም ባሻገር የሚጠጣው ዉሃ ከፍተና ጨዋማ የሆነ ከመሆኑም በላይ ስውነትን ለመላላጥ እና ለተለያዩ ጉዳቶች ሊያደርስ የሚችል መሆኑን ያገኘኋቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ ።ይኅንን ስቃይ እና መከራ ለምን ዜጎቻቸው እንዲጋፈጡት ፈለጉ ፣መንግስት እንዲህ አይነቱን የክፋት ወንጀል ለምን በህዝቦቹ ላይ መፈጸም አስፈለገው ፣ለምንስ በስደት ያሉት ወገኖች ላይ አነጣጠረ የሚለው ምላሽ ።
ዋነኛው ምክንያት በህገወጥ ገቡ የተባሉት ወገኖች በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘውን ክፍት የስራ ቦታ ስለሚሸፍኑት መንግስት በህጋዊ መንገድ አቅርባቸዋለሁ ያላቸው ሌሎች ዜጎቹን ስራ አጥተው እንዳይሰቃዩበት ስጋት ስለያዘው እና ፣አዲስ የሚጀምረው የጉዞ ሂደት እንዳይደናቀፍበት ቅድመ ጥንቃቄ ለመውሰድ ያስችለው ዘንድ ህጋዊ አልሆኑም ያላቸውን ህዝቦቹን በግዳጅ ከሳኡዲ መንግስት ጋር በመተባበር እንዲያስወጡ መምከሩ ግድ ሆኖ ስለታየው ያንን ሃላፊነት እራሱ ላይ መሸከምን ችሎአል ።ለዚህ ሲባል የሳኡዲ መንግስት በንጹሃን ህዝቦች ላይ ጥቃትን ፈጽሞአል መንግስትም ይህንን አላየሁም ሲል ድፍን አድርጎ የገለጸ ሲሆን በትላንትናው እለት በቴሌቪዝን የአየር ሰአት ላይ ለማረጋገጥ እንጥራለን ሲል ቃሉን ሲያጥፍ ተሰምቶአል ።
እንደ ማጠቃለያ ...መፍትሄው በሃገር ውስጥም ሆነ ተለያዩ አገራት የምንገኝ ዜጎች የህዝቦቻችንን መብት ለማስከበር በምናደርገው ጥረት ማናችንም በአለን ሃይል ተጠናክረን በመምጣት የህዝቦቻችንን መብት ማስከበሩን ግፊት በማድረግ በአረቡ አለም ላይ ጫና እንዲደረግ መጠየቅ እና መምከር ያስፈልገናል ከዚያም ባሻገር በሳኡዲ አረቢያ ኢምባሲ ቅርንጫፍ ቢሮዎችም ሆነ ቆንጽል ስህፈት ቤቶች በመገኘት ድምጻችንን እናሰማለን ከዚያም ቀጥሎ የዚህን አድሃሪ የሆነ መንግስት ሴራ ማጋለጡም ቢሆን ለጉዳት የሚዳርገን አይመስለኝም እና ሁላችንም ለህዝቦቻችን ቅድሚያ በመስጠት የንጹሃኖችን ህይወት እናትርፍ እያልኩኝ እለያችኋለሁ ።ስለያችሁ በአሜሪካ የሚገኙትን ሴናተሮች እና አገረ ገዢዎችን ኢሜል አድራሻ አያይዤ ሳቅርብላችሁ ሁላችሁም ጩኸታችሁን በኢሜሎቻቸው ላይ ያድርሱአቸው የሚለው የመጨረሻው የልመና ቃሌ ነው ሰላም ያገናኘን ።ዘላለም ገብሬ ከማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ።
maleda times | November 10, 2013 at 9:11 pm | URL: http://wp.me/p2gxmh-2sc
Comment    See all comments

Sunday, September 1, 2013

ሰላማዊ ትግልን የሚገድብ ህገወጥ መመሪያ ተግባራዊ






የአዲስ አበባ መስተዳድር ካቢኔ በተለይ የአንድነት ፓርቲን ህዝባዊ ንቅናቄ ለማፈን የሚያስችል አዲስ የሰላማዊ ሰልፍና የሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ መመሪያ በማዘጋጀት በህገወጥ መንገድ ተግባራዊ ማስደረጉ ታወቀ፡፡

ካቢኔው ያፀደቀው አዲሱ መመሪያ አንድነት ፓርቲ በመላ ሀገሪቱ እያደረገ ያለውን ስኬታማ ህዝባዊ ንቅናቄ ግምት ውስጥ የከተተ እንደሆነ ማንነታቸው እንዲገለፅባቸው ያልፈለጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ ኃላፊ ለአንድነት ፓርቲ አመራሮች ገልፀዋል፡፡ የፖሊስ ኮሚሽን ኃላፊው እንደሚሉት ነሃሴ 10 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ካቢኔ የፀደቀውና ለኮሚሽኑ የተላከው መመሪያ ከሕዝብ ፊርማ ለማሰባሰብ፣በራሪ ወረቀት ለመበተን፣ በማይክራፎን ለመቀስቀስና ፖስተር ለመለጠፍ ውስብስብና የተለያዩ አካላትን ፍቃድ ማግኘትን የግድ የሚል ነው፡፡ ሃላፊው “መመሪያው በተለይ የአንድነት ፓርቲ እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ውጤታማ እንይሆን በችኮላ ተግባራዊ የተደረገ ነው፡፡” በማለት ጨምረው አስረድተዋል፡፡
የመመሪያው አወጣጥ ህገወጥነት እንደተጠበቀ ሆኖ መመሪያው በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ሳይወጣና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም ሳይሰራጭ፤ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ህገወጡን መመሪያ እንዲያስፈፅም ከአዲስ አበባ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ትእዛዝ መተላለፉ በኢትዮጵያ የህግ የበላይነት እንዳበቃለት የሚያሳይ ነው፡፡

የመመሪያው ህገወጥነት አሳሳቢ በመሆኑ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የፓርቲው ዋና ፀሀፊ አቶ አስራት ጣሴ ከአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ግርማ ካሳና ከኮሚሽኑ 3 ከፍተኛ ሀላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ህገወጡን መመሪያ ፖሊስ ኮሚሽኑ እንዲያስፈፅም መታዘዙን አረጋግጠዋል፡፡

“መመሪያው በ1983 ዓ.ም ከወጣው (አዋጅ ቁጥር 3/1983 ዓ.ም ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት የወጣ አዋጅ ገጽ 12) አዋጅ ጋር የሚጣረስ ነው፣ በአዋጁ የአዲስ አበባ መስተዳድር የራሱን መመሪያ ማውጣት እንደሚችልም የሚገልፅ ነጥብ የለም፡፡ ” በሚል የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የአዲስ አበባ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ሃላፊዎችን ቢጠይቁም የከንቲባ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው “ለሰኞ ተመካክረን ምላሽ እንደጣችኋለን” የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸዋል፡፡
የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ዛሬ ከሰአት ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለመመሪያው የሚያውቀው ነገር እንዳለ በቦርዱ ጽ/ቤት በአካል ተኝተው ጥያቄ ቢያቀርቡም የቦርዱ ዋና ፀሀፊ አቶ ነጋ “ምርጫ ቦርድ እንዲህ አይነት መመሪያ ስለመውጣቱ የሚያውቀው ነገር የለም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል በመላው ሀገሪቱ እያካሄደ ላለው ህዝባዊ ንቅናቄ ከህዝብ ፊርማ ሲያሰባስቡ፣በራሪ ወረቀት ሲበትኑና የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ከ72 በላይ የሚሆኑ አባላቱ በአዲስ አበባ ህገወጥ እስር ተፈፅሞባቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡
staff reporter | August 30, 2013 at 9:51 am | URL: http://wp.me/p2gxmh-2bK
Comment    See all comments