Wednesday, July 31, 2013

የት ይደርሳል የተባለ ጥጃ ወያኔ ግቢ ውስጥ ሲልከሰከስ ታዬ! ጦቢያን ገረመው


       
Gudu Kassa
 ኃይሌ በዜግነት ምክንያት ፕሬዝደንት ይሆናል አይሆንም የሚባለው ቀልድ ጉንጭ አልፋ ነው፡፡ ወቅታዊ ቀልድም ይመስለኛል፡፡ መለስ ዜናዊና በረከት ስምዖን በፍላጎታቸውና በወፍዘራሽ የዜግነት ፍልስፍናቸው ‹ኤርትራዉያን› ሆነው ሲያበቁ ‹የጎረቤት ሀገር ኢትዮጵያን› አንቅጥቅጠው እየመሩ ባሉበት ሁኔታ ኃይሌን ከኢትዮጵያዊነት አንጻር ማማት ለራሱም ሳያስቀው አይቀርም፡፡ ያ ዓይነቱ ጨዋታ የፖለቲካ ጨዋታ ነው፡፡ ‹በእውኑስ አሁን ኢትዮጵያ እየተመራች ያለችው በኢትዮጵያውን ነውን?› ብለንም መልሱ በአንድዬ እጅና በታሪክ ማሕጽን ውስጥ የሚገኝ ጥያቄ መጠየቅ እንችላለን - ለራሳችን፡፡ ኃይሌን በዜግነት ችግር ማንቀራበጥ ለወያኔ ድራማ ማጠናከሪያ ውሻል ማቀበል ይመስለኛል፡፡ አንደኛ ነገር ወያኔ ሕግ ማውጣት እንጂ ማክበር አያውቅበትም፤ እንዲያውም ያቆመው ሕግ የማይጠቅምና በረዳቶቹ ዘንድ ትዝብት ውስጥ የሚጥለው መስሎ ካየው በአንድ አዳር ያን ሕግ ተብዬ ሰርዞ በምትኩ ሌላ ሊያወጣ የሚችል የዘመኑ መንግሥታዊ ጨቡዴ መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ እናም ችግሩ የዜግነት እንደማይሆን ይገባል ይልቁንስ፡፡ የኃይሌ ሀገርን መምራት ያለመቻል ችግር ያለው ከዜግነት አንጻር ሊመስለኝ አልፈልግም፡፡ ስንትና ስንት የፈጠጠ ጉድለት እያየንበት በዚህ ውሃ የማያነሳ ጉዳይ ጊዜ ማባከኑ በማይሠራ ሕግና ከ‹ተጻፈበት ቀለም› የዘለለ ዋጋ በሌለው ወረቀት ላይ በከንቱ ከመጯጯህ ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡

ከሰሞነኛ የሀገራችንና የዓለማችን አንዳንድ ሥራ ፈት የዜና ማዕከላት ወሬዎች መካከል አንዱ የኃይሌ ገ/ሥላሤ የሥልጣን አራራ መሆኑን በግሌ መረዳን ሳላሳውቅ ወደሁለተኛው አንቀጽ በመግባቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ እናም በግሌ - ጉዳዩ በቀጥታ እንደሚያገባው አንድ ኢትዮጵያዊ - ስለዚህ መካሪ ያጣ የገንዘብና የሥልጣን በሽተኛ ሰውዬ የሚሰማኝን ጥቂት ነገር ልበል፡፡ ያገባኛል ያልኩት ያለኝ ዜግነት አንድ ብቻ - ያም ኢትዮጵያዊነት ብቻ በመሆኑም ብቻ አይደለም፤ ያገባኛል ያልኩት ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ መመኪያና መኩሪያ ስለሌለኝ ብቻም አይደለም፤ ያገባኛል የምለው ይህን ሰው በሚገባ ስለማውቀው እንኳንስ ሀገርን የመሰለ ትልቅ ነገር ለመምራትና ቤቱንም በአግባቡ ለማስተዳደር የሚያቅተውና በዘመናዊ የቴክሎጂ መሣሪያ ቢመረመር የጤናማነቱ ጉዳይ ቤተሰብ ለመመሥረት ጭምር የማያስቸለው እንደሚሆን በከፍተኛ ደረጃ ስለምጠራጠር ነው - የኔ ‹ሥራ› መጠራጠር ነው - የ‹አልጠረጠርም› ባይ ሥራ ደግሞ ጥርጣሬን ማስወገድ የሚያስችል ማስረጃ ማቅረብና ጠርጣሪን ማሣፈር ነው፡፡ አዎ፣ ደደብን ደደብ ካላሉት ቤተ መንግሥት ውስጥ በማያውቀው ነገር ገብቶ ይፈተፍታል ይባላል፡፡  ኃይሌ እውነቱን ይረዳው - ሕዝቡ አብጠርጥሮ ያውቀዋል - ከዋናው በር እስከመኝታ ቤቱ እናውቃለንና ዝምተኝነታችንን አይበዝብዝብን፤ በሀብቱ ወይም በወያኔያዊ ጥገኝነቱ ፈርተን የማንናገር ከመሰለው ተሳስቷልና ከአሁኑ ይታረም - ቢያንስ እሱና እሱን መሰል ቅሌታሞች እንዲፈነጥዙብን አንፈቅድም - እውነቱን በመናገር የእሱነቱን ማንነት እናጋልጣለን፡፡ እናም ዘመድ ካለው በጊዜ ይምከረውና የሥነ ልቦና ዐዋቂ/ሐኪም እንዲያክመው ያድርግ፤ አለበለዚያ ብዙ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ በእልህ የጀመረውን የዕብድ ውሻ መንገድ እገፋበታለሁ ካለ በግል ሕይወቱ ጭምር እየገባሁ በምዘባርቃቸው አንዳንድ ጉዳዮች በጣም ላስከፋው ከወዲሁ ቃል እገባለሁ፤ ከዛሬ ጀመርኩ፡፡ ይሉኝታ የሚሠራው ይሉኝታ ላለው ነው፤ ከፈጣሪ መንገድ እንዳፈነገጥሁ ይገባኛል - ጊዜ ካለኝ ንስሃ እገባለሁ እንጂ እንዲህ ያለውን መናኛ ስብዕና ከማጋለጥ አልመለስም፡፡ በሚሆነው አዝናለሁ - ምርጫ ግን የለኝም፡፡
እርሱ በኛ ላይ ከሚያደርገው ብልግና ይልቅ የአንድን ሰው ገመና ገሃድ ማውጣትና ሀፍረትን የሚያውቅ ከሆነ በሀፍረት እንዲሸማቀቅ ማድረግ ከተቆርቋሪ ዜጎች ይጠበቃልና የእርሱን ብልግና የምታውቁ ሁሉ ከእንግዲህ አትሳሱለት፤ ለይሁዳ የሚሳሳ አንጀት ሊኖረን አይገባም፡፡ ገና ለገና ባንዲራችንን - ሊያውም ኋላ ኋላ ላይ ኢትዮጵያን በትክክል የማይወክል የወያኔን ደባደቦ ባንዲራ እየመረጠ - አውለብልቧል ብለን እላያችን ላይ ሲያቀረሽ ዝም ማለት የለብንም፡፡ ይሄ ቆሻሻ የውሻ ልጅ በኢትዮጵያማ እንዲህ አይጨማለቅም! የሌሎቹ አነሰንና ደግሞ ይህ ማይም የወያኔ እግር አጣቢ በስማችን ይነግድብን? አላሙዲንና ኃይሌን ለመሰሉ ውሾች - በአእምሮ ሣይሆን በሆድ የሚያስቡ ደንቆሮ ዓሣሞች የሚያዝን ኅሊና የለኝም፡፡ ይቅርታና ምሕረት ሌላ ነው - ሆን ብሎ ሀገርን ለገንዘብና ለዝና እንዲሁም ለሥልጣን የሚሸጥ የዲያብሎስ አጋንንት ግን በምንም መንገድ ሊታለፍ አይገባም፡፡ ወያኔ ጋር እየተሸራሞጡና ሣምባን ከካሊፕሶ እየጨፈሩ ሕይወቴን የቀን ጨለማ እንዲውጠው ያደረጉትን ሁሉ - ማንም ይሁኑ ማን - ምንም ይሁኑ ምን - በተቻለኝ ሁሉ ሌላው ቢቀር በብዕር እዋጋቸዋለሁ፡፡ የነዚህን ሰዎች ግፍና በደል ለመሸፈን የሚሞክር ሁሉ የነሱ ተባባሪና ረዳት ነውና በበኩሌ ጥቁር ውሻ እንዲወልድ እራገማለሁ፤ እናም ተራገምኩ - ‹ይህን መልእክት ሆን ብሎ ያፈነ  ወይ ያሳፈነ በዚህ መልእክት ውስጥ የተጠቀሰ የመርገምት ቃል ሁሉ በራሱና በትውልዱ ይድረስ!›፡፡ ከአሁን በኋላ ለኃይሌ የሚራራ አንጀት ያለውና ከእርሱ ጎን የሚቆም ሁሉ ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር ተባብሮ ታሪክንና ሀገርን ለማጥፋት ከጥልቁ የእሳት ባህር የመጣ እንጂ ሕዝባዊ ወገናዊነት ያለው ጤናማ ዜጋ ሊሆን አይችልምና ኃይሌንና መሰል የወያኔ ቡችሎችን የማይቃወም ከወያኔ አንድ ነው - ስለሆነም እየመጣ ያለው የእሳት ዝናም በእርሱም ላይ ይዝነብ፡፡ ዕድሜውም ልክ እንደወያኔ ሁሉ አጭር ይሁን፤ የወያኔ ጣዕረሞት የርሱም ዕጣፋንታ እንዲሆን ፈቃደ መለኮት ይሁንልኝ - ‹እንዴት? በምን ምክንያት?› እያላችሁ አትጠይቁ (መጠየቅ ያስቀስፋል! Kidding … )- የወያኔ ዕድሜ በሰማያዊ የጊዜ አቆጣጠር በክፍልፋይ ሴከንዶች የምትቆጠር ናት - ወያኔ ጣር ላይ ነው፡፡ ጣር ላይ ያደረሰው የምሥኪኖች ዕንባና የሚዋኝበት የደም ባህር እንጂ የሌላ እንዳይመስላችሁ በተለይ አንዳንዶች በሰው ሥራ ላይ እንዳትመኩ - ማለቴ እንዳትኮፈሱ፡፡ የታዘዘው ኃይል ገና ተገቢ ሥራውን በቅጡ አልጀመረምና! (የነቢይነት ተሰጥዖ የለኝም - እምናገረው የውስጤ የሚነግረኝን እንጂ እንደሁሴን ጅብሪል ፊት ለፊቴ የተሰቀለ ጀንዲ ወይም አንሶላ ላይ የተነጠፉ ቃላተ ትንቢትን እያነበብኩ አይደለም - ስለዚህ ይህን ‹ስሜት ወለድ› ፈለገ-ሃሤት  ጠቅሶ ሰውን ማስደሰት እንዳይቻል በማይም ቃሌ ገዝቻለሁ - ቆዳ ታጣቂውና አንበጣ በሊታው ዮሐንስ በባዶ እግሩ በበረሃ እየዞረ ምን ነበር ያለው? … (አሃ፣ ወዴት ጠጋ ጠጋ - የስሙኒ ቲማቲም በኪሎ 25 ብር ገዝተው ‹እየቆረጡ›ና የአንድ ብሩን ነጭ ፊያሽኮ ቪኖ  በ45 ብር ገዝተው ‹እየኮመኮሙ› የምን ‹ጊዜው ቀርቧል፤ ንስሃ ግቡ› እያሉ በከተማ በረሃ ባስካርባ እየሄዱ መጮህ ነው?)ዓለም
ኃይሌ ፍጹማዊ ገብጋባ ነው - ከሚቋምጥለት ሥልጣን ጋር ምን አገናኘው እንዳትል - ትስስሩን  እናገራለሁ፡፡ ገብጋባነቱ ደግሞ አንድና ሁለት ብቻ ሣይሆን ዓለም የምትጠቀማቸው ቁጥሮች አይገልጹትም፡፡ እንዴ! ለመሆኑ ኃይሌ ከነአካቴው ሰው ነው ማለትስ ይቻላልን? ቀጣዩን የአንዲት ቀን ገጠመኝ (anecdotal episode) እዩና ራሳችሁ ፍረዱ፡፡ ይህ ሰው ልምራችሁ ሲልም ይታያችሁ፡፡
ኃይሌ ይህን እውነተኛ ታሪክ እንዲያስታውስ ወዳጆቹ ንገሩት - የዚህን ደብዳቤም ግልባጭ ላኩለት፡፡ አንድ ወቅት ወደርሱ ቤት የሚገባ የውሃ ጉድጓድ ይቆፈር ነበር፡፡ የቁፋሮው ሥራ እየተካሄደ ሳለ ከሚቆፍሩት ወዛደሮች አንድኛው በናዳ ሕይወቱ ያልፋል፡፡ ያን ሬሣ ወዳገሩ (ወደጎጃም) ለመላክ ሥራውን ይቆጣጠር በነበረ አንድ ጓደኛየ አማካይነት የአካባቢው ማኅበረሰብ ገንዘብ እንዲያዋጣ ይጠየቃል፡፡ ቦታው ቦሌ ነው፡፡ ሁሉም የቻለውን ረዳ፡፡ ያ ከዚያን ጊዜ በፊት ኃይሌን ከቆንቋናነት አንጻር የማያውቀው ጓደኛየ ኃይሌን ከቤቱ አስጠርቶ ችግሩን ይገልጥለትና የረድኤት እጁን እንዲዘረጋ ይጠይቀዋል፡፡ ሀገርና ወገን ወዳዱ ኃይሌ፣  በኦሎምፒክ ሜዳዎች ባንዲራ ሲሰቀል የዐዞ ዕንባውን የሚረጨው አስመሳዩ ኃይሌ ወዲያውኑ ሃያ ብር ያወጣና ይሰጣል፡፡ ጓደኛየ ክው ብሎ ይደነግጣል - እዚያ አካባቢ የነበሩ ወዛደሮችና አላፊ አግዳሚ ተራና በጣም ድሃ ዜጎች ከዚያ ገንዘብ እጅግ የሚበልጥ ሰጥተዋልና የጓደኛየ ድንጋጤ የሞት ያህል ሆኖ አጽናኝ አስፈልጎት እንደነበር ከብዙ ዓመታት በኋላም አሁን ድረስ እያንዘረዘረው ያስታውሰዋል፡፡ ጓደኛየ ሲረጋጋ “ምነው ኃይሌ? ይህን ያህልማ እኔም አያቅተኝም፤ ከአንተ እኮ የምንጠብቀው … ይህ ልጅ እኮ ሲሰራ የነበረው ወዳንተ ቤት ይገባ በነበረ መስመር ነው፡፡ ካንተማ …” በማለት ሲወተውተው “እንዴ - ደም ተፍቼ እኮ ነው የማገኘው፤ መሬት ወድቆ እኮ አላገኘሁትም …”ብሎ እያጉመተመተ ቤቱ ይገባና ያቺን ሃያ ብር አስቀርቶ 200 ብር ይሰጠዋል፡፡ ኃይሌ እኮ ለጫማ ጠራጊ አንድ ብር ሰጥቶ ሃያ አምስት ሣንቲም መልስ ለመቀበል ዝርዝር እስኪገኝ ድረስ ግማሽ ሰዓት የሚጠብቅ እጅግ ሰፍሳፋና ‹ሀገርና ወገን ወዳድ› ብርቅዬ ዜጋ ነው፡፡ …
መስጠት አለመስጠት የግል ጉዳይ ነው - በመሠረቱ፡፡ እኔ የምለው ግን የዚህ ዓይነት የተለዬ ጋብሮቭ ኢትዮጵያን ልምራ ብሎ መናገር ሳይሆን ማሰብም አይገባውም፡፡ ይቅርና በወያኔ የውሸት ሥልጣን፣ በነገይቱ ኢትዮጵያም ቢሆን ማሰብም የለበትም፡፡ አመራር ከቸርነት ይጀምራል፤ ያለውን አለምክንያት ይበትን ወይ ይዝራ ማለት አይደለም - ግን እስከዚህን አስተዛዛቢና አንጀትን እስከወዲያኛው የሚቆርጥ ደረጃ የሚንገበገብ ሰው የቤቱንም ቆሎና ስኳር እየቆጠረ - የሞሰብ እንጀራ ላይ በሣር ምልክት እያደረገ በሻይሎካዊ ባሕርይ ሌሎችን ሰላም መንሳቱ አይቀርምና ወደ ቁጩም ሆነ ወደእውነተኛ የሥልጣን ወንበር ሊጠጋ አይገባውም፡፡ ከነብሂሉ ‹ሆዳም ሰው ፍቅር አያውቅም›፡፡ ገብጋባ ሰው ሆዳም ነው፤ ሆዳም ሰው ገብጋባ ነው፤ ገብጋባ ሰው ራሱን አይወድም፤ ገብጋባ ሰው ሰውን አይወድም፤ ገብጋባ ሰው ሀገር አያውቅም፤ ገብጋባ ሰው ፍቅር አያውቅም፤ ሆዳም ሰው ለሆዱ ሲል ሀገሩንም ወገኑንም ቤተሰቡንም ይሸጣል፡፡ ኃይሌ ለገንዘብና ለዝና ሲል ዓለምን ሸጦኣል ፤ ዓለምም ዘወርዋራ ናትና ፊቷን አዞረችበት - በመጨረሻም የሀብትና የዝና ጥሙ አንጎሉ ላይ ሲያናፍልበት ተመልክታ ብታስጠነቅቀውም ሊሰማት ባለመቻሉ እሷም ናቀችው - ከሕዝብ ጋር ሲላተም እያየችም አላዘነችለትም፤ በቂ የጥሞና ጊዜ ስጥታው ነበርና - ዓለም እንዲህ ነች፤ ሕይወትም፡፡ ተፈጥሮው ለአመራር ሳይሆን ገንዘብና ዝና ለማሳደድ ነው - ኃይሌ ገንዘብና ዝና አይጠግብም - እሱን መሰሎችም እንዲሁ፡፡ ኃይሌ ያቋቋመው በጎ አድራጎት አለ? ኃይሌ እንዲህ ያለ መልካም ነገር ለእገሌ ሠራ ተብሎ ያውቃል? በመጀመሪያ ለዕርዳታና ለመሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች ወደኃይሌ ቤት የሚሄድ ሰው ያለም አይመስለኝም - ሁሉም ስለሚያውቀው - ማን አፉን ያበላሻል? ለወትሮ ጅብ ነበር ወደማያውቁት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ የሚል፤ ዛሬ ደግሞ ዘመን ተዛወረና ደደቡና ማይሙ ኃይሌ በሚታወቅለት ለፍዳዳ አንደበቱ የሕዝብን የነጻነት ትግል ለማኮላሸት ከሀገር መሠሪ ጠላቶች ጋር ይለፋደድ ያዘ፡፡ ‹ልጅ አይውጣለት› ብዬ አልረግመው ነገር ሆኖብኝ ተቸገርኩ እንጂ ሰውዬው ብዙ ያናግራል፡፡ ብቻ እግዜር ይይለት - ዕድሜውንም እንደሚያመልክበት እንደመለስ ያድርገው! በቃ፡፡ ከጠሉ ወዲያ ልምምጥ የለም፤ የኛ ነበር - የኛነት አስጠላው - የዝና ሰይጣናዊ መንፈስ እኛን እንዲጠየፍ አስገደደው - በኛም ላይ ሽንቱንና ለከት ያጣ ቅርሻቱን ይለቅብን ጀመረ፡፡ ስለዚህ ሞቱን እንጂ ብልግናውን ላለማየት ቆርጫለሁ - ይሆናል፡፡ እንኳን ኃይሌ ጎብላላዎቹ ሐምሌና ነሐሴም ያልፋሉ፡፡
የኃይሌ ተፈጥሮ ሀገርን መምራት ሳይሆን ሮጦ የራሱን ስምና የሀገርን ስም ማስጠራት ነው፡፡ ሁሉም ሰው የየራሱ ተፈጥሮ አለው፡፡ ለመሪነት የራሱ የሆነ ግርማ ሞገስና የዕውቀት ደረጃ አለው - እንዳሁኑም የወያኔ ዘመንም ሆነ እንዳለፉት መሪር አገዛዞች ሳይሆን እንደጥንቱ አፍላጦናዊ ፍልስፍና፡፡ ማይሙ ኃይሌ ተፈጥሮ የለገሰችው ችሎታ መሮጥን ነው - በቃ፤ እግርና ጭንቅላት ደግሞ ለዬቅል ናቸው - በአቀማመጣቸው እንኳን ተቃራኒዎች መሆናቸውን ያጤኗል፡፡ ከተፈጥሮ ችሎታው ከሩጫ አልፎ መሪ አድርጉኝ ቢል ግን ወጥ መርገጥና አሳዳጊ የበደለው መሆኑን በይፋ ማሳወቅ ነው - ለወያኔ ሥልጣን አይመጥንም ማለት እንዳልፈለግሁ ግን አስረግጬ መናገር እፈልጋለሁ - ለወያኔ ሹመት በትንሹ ግዑዝ ድንጋይ መሆን ከበቂ በላይ ነው - አምባሳደር ለመቀበልና ለመሸኘት ደግሞ እንደራስ ሆቴል አንበሣ በምሥል መልክ ወንበር ላይ የሚዘፈዘፍ ግርማ ወልደጊዮርጊሳዊ ጥውርም ሲበዛ ነው፡፡ ኃይሌን በሚመለከት አጥንቴ ድረስ ዘልቆ ክፉኛ የተሰማኝ የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቁና ሀገር ሻጭ ወያኔን መጠጋቱ ነው - ምንም ነገር ሳይቸግረውና ማይማዊ ደደብነቱ አስገድዶት (በነገራችን ላይ እንደወያኔዎች ሁሉ በሰይጣናዊነት እንደሚታማም አውቃለሁ - በማስጠንቆል የደረሰበትን የሀብትና የዝና ጣሪያ የማናውቅ መስሎትም ከሆነ ተዘናግቷልና እንደምናውቅ ይወቅ፤ ከተመቸኝና ከፈለግሁ ወደፊት በዚህ ጉዳይ ዙሪያ እመለስበታለሁ)፡፡ እንኳንስ እርሱ እኔ ራሴ - ኃይሌ ንፍጡን እያዝረከረከ ደብተሮቹን በጉያው ወትፎ ወዳልጨረሰው ትምህርቱ ይሄድ በነበረበት ሰዓት ከፖለቲካው ባልራቀ ሁኔታ ሀገሬን አገለግል የነበርኩትና በመቶዎች የሚቆጠሩ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው መጣጥፎችን ለሀገሬ ያበረከትኩት ሰውዬ ለቀበሌ አመራር እንኳን እበቃለሁ ብዬ አላስብም፤ ምክንያቱም ተፈጥሮየ ለአመራር ሳይሆን ለመጻፍና ምናልባትም ለማላውቀው ለሌላ ነገር ነው፡፡ ምቹ ሁኔታ ተፈጠረልኝ ብዬ እንደኃይሌ ‹ለዚህ ቦታ ምረጡኝ› ብል መናገሩንና መወዳደሩን እንደምችል ባውቅም ካለተፈጥሮ ዝንባሌና ችሎታ ገብቼ መፈትፈቱ ግን የኋላ ኋላ ችግር እንደሚያመጣብኝ እረዳለሁና አልሞክረውም፡፡ ይህን የምለው ለጊዜው ሌላ እውነተኛ ማነጻጸሪያ ስላጣሁና እውነቴንም ስለሆነ ነው፤ ጊዜ ሰጠኝ ተብሎ ወደአንድ ነገር ቢሞጀሩበት ችግር ነው - የግብጹ ሞሐመድ ሞርሲን ልብ ይሏል - የተፈጥሮ ጥሪን መረዳት ተገቢ ነው ወንድሞቼ እንዲሁም እህቶቼ፡፡ እናም ኃይሌ መቶ ሀገር ቀርቶ አንድ ሺህ ሀገር ቢዞርም በኢሣት እንደሰማሁት  አዟዟሩ የሩጫ እንጂ ፖለቲካዊ የሥራ ጉብኝት ባለመሆኑ ዙረቱ እንደተባለው ዕቃ ለመሸመትና ያማረ ሆቴል ተከራይቶ ለመንፈላሰስ ካልሆነ በስተቀር ለምንም ዓይነት የፖለቲካ ተሹዋሚነት አያበቃውም፡፡ ይህ ሰው ጭንቅላት የሚባል ነገር በጭራሽ ስለሌለው እንጂ - እንደእንስሳ ሽምጥ ለመጋለብ ከሚጠቅም ደመነፍሳዊ አንጎል በስተቀር ማለት ነው - ትንጥዬ አንጎል ብትኖረው ኖሮ ወደዚህ ቅሌትና ውርደት አይገባም ነበር፡፡ በደደብነቱ ሳቢያ ልቦናው ታውሮበት እንጂ እኔና እርሱ እንደዮሐንስ መጥምቁ አባባል የጫማቸውን ማሠሪያ ለማሰር ወይ ለመፍታት የማንበቃ ስንትና ስንት ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ኢትዮጵያውን ቀኒቱን እየተጠባበቁ ናቸው - በበሣል አመራራቸው እንደእስራኤል በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ሌሎች ሀገሮች ወደደረሱበት የሥልጣኔና የዕድገት ማማ ለማድረስ(አባብሌ ዲግሪው ላይ አለመሆኑን ‹ፕሊዝ› ተገንዘቡልኝ - ለዲግሪ ለዲግሪውማ ‹ፕሮፌሰሮች› ክንፈ አብርሃምና አንድርያስ እሼቴስ ነበሩን አይደል? በአካልም በመንፈስም በኅሊናም ሙታን ሆነው ሀገር ሻጮች ጋር ተባበሩብን እንጂ)፡፡ ከዚህ ሰው ሳይሆን ምቹ ሁኔታን የማጣታችን ሁኔታ አኳያ የዚህን ንፍጣም ሰውዬ ምኞትና የሕጻን ፍላጎት የሚመስል ጤንነት የጎደለው ቅዠት ስታዘብ አንዳች የመደፈር ጸጸት ይወረኛል፤ በምትንቀው መናኛ ሰው እንደመደፈር ያለ ደግሞ የጸጸት መንስኤ የለም - ደግሜ ልራገም መሰለኝ - የሥራውን ይስጠው፤ እሱ ሕዝብን እንደናቀ በዓለምም እንዳስገመተን ሞት ግን ውለታ ይዋልልንና ንቆ አይተወው፡፡  ራስን ያለማወቅ ችግር - እርግጥ ነው - የዓለማችን ራስ ምታት መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና ራስን አለማወቅ የፈለገውን ያህል  ችግር ያስከትል እንጂ እንደኃይሌ ያለ ሰው በምናውቅለት የሥራና የትምህርት ወይም የችሎታና የልምድ ታሪክ ከመሬት ተነስቶ የጠላት መሣሪያ ልሁን ብሎ መነሳቱ ዕብደት ካልሆነ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡
‹ምላሴ ጥቁር ነው፤› እርግማኔ አይደርስም አልልም፡፡ በሥርዓት ደረጃ እየዘገየብኝ ተቸገርኩ እንጂ በግለሰብ ደረጃ እርግማኖቼ ዒላማዎቻቸውን መትተው ወደሰገባቸው የሚመለሱባቸውን ጊዜያት ማስታወስ አይከብደኝም፡፡ አበበ ገላው በመብረቃዊ የቁጣ ድምጹ የተሸሸገና በያዝ ለቀቅ የፖሊስና ሌባ ጨዋታ ከሟች ጋር ድብብቆሽ ይጫወት የነበረን ነቀርሣ አፋፍሞ የመለስን ሞት ማፋጠኑ አይዘነጋም፡፡ በዚያም ምክንያት የጎጃም ባላገር እንዲህ ብሎ ስንኝ መቋጠሩ በ‹ኢቲቪና በኢትዮጵያ ኤፍ ኤሞች› በስፋት ተዘግቧል፡፡
ሽጉጥ አልታጠቀ መትረየስ የለው፤
ባንደበቱ ገዳይ አበበ ገላው፡፡

እኔም በእርግማን ሰው መግደሌ ይፋ ሆኖ ወደሕዝብ ጆሮ የሚደርስልኝ ከሆነ ያገሬ ባላገር እንዲህ ብሎ ሳይቀኝልኝ እንደማይቀር ተስፋ አደርጋለሁ፤ ምኞት መቼም አይከለከልም፡፡

ሞይዘር አልታጠቀ ፊሻሌ የለው፤
በጠሎቱ ገዳይ ጦቢያን ገረመው፡፡

ስለዚህ ኃይሌን እረግሜያለሁና ‹ከኔ እርግማን› ነጻ መውጣት ከፈለገ አሁኑኑ ይቅርታ ጠይቆ ከ‹ውድድሩ› ይውጣና አርፎ ሌላ የሚችለውንና የሚገባውን ሥራ መሥራቱን ይቀጥል፡፡ በበኩሌ ጦሬን ሰክቻለሁ - በፈጣሪ ፊት ተንበርክኬ የእርሱን መጨረሻ እንዲያሳየኝ በዕንባ ጭምር ጠምጄ ይዠዋለሁ - ሌሎችም ዕርዱኝ - እንረዳዳና ይህን ተናግሮ አናጋሪ የወያኔ ዕብድ ውሻ እናስወግድ - የተከፋች ‹አብዮት ልጇን› እንደምትበላም እናሳየው፡፡ መዳኛው አንድና አንድ ብቻ ነው - ያም ተጸጽቶ ሕዝብንም ይቅርታ ጠይቆ መመለስ ብቻ ነው(በወያኔ ትዕዛዝ ወደ አሥመራ ተልኮ ሻዕቢያ ሥር በመደፋት የአማራውን ሕዝብ ለውርደት የዳረገው ንጉሤ አስገልጥ(?) የተባለ ቀልማዳ ከሃዲ እንዴት እንደሞተና ሕዝብ አድሞበት ሬሣው በኩሊ እንደተቀበረ ልብ ይሏል፤ ሕዝብ ከጠላ መድረሻ የለም - በተለይ የኢትዮጵያ! ያቆየንና ገና ብዙ እናያለን ውድ ወርቃማ ኢትዮጵያውያን!) ፡፡ ይህን ደግሞ ይወቅ - ከተገፋና በበደል ብዛት ከሚንተከተክ አእምሮ ኃይል ይመነጫል፤ ያ ኃይል ደግሞ አጥፊም አልሚም ሊሆን ይችላል - ጦርም ዳቦም ከአእምሮ ይፈልቃል፡፡ እየተረጋገምን ዘር ከምናጠፋ እየተሳሰብን ዘር ብናለማ ይሻላልና ይህን መልእክቴን - ሳታናንቁብኝ - ለርሱው ለደንቆሮው ኃይሌ አድርሱልኝ - ሁኔታዎች ቢመቻቹ በአካል ባገኘውና እስከዶቃ ማሰሪያው ብነግረው በወደድኩ - ግን … ፡፡ (እንዳስፈላጊነቱ እቀጥላለሁ!)

maleda times | July 29, 2013 at 1:30 pm | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-25d
Comment   See all comments

Wednesday, July 17, 2013

የሚወለዱበት፣ የሚሞቱለትና የሚሞቱበት መሬት (ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም)


የሚወለድበትን መሬት ማንም ሰው አይመርጥም፤ የዘመኑ ቅንጦት ኢትዮጵያ አርግዞ አሜሪካ መውለድ ቢሆንም፣ ልጁ ምርጫው ውስጥ የለበትም፤ አንኳን ልጁ አባትዬውም ምርጫው ውስጥ የሚገባ አይመስለኝም፤ በእንደዚህ ያለው ኢትዮጵያን አስጠልቶ-ሌላ-እንዲሆን በተፈጠረ ቅንጦት የሚወለድ ኢትዮጵያዊ ምን እንደሚሆን መተንበይ ያዳግታል፤ ልጁ ወይም ልጅቱ በራሳቸው ዝንባሌ፣ ፍላጎትና ጥረት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸው ግንኙነት በእልህ ከአልተለወጠ እናቶቻቸው የተለሙላቸው ማንነት ከኢትዮጵያዊነት ይገነጥላቸዋል፤ ነገር ግን የኢትዮጵያዊነት ስሜት እንዲህ በቀላሉ ተቀርፎ የሚወድቅ አይደለም፤ ሲደንቀኝ የቆየ ነገር ልናገር፤ አንድ ጊዜ በኢሰመጉ ተልእኮ ካናዳ ሄጄ አንድ ስብሰባ ላይ አንድ አርመን ወጣት ነበረ፤ ይህ ሰው ለኢትዮጵያ ያለው ስሜት በጣም የጋለ ነበር፤ በሌላ ዘመን ደግሞ ፋጡማ ሮባ በአትላንታ ማራቶን በአሸነፈች ጊዜ ደግሞ በቴክሳስ የሚኖር ከአንድ ግሪክ ገንፍሎ የወጣው ንግግር በጣም ልብን የሚነካ ነበር፤ ለዚህ አርመንና ለዚህ ግሪክ የኢትዮጵያዊነት ስሜት በዘር የተላለፈላቸው አይመስለኝም፤ ስለዚህም አሜሪካ የሚወለዱትም ኢትዮጵያውያን ልጆች እናቶቻቸው ሳያውቁ ከውስጣቸው የሚያስተላልፉላቸው ስሜት ኢትዮጵያዊነታቸውን ይገነባው ይሆናል፤

እንደሚመስለኝ የሚሞቱለት መሬት ከውስጥ ከነፍስ ጋር በተገናኘ ስሜት የተቆራኘ ነው፤ መሬቱንና ስሜቱን ምን አገናኛቸው? ምን አቆራኛቸው? እንዴት ተቆራኙ? የሚሉትንና ሌሎችንም ጥያቄዎች ለመመለስ መሞከር እዚህ ቦታው አይደለም፤ ለዚች መሬት የሞቱላት በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች መኖራቸውን አምነን በመቀበል እንነሣ፤ ምናልባትም አብዛኛዎቹ ቁራጭ መሬትም አልነበራቸውም፤ እንዲያውም አብዛኞቹ ለመቃብር ያህል ሁለት ክንድ መሬት አንኳን አላገኙም፤ በተሰለፉበት ወድቀው የአውሬና የአሞራ ምግብ ሆነው የቀሩ ናቸው፤ ለመሬት ፍቅር ሞተው ለመቃብር የሚሆናቸው መሬት እንኳን አላገኙም፤ ነገር ግን የሚደንቀው እነሱ ሞተው ለመቃብርም የሚሆን መሬት ሳያገኙ የሚቀጥለውን ትውልድ ባለመሬት አደረጉት።
እንደሚመስለኝ የአንድ አገር አንዱ ትውልድ በሞቱ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፈው መሬት ብቻ አይደለም፤ ሲሞት ይዞት የነበረውን ጎራዴና ጋሻ፣ ለሞት ያበቃውን የመሬት ፍቅር፣ ክብርና ኩራትም ጨምሮ ነው፤ መሬቱን ብቻ ተረክቦ ሌላውን መጣል የውርደት መጀመሪያ ይሆናል፤ እዚህ ላይ ብዙ ሰዎች በሚጠሉት ቃል መጠቀም ልገደድ ነው፤ ባንዳ የሚባለው መሬቱን ከክብርና ከኩራቱ ጋር ለጠላት ያስረከበ ነው፤ (እውነተኛው ባንዳ እንዲያውም ዜግነቱንና ወገኖቹን ክዶ፣ የሰውነቱን ክብር ሸጦ የጠላት ሎሌ በመሆን ወገንን እያስጠቃ ተዋርዶ የሚያዋርድ ነው)፤ ለባንዳው መሬት ርስትና ዓጽመ-ርስት የሚባሉ ነገሮች ትርጉም የላቸውም፤ ዓጽመ-ርስት የሕይወት መስዋእት የተከፈለበት መሬት መሆኑ ለባንዳው ባዕድ ነገር ነው።
የኢትዮጵያ መሬት ከአድዋ ዘመቻ እስከዛሬ ስድስት ያህል ትውልዶችን አስተናግዶአል፤ ከአድዋ አስከማይጨው ሁለት ትውልዶች፣ ከማይጨው እስከ1967 ሁለት ትውልዶች፣ ከ1967 አስከ2005 ሌላ ሁለት ትውልዶች እነዚህ ትውልዶች በኢትዮጵያ መሬት ላይ ያመጡትን ለውጥ ሁሉም የሚያውቀው ይመስለኛል፤ ቢሆንም ልዩነታቸውን ማመልከት የሚያሻ ይመስለኛል፤ በአድዋ የዘመተው ትውልድ በርስትና በዓጽመ-ርስት ላይ የተተከለ ልበ-ሙሉ ባለቤት ነበር፤ የማይጨው ዘማች በግርማዊነታቸው ቸርነትና መልካም ፈቃድ ላይ የተመሠረተ ስጦታና የማደሪያ መሬት ነበረው፤ በአንዳንድ ቦታ ብዙ ገበሬዎችን ከመሬት ባለቤትነት የነቀለና ወደጭሰኛነት የለወጠ ሥርዓት ነበር፤ ከ1967 ወዲህ ሁለት ዓይነት የመሬት አጠቃቀም ይታያል፤ አንዱ የደርግ ሥርዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ በሙሉ ከዳር አስከዳር እኩል ባለመሬት ለማድረግ ያወጣው አዋጅ ርስትንም ማደሪያንም ሽሮ የመሬት ባለቤትነትን በዜግነት ላይ ተከለ፤ የወያኔ ሥርዓት ሲመጣ የገጠር መሬትን በፖሊቲካ ታማኝነት ደለደለ፤ የከተማ ቦታን ደግሞ በአጼ ዘመን ሲሠራ እንደነበረው ለቅርብ ሎሌዎችና ታማኛ አገልጋዮች እንደማደሪያ ዓይነት እየሆነ ተሰጠና አዲስና በጣም ከፍተኛ የከተማ ባለሀብቶች መደብ ተፈጠረ፤ በገጠርም ለልዩ ሰዎችና ለስደተኞች፣ እንዲሁም ለውጭ አገር ባለሀብቶች (ቻይና፣ ህንድ፣ ሆላንድ … ) ተደለደለ፤ እንዲህ እንዲህ እያለ በወያኔ አገዛዝ በውጭ አገር ከበርቴዎችና በአገር ውስጥ የቢሮና የጠመንጃ ከበርቴዎች እየበረከቱ ደሀው ተደፈጠጠ፤ የወያኔ አገዛዝ የማርክስና የሌኒንን መፈክር አንግቦ ተነሣና ደሀን የጠላበት ደረጃ ላይ ደረሰ፤ እንደሚስለኝ የተለመደው የአስተሳሰብ ስሕተታቸው ነው፤ ደሀነትንና ደሀን አንድ አድርገዋቸዋል!
በወያኔ አገዛዝ በገጠሩም ሆነ በከተማው መሬት ላይ የተወሰደው በጣም ደፋር እርምጃ በጣም የሚያስደንቅና ገዢዎችንም ተገዢዎችንም ለታሪክ ትዝብት የሚዳርግ ነው፤ አንድ ኪሊሜትር መንገድ ለመሥራት ስንት ደሀ ቤተሰብ ይፈናቀላል? አንድ ትልቅ ሕንጻ ለመገንባት ስንት መድረሻ የሌላቸው ደሀዎች አውላላ ሜዳ ላይ ይወድቃሉ? ነገር ግን ጨቋኝና ተጨቋኝ በስምምነት ለሚቀጥለው የጥቃት ዙር ይዘጋጃሉ፤ ይህ የትም ሌላ አገር የሚሆን አይመስለኝም፤ የኢትዮጵያውያን ልዩ ችሎታ ነው፤ እዚህ ወደዝርዝር ምክንያቱ አልገባም፤ ግን ምክንያት አለው።
እንኳን ለቀለብ ማምረቻ የሚሆን መሬት፣ አንኳን የመኖሪያ ቤት የሚሠራበት መሬት ለመቃብርም የሚሆን ሁለት ክንድ መሬት በሊዝ ሆኖአል፤ ወደፊት ደሀ የሚጣልበት መሬት አይገኝም ይሆናል፤ እንግዲህ የሚሞቱበት መሬት ወደማይኖርበት ሁኔታ እየደረስን ነው ማለት ነው፤ ስለዚህም አስቀድመን ማሰብ የሚያስፈልገን ይመስለኛል፤ በራሴ በኩል አውጥቼ አውርጄ ውሳኔ ላይ ከደረስሁ ቆይቻለሁ፤ መቀበር አልፈልግም፤ ሕይወቴን በሙሉ ተቀብሬ ኖሬአለሁ! ወይም በመቃብር ውስጥ ኖሬአለሁ፤ ድንጋይ እየተደራረበ ተጭኖብኝ አምላክ ድንጋዩን አፈር አድርጎ እያቀለለልኝ ሳልጨፈለቅ ቆይቻለሁ።
ስሞት ደግሞ፣ ወይም አንዳንዶቻችሁ ቃልም እንደምትፈሩ ለማሳየት እንደምትሉት ለህልፈት ስበቃ የሬሳን ፈቃድ የሚፈጽም ከተገኘ መቀብር አልወርድም፤ ድንጋይ አይጫንብኝም፤ ይበቃኛል፤ ኑዛዜ– ከሚለው ግጥሜ ቀንጭቤ ፍላጎቴን ልግለጽላችሁ፡ –
የሕይወት ጽዋዬ ጥንፍፍ ብሎ ሲያበቃ፤
ሲቀር ባዶውን፣ የቆየ ባዶ ዕቃ፤
ሲበቃኝ፤ በቃህ ስባል፣
ትንፋሼ ሲቆም በትግል፣
ስሸነፍ ተሟጦ ኃይል፣
ሰው መሆኔ ቀርቶ፣- አስከሬን ስባል፣
እወቁልኝ ይህን ብቻ፣- የገባኝን ያህል
ሞክሬ ነበር ሰው ለመሆን፤
ሰውነት በከፋበት ዘመን።
በቁማችን ስንቃጠል ስንቀጣጠል ኖረን ስንሞት እሳትን ለምን እንፈራለን? ጭቆናና መታፈን ለምደን መቃብር እንወዳለን፤ እንደአህያችን ጭነት ለምደን ድንጋይ ለመሸከም ቀባሪ አታሳጣን እንላለን፤ –
መሬት አልነበረኝም በሕይወቴ
መሬት አልፈልግም፤ አሁን በሞቴ
አቃጥሉልኝ ሬሣዬን፤
አመድ እስኪሆን፤
አዋሽ ውስጥ ጨምሩልኝ አመዴን፤
አመዴ
ከአዋሽ ይቀላቀል ከዘመዴ
ይቺን አትንፈጉኝ አደራ
አመዴ እንኳን እንዲኮራ
የወያኔ አገዛዝም ሬሳ አቃጣይ ድርጅት ቢከፍት ለመቃብር የሚውለውን መሬት ለቻይና በማከራየት ኪራይ ሰብሳቢነቱን ያጠናክር ነበር፤ ህንዶች ሬሳ በማቃጠል ልምድ ስላላቸው አንድ የህንድ ባለሀብት ሬሳ በማቃጠሉ ሥራ ቢሰማራ የኢኮኖሚውን እድገት በጣም ያፋጥንላቸው ነበር፤ ለአገዛዙም፣ ለባለሀብቱም አዲስ የሥራ መስክ ይፈጥራል፣ ሬሳ የማቃጠሉ ተግባር በቁሙ የተጎዳውን ደሀ ሲሞት ደግሞ መድረሻ እንዳያሳጣው የደሀ ሬሳ ለማቃጠል የሚያስፈልገው ወጪ ‹‹ድህነትን ለመቀነስ›› ከሚለው በጀት ወይም እርዳታ ቢወጣ ችግሩን ሁሉ ያቀላጥፈዋል፤ ደሀውም እየተደሰተ ይቃጠላል ወይም ችግሩ አብሮት እንደሚቃጠል እያወቀ ይደሰታል።
የወደፊቱ ኢትዮጵያዊ የሚወለድበት መሬት የለውም፤ የትም የሚወለድ ነው፣ ፍቅሩን ከመሬት ላይ አንሥቶ ጥሬ ገንዘብ ላይ በመካቡ የሚሞትለት መሬት የለውም፤ ከመሬት ጋር ያለው የዓጽመ-ርስት ቁርኝት ስለተበጠሰ የሚሞትበት መሬት የለውም፤ ‹‹አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለህ፤›› የተባለው ቀርቶ ድንጋይ ነህና ወደድንጋይ ትመለሳለህ የሆነ ይመስላል፤ መሬት የሰውነት መለኪያ መሆኑ ቀርቶ የሀብት መለኪያ ሆኖአል።
staff reporter | July 16, 2013 at 12:37 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-23v
Comment   See all

Thursday, June 20, 2013

ይኼ ሰው ጀግና ነው by Daniel Kibret



አበሻን በአንድ እግሩ ያስቆመ፤ ለሃያ አራት ሰዓታት የመግቢያ ትኬት ፍለጋ ያሰለፈ፤በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የብሔራዊ ቡድኑን ዐርማ የያዙ ቲሸርቶች እንዲቸበቸቡ ያደረገ፤ ሕዝብ እንደ መንጋ ንብ አንድ ዓይነት ዜማእንዲያዜም ያስቻለ፤ ሽማግሌን እንደ ሕጻን ያስጨፈረ፤ ሕጻንን እንደ ሽማግሌ ያስተከዘ፤ የፓርቲና፣ የዘር፣ የእምነትና የባህልንአጥር አስጥሶ ወገንን በአንድነት ገመድ ያስተሣሠረ፤ ይኼ ሰው ጀግና ነው፡፡

ተረስተን ነበረ፤ ረስተንም ነበረ፤ ርቀን ነበረ፤ ተርቀንም ነበረ፤ ተርተን ነበረ፤ተረት ሆነንም ነበረ፤ እግርን ከኳስ አውጥተን ለሩጫ ብቻ አውለነው ነበረ፤ እንዲያ በሩጫ ዓለምን አስደምመን፣ ኳስ ሜዳ ግንዘጠና ደቂቃ መሮጥ አቅቶን ደክሞን ነበረ፡፡ ሕዝባችን ከካምቦሎጆ ኳስ ወደ ዲ ኤስ ቲቪ ኳስ ፊቱን አዙሮ ነበረ፡፡ ይህንንቀይሮ በአፍሪካ ምድር ከ31 ዓመታ በኋላ ብቅ እንድንል ያደረገ፤ በዓለም መድረክ ‹እኛም አለንበት› እንድንል ያስቻለ - ይኼሰው ጀግና ነው፡፡
 ድሮም የዓለምን ታሪክ የሚቀይሩት ጀግና ግለሰቦች ናቸው፡፡ አገር በኮሚቴ አድጋ፣ታሪክ በቡድን ተቀይሮ አያውቅም፡፡ የዓለም ክፉም ሆነ በጎ ታሪክ የተለወጠው የመለወጥ ዐቅም ባላቸው ግለሰቦች ማርሽ ቀያሪነትነው፡፡ ሌላው አጃቢ፣ ተባባሪ፣ ተከታይና ፈጻሚ ነው፡፡ ቢስማርክ የሚባል ሰው ባይነሣ ኑሮ ጀርመን የምትባል ሀገር ተረት ትሆንነበር፡፡ ካሣ (ቴዎድሮስ) የሚባል ጀግና ባይነሣ ኖሮ የዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ቅርጽ ማን ይቀይር ነበር፡፡ አብርሃም ሊንከንየሚባል ፕሬዚዳንት ባይነሣ ኖሮ የአሜሪካን የርስ በርስ ጦርነት ማን ይፈታው ነበር፡፡ ሌኒን የሚባል ሰው ባይወለድ ኖሮኮሚኒዝም የሚባለውን ነገር ከሃሳብ አውጥቶ ማን ሥጋ ያለብሰው ነበር፡፡ ጎርባቾቭ የሚባል ሰው ባይፈጠር ኖሮ ኮሚኒዝምን ማንታሪክ ያደርገው ነበር፡፡ ማንዴላ የሚባል ጀግና ብቅ ባይል ኖሮ የዛሬዋን ደቡብ አፍሪካ ማን ይፈጥራት ነበር፡፡ ቴዎዶር ኸርዝልየሚባል ይሁዲ ባይነሣ ኖሮ እሥራኤል የምትባለውን ሀገር ማን እውን ያደርጋት ነበር፡፡ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ የሚባሉ ንጉሥ ባይነግሡኖሮ ለሁለት የተከፈለችውን አፍሪካ ወደ አንድ አምጥቶ ማን የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሠረት ያደርግ ነበረ፡፡
 በቅርቡ የታሪካችን ክፍል እየተደጋገመ አንድ ነገር ሲነገረን ነበር፤ እየተነገረንምነው፡፡ ‹ታሪክ የሚሠራው ሰፊው ሕዝብ ነው› ይባላል፡፡ እንዴው ለመሆኑ ሕዝብ እንዴት ተሰባስቦ፣ እንዴትስ ተመካክሮ፣ እንዴትስወደ አንድ አቋም ደርሶ ነው ታሪክ የሚሠራው? ሕዝብ ማለትኮ ከመቀሌ እስከ ሞያሌ፣ ከአሶሳ እስከ ቶጎ ጫሌ ያለው ነው፡፤ የትተዋውቆ፣ መቼ ተገናኝቶ፣ እንዴትስ አድርጎ ተደራጅቶ ታሪክ ይሠራል፡፡ ሕዝብ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃልም ተናጋሪእንዲሆን የሚያደርጉትኮ ግለሰቦች ናቸው፡፡
 ሕዝብ ታሪክ እንዲያራምድ የታሪክ ሞተር የሚያስነሡ አውራ ግለሰቦች ያስፈልጉታል፤ሃሳብ የሚያመነጩ፣ ሃሳቡን የሚያሰርጹና ለሃሳቡ ግንባር ቀደም የሚሆኑ ግለሰቦች ያስፈልጉታል፡፡ የአፕል ካምፓኒ መሥራች ስቲቭጆብስ ብቅ ባይል ኖሮ የሞባይል ስልክን ታሪክ ማን ይቀይረው ነበር? ‹ዓለምን የቀየሩት ሦስት አፕሎች ናቸው፡፡ አዳም የበላውአፕል፣ በኒውተን ራስ ላይ የወደቀው አፕልና ስቲቭ ጆብስ የሠራው አፕል እስኪባል ድረስ የስልክን ተፈጥሮ የቀየረው እርሱአይደለም ወይ፡፡ እነ ማርክ ዙከርበርግ ተነሥተው ፌስ ቡክ የሚባል ማኅበራዊ ሚዲያ ባይፈጥሩ ኖሮ የዘመኑን የግንኙነት ባህልማን ይቀይረው ነበር?
 አዎን ሕዝብ አለ፡፡ ሕዝብም ግን ታሪክ ያራምዳል እንጂ ታሪክን አይሠራም፡፡ ግለሰቦችየፈጠሩትን፣ ያሰቡትን፣ የፈለሰፉትን፣ ያመነጩትን የሚያራመደው፣ የሚያቀነቅነው፣ የሚያስፈጽመው፣ ገንዘብ የሚያደርገውና ያንንሃሳብ፣ ፈጠራ፣ ፍልስፍና፣ ግኝትና ጥበብ የኑሮ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል የሚያስችለው ሕዝብ ነው፡፡
 ቡድን ታሪክ የማይሠራበት ምክንያት ታሪክ ለመሥራት ማሰብ ወሳኝ ስለሆነ ነው፡፡ ማሰብደግሞ ግላዊ እንጂ በቡድን ሊታሰብ አይችልም፡፡ በቡድን መመካከር፣ መወያየት፣ ማጥናት፣ መመራመር ይቻል ይሆናል፡፡ በቡድንማሰብ ግን አይቻልም፡፡ ሰው የተፈጠረው በየግሉ ነው፡፡ እንደ መላእክት በማኅበር አልተፈጠረምና በማኅበር ሊያስብ አይችልም፡፡በየግል የታሰበውን ግን በማኅበር መፈጸም ይቻላል፡፡ ቡድኖች፣ ማኅበራትና ተቋማት በግለሰቦች የሚመነጩትን ሃሳቦች የሚፈጽሙ፣የሚያዳብሩና ሕልው እንዲሆን የሚያደርጉ እንጂ ግለሰቦችን የሚተኩ ግን አይደሉም፡፡
 አንዳንድ ማኅበረሰብ ለግለሰቦች ቦታ የለውም፡፡ ‹ሰፊው ሕዝብ› የሚባል የማይጨበጥአካል አስቀምጧል፡፡ ሁሉንም ነገር ለሰፊው ሕዝብ ይሰጠዋል፡፡ ሕያው የሆኑትን ግለሰቦችን ገድሎ፣ ሕያው ያልሆነ ‹ሰፊ ሕዝብ›የሚባል አካልን ያነግሠዋል፡፡ ሰፊ ሕዝብ ድርሰት ይደርስ ይመስል፤ ሰፊ ሕዝብ ዜማ ያመነጭ ይመስል፤ ሰፊ ሕዝብ ይፈጥር ይመስል፤ሰፊ ሕዝብ ይፈላሰፍ ይመስል፡፡ የሕዝብ ሆነው የቀሩ ግጥሞች፣ ታሪኮች፣ አባባሎች፣ ዜማዎችና ባህሎች እንኳን ‹ሰፊ ሕዝብ› ውጦያስቀራቸው ግለሰቦች ባልታወቀ ዘመንና ባልታወቀ ቦታ ያመነጩት ነው፡፡ ግን ምን ያደርጋል ስንት ባለ ዜማዎች፣ ስንት ባለቅኔዎች፣ ስንት ጀግኖች፣ ስንት ታሪክ ነጋሪዎች፣ ስንት ተረት ደራሲዎች ተውጠው ቀርተዋል፡፡
 ይኼው የሐበሻ ጀብዱ የሚባል መጽሐፍ ቢተረጎም አይደል እንዴ ከሰላሌ የሄደ አብቹየተባለ ጀግና ማይጨው ላይ ታሪክ መሥራቱ የታወቀው፡፡ ሰላሌ ወርዳችሁ ብታስሱ ግን አብቹን የሚያውቀው የለም፡፡ ታሪኩን ሕዝብወርሶታል፡፡ ‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ጀግና ነው› በሚለው ብሂል ተውጦ አብቹ ቀርቷል፡፡
 ባህላችን ለቡድኖች፣ ለማኅበራትና ለተቋማት የሚያደላ በመሆኑ አያሌ ግለሰቦችእንዳይሠሩ አድርጓል፡፤ የሠሩትም ቢሆኑ እንዳይታወቁ ውጧል፡፡ ሥራቸውን እንጂ ሰዎቹን ዕውቅና አንሰጣቸውም፡፡ ለመሆኑ ይህንንደረታችንን ነፍተን የምንኮራበትን የአኩስም ሐውልት ሐሳብ ያፈለቀው ማነው? ማን ነበር ጥበበኛው? ማን ነበር ቀማሪው? ማንስነበር ያቆመው? ሐውልቱን እንጂ ማንነቱን አላገኘነውም፡፡ የታደሉት ሀገሮች ሳያውቁት ለቀሩት ጀግና ወታደር ‹ላልታወቀውወታደር› የሚል ሐውልት ይሠሩለታል፡፡ እኛስ ምን ነበረበት ‹‹ላልታወቀው የአኩስም ሐውልት ጠቢብ›› የሚል ሐውልት ብናቆምለት፡፡ለመሆኑ ምን ምን ዕውቀት ያሉት ሰው ነው ያንን ለማሰብ የሚችለው? ታሪኩን በመላ ምት እንደገና ማነጽ ይቻላልኮ፡፡ ሰዓልያንናቀራጽያን በምናባቸው ማሰብ ይችላሉ፤ የታሪክ ምሁራን ከግኝቶቻቸው ተነሥተው መተለም ይችላሉ፡፡
 ልጆቻችን ሐውልቱን እንዲያደንቁ እንጂ ጠቢቡን እንዲያደንቁ አላደረግናቸውም፡፡የጎንደርን ሕንፃ እናደንቃለን እንጂ ስለ አርክቴክቶቹ፣ ስለ መሐንዲሶቹ፣ ስለ ግንበኞቹ አውርተን አናውቅም፡፡ ግንቡ በተአምርየተሠራ ይመስል፡፡ በፋሲል ግንብ ውስጥም እነዚያ ጠቢባን እነማን እንደሆኑ ሊያሳይ የሚችል ምንም ነገር የለም፡፡ አንዴፖርቹጋሎች አንዴ ግሪኮች አንዴ ፈረንሳዮች እያልን የመሰለንን ሁሉ በቡድን ስም ስንጠራ እንኖራለን፡፡ የጥበብ አሻራዎቻችንበሚገኙባቸው በታላላቅ አድባራትም ያሠሩት ሰዎች ስም እንጂ የእነዚያ ጠቢባን ስም ተረስቷል፡፡ ልክ በመጻሕፍቱ ላይ ያስጻፉትሰዎች እንጂ የደራስያኑ ስም ተረስቶ እንደቀረው፡፡
 ብዙ ጥያቄዎች አሉ፡፡ መመለስ የነበረብን ግን ያልመለስናቸው፡፡ እንዴው ለአፍ ታሪክያህል እንኳን የሐበሻ ቀሚስን ማን ጀመረው? እንጀራ መጋገርን ማን አመጣው? አምባሻ ዳቦ በማን ተፈለሰፈ? ሞሰብና ሰፌድ መስፋትንማን አመጣው? ዋሽንትን ማን ጀመረው? ክራርንስ ማን ፈጠረው? ቆጮን ማን ጀመረው? ክትፎስ የማን ፈጠራ ነው? ገንፎንስ ማንፈለሰፋት፣ ጭቆና ቆጭቆጫ፣ ቃተኛና ፍርፍር፣ ቆሎና ዳቦ ቆሎ ማን ይሆን ያመጣቸው? ሽሮና በርበሬ፣ ድቁስና ሚጥሚጣ፣ አዋዜናስናፍጭ ማን ነበር አስቦ የፈለሰፋቸው? እነዚህን ጥያቄዎች ብንጠይቅ የብሔረሰቦችና የጎሳዎች ስም፣ የአካባቢና የጎጥ ስም እንጂየግለሰቦችን ስም አናገኝም፡፡ እነርሱ ተውጠው ቀርተዋል፡፡
 ልጆቻችን አርአያ ሊያደርጉት፣ ሊከተሉትናሊፎካከሩት የሚችሉት ግለሰብን ነው፡፡ ማኅበርን ወይም ሕዝብን መከተል አይቻልም፡፡ ግለሰቦችን በዋጥናቸውና ባጠፋናቸው ቁጥር፣ለጀግኖቻችን ክብርና አድናቆት በነፈግናቸው ቁጥር ሌላ ጀግና ማግኘት አንችልም፡፡ ሰነፎች ‹ሕዝብ› በሚባል የማይዳሰስ መዋቅርውስጥ ገብተው ይደበቃሉ፡፡ ሕዝብ ተጠያቂነት የለበትምና፡፡ ሰነፎችም ተጠያቂነትን ሲፈሩ ሕዝብ ውስጥ ይደበቃሉ፡፡ እንደ ጀግኖችመሥራት ሲያቅታቸው የጀግኖችን ዋጋ ለሕዝብ ይሰጡና እነርሱም የዋጋው ተቋዳሽ ይሆናሉ፡፡
 እኔም እሑድ ዕለት በተደረገው የኢትዮጵያናየደቡብ አፍሪካ ጨዋታ ያየሁት ይኼንን ነበር፡፡ ቡድኑን አሠልጥኖና መርቶ ለድል ያበቃው አሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው ሳይሆን ሌሎችነበሩ ሲመሰገኑ የነበሩት፡፡ ከሌሊት ጀምረው ወረፋ ያዙት፣ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ለብሰው የደገፉት፣ ጨዋታውን ያስተላለፉት፡፡ለስፖርት ልዩ ፍቅር ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነበሩ ስማቸው ከፍ ከፍ ያለው፡፡ እነዚህ ሁሉ ከፍ እንዲሉ ያደረገው ግን ሰውነትየሚባል አንድ ጀግና ተነሥቶ ነው፡፡ በስታየሙ ውስጥ ግን ‹ሰውነት ሆይ እናመሰግናለን› የሚል ነገር አላየሁም፡፡
 የአፍሪካ ዋንጫ ድሮም ነበረ፤ የዓለምዋንጫ ድሮም ነበረ፤ ከሱዳን ጋር ብዙ ጊዜ ገጥመናል፤ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ደጋግመን ተጫውተናል፡፡ አሁን ማርሹን የቀየረውማነው? ሰውነት የሚባል አንድ ታሪክ ሠሪ ነዋ፡፡ ማንቸስተርዩናይትድ ባለፈው ጊዜ ሃያኛውን ዋንጫ ሲወስድ ስታዲዮሙ ‹ፈርጉሰን ሆይ እናመሰግናለን፤ ፈርጉሰን ጀግና ነው፤ ፈርጉሰንለዘላለም በልባችን ይኖራል› በሚሉ መፈክሮች ተሞልቶ ነበር፡፡ ልክ ነው ፈርጉሰን የማንቸስተርን ታሪክ ለውጠውታል፡፡ ሰውነትምየኢትዮጵያ እግር ኳስን ታሪክ ለውጦታል፡፡
 ምኒሊክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ ዕንቁላል ነበር ይኼን ጊዜ አበሻ
 የተባለውኮ ያለምክንያት አይደለም፡፡ በታሪክ ውስጥ የወሳኝነት ድርሻ ላላቸው ሰዎችክብር ለመስጠት እንጂ፡፡ ሰውነት የሚባል አሠልጣኝ ተወልዶ ይኼው ታሪክ አየን፡፡ ትረካችን ተለውጦ ለአፍሪካ ዋንጫ መብቃትናአለመብቃት፤ ለዓለም ዋንጫ መብቃትና አለመብቃት ሆነ፡፡ ‹ስንት ለዜሮ ይሆን የምንሸነፈው?› የሚለው ሥጋት ቀረ፡፡ ከዚህ በላይምን ጀግንነት አለ? ከዚህ በላይ ምን የገጽታ ግንባታ አለ፡፡
 ተዉ ጎበዝ ይኼ ሰው ጀግና ነው፡፡
 እኛ በጠባያችን አንበሳውን ካዳነው ሰው ይልቅ የገደለውን ጀግና ስለምናደርግ ነውእንጂ፡፡ እኛ በጠባያችን ችግር ሲመጣ ለግለሰቦች፣ ድል ሲመጣ ለጋራ ስለምንወስድ ነው እንጂ፤ እኛ በጠባያችን ማኅበርና ቡድንግለሰብን ስለሚውጥ ነው እንጂ፡፡ ይኼ ሰው ጀግና ነው፡፡ በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በአረንጓዴ ቀለም አሻራውን ያስቀመጠጀግና፡፡
በቅርቡ ስለ እግር ኳስ ሜዳዎች የሥነ ምግባር ችግር በተጠራ ስብሰባ ላይ ‹አሠልጣኝሰውነት መሰደብ የለበትም› ተብሎ ሲነሣ አንድ የእግር ኳሱ ባለሥልጣን ‹አሠልጣኝ ቢሰደብ ምን አለበት? አሠልጣኝን መስደብ ዛሬነው እንዴ የተጀመረው፡፡ ድሮም እነ እገሌና እገሌ ሲሰደቡ ነበሩ›› እያሉ ሲቀልዱ ሰማሁ፡፡ ‹እንኳንም እርስዎ የጤና ጥበቃሚኒስትር አልሆኑ› ብዬ ደስ አለኝ፡፡ የሴት ልጅ ግርዛት ይቅር ሲባሉ ‹ሴት መገረዝ የጀመረችው ዛሬ ነው እንዴ› ይሉ ነበር፡፡ግግን ማስቧጠጥ ይቅር ሲባሉ ‹‹ግግ መቧጠጥ በኛ ዘመን ነው እንዴ የተጀመረው፤ ስንቱ ሲያስቧጥጥ አልነበረም እንዴ›› ይሉነበር፡፡ እንጥል ማስቆረጥ ይቅር ሲባሉ፡፡ እንጥል ማስቆረጥ ድሮም ነበረ፡፡ ምን አዲስ ነገር መጣ›› ይሉን ነበረ፡፡ ‹‹ ያለእድሜ ጋብቻ ይቅር ሲባሉ ‹‹ምነው እገሊትና እገሌ ያለ እድሜያቸው አልነበረም እንዴ የተጋቡት? ዛሬ ምን አዲስ ነገር መጣ››ይሉን ነበር፡፡ እግዜርም ዐውቆ ሰማዩን ዐርቆ ማለት ይኼ ነው፡፡
 ለነ ወልደ መስቀል ኮስትሬ ክብር እየነሣንየኢትዮጵያ ሩጫ እንዲያድግ የምንመኝ የዋሐን ጀግናን መግደልና ታሪክ ሠሪን ማጥፋት ለምዶብናል መሰል፡፡ በላይ ዘለቀን ገደልን፤አክሊሉ ሀብተ ወልድን ገደልን፣ አቤ ጎበኛን ገደልን፣ በዓሉ ግርማን ገደልን፣ አበበ አረጋይን ገደልን፣ ዮፍታሔ ንጉሤንገደልን፣ አለቃ ታየን ገደልን፣ ንግሥት ዘውዲቱን ገደልን፣ ከበደ ሚካኤልን ሀብታቸውን ነጥቀን በቁማቸው ገደልን፣ ሐዲስዓለማየሁን መጽሐፋቸውን እያሳተምን የእርሳቸውን ንብረት ቀምተን በቁማቸው ገደልን፣ ስንቶቹ ዘፈናቸውን እየሰማን እነርሱን ግንገደልን፤ ስንቶቹን ቲያትራቸውን እያየን እነርሱን ግን ገደልን፤ ስንቱን ስንቱን ገደልን፡፡
አገዳደላችን በሦስት መንገድ ነው፡፡አሳቢውን በማጥፋት፣ ሃሳቡን በማጥፋትና ሃሳቡን በመንጠቅ፡፡ ስንት አሳቢዎች ‹ዓሣውን ለማጥፋት ባሕሩን ማድረቅ› በሚለውብሂላችን ምክንያት ከነ ሃሳባቸው ተገደሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ሃሳባቸው እንዳይሰማ፣ እንዳይነበብ፣ እንዳይሳካና እንዳይታይ በማድረግተገደሉ፡፡ በሌላ በኩልም አሳቢውን ዝም አሰኝቶ ሃሳቡን በመንጠቅና አሳቢው ተንገብግቦ እንዲሞት በማድረግ ስንት ጀግናአጥተናል፡፡ የነ አያ እገሌ ፈጠራዎች፣ ሃሳቦች፣ ድርሰቶች፣ ግኝቶች፣ ፍልስፍናዎች ተነጥቀው የነ አቶ እገሌ ሆነው ቀርተዋል፡፡የነ አያ እንትና ታሪክ ለነ ክቡር እንቶኔ ተሰጥቷል፡፡ የአሳቢዎችን ጥቅም ክብርና ዝና፣ አቀንቃኞች ወስደውት ‹‹የበሬንምስጋና ወሰደው ፈረሱ›› ተብሎ ተዘፍኗል፡፡
 አሁንም ሺ ‹ሰውነቶች› ወደፊት ተነሥተውየሀገራችንን የስፖርት መልክ እንዲቀይሩት ከፈለግን የዛሬውን ሰውነት እናወድሰው፡፡ ሰውነት ጀግና ነው፡፡ ታሪክ የለወጠ፣ሕዝብን ያስዘመረ፣ አገርን አንድ ቋንቋ ያናገረ፤ ቡድኑን መርቶ ውጤት የዘወረ፣ ኃላፊነትን ተሸክሞ ሀገር ያስከበረ፡፡ ከዚህበኋላ ያለው ውጤት እንኳን ቢቀየር ሰውነት ግን የኢትዮጵያን እግር ኳስ ወደ አንድ አይተነው ወደማናውቀው የታሪክ ምዕራፍአድርሶታል፡፡ይኼ ሰው ጀግና ነው፡፡ ሃያ አራት ሰዓት ስታዲዮም በር ላይ የተሰለፍነው ሰውነት የሚባል ሰው ተስፋ ያለው ቡድንስለሠራኮ ነው፡፡ እንዲያ ስታዲዮም ገብተን የደገፍነው ሰውነት የሚባል ሰው የሚደገፍ ቡድን ስላዘጋጀኮ ነው፡፡
 ከነ ስሕተቱም፣ ከነ ጠባዩም፣ከነጉድለቱም፡፡ ይኼ ሰው ጀግና ነው፡፡

Comment   See all comments

Wednesday, June 5, 2013

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በአባይ ጉዳይ ላይ

ዛሬ ደግሞ…

ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም
ጦርነት እንኳን ገና በልቶ ላልጠገበ ሕዝብና ለጥጋበኞቹም አይመችም፤ የተራበ ሕዝብ በጠገቡ መሪዎች ሲነዳ ግን ጦርነት ለአጉል ጀብደኛነት ዝና የሚጠቅም መስሎ ይታያቸዋል፤ ከኤርትራ ጋር ጦርነት ለመግጠም በሚያሰፈስፉበት ጊዜ በርቱ እያሉ የሚያቅራሩ ሞልተው ነበር፤ ዛሬ አቀራሪዎቹም ሆኑ ጀብደኖቹ በኤርትራ ጦርነት ያለቀባሪ ስለቀሩት ሰዎች፣ ጠዋሪ ስላጡ እናቶችና አባቶች፣ አሳዳጊ ስለሌላቸው ልጆችና አካለ-ጎደሎ ለሆኑት የሚያስብላቸው አለ ወይ? የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት መነሣትና በኢጣልያ የግራዚያኒ ሐውልት እንዳይሠራ የተጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎ ለሰልፍ የወጡትን አስሮ ያሳደረ አገዛዝ ለአገራቸው ለሞቱት ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዋጋ በመጠኑም ቢሆን ያሳያል፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ሲወዱ ራሳቸው በልጽገው ለልጆቻቸው ብልጽግናን እንዲያወርሱ ሕይወታቸውን ቢጠብቁ ለአገራቸውም ክብር ይሆናሉ፡፡
ለፍቅር መተዋወቅ እንደሚያስፈልግ ሁሉ ለጠብም መተዋወቅ ያስፈልጋል፤ የተሟላ መረጃ ቢኖረን የጥንት ታሪክ እየጠቀስን ሰዎችን ለጦርነት እንቀሰቅስም ነበር ብዬ አምናለሁ፤ ስለዚህም አንዳንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ላቅርብ፤ —
1. የግብጽ የጦር ኃይል በዓለም አሥረኛ ነው፣ በአፍሪካና በመሀከለኛው ምሥራቅ የሚወዳደረው የለም፤ አንድ ሚልዮን ተኩል ያህል የጦር ኃይል አለው፤ በዓየር ኃይልም ከዓለም አሥራ አራተኛ ነው፤ በታንክ ብዛት አራተኛ ነው፤ በባሕር ኃይል ሰባተኛ ነው፤ በጦር በጀት አርባ ሦስተኛ ነው፤
2. በኢትዮጵያ ዙሪያ ጂቡቲ፣ ሶማልያ፣ ሱዳን የአረብ ማኅበር አባሎች በመሆናቸው ለግብጽ ማኅበረተኞች ናቸው፤ በወያኔ ፈቃድ የተገፋችው ኤርትራም የዚሁ ማኅበር ታዛቢ አባል ነች፤ ከቀይ ባሕር ማዶ ያሉት አገሮች ሁሉ ሀብታሙንና ኃይለኛውን ሳኡዲ አረብያንም ጨምሮ የግብጽ ማኅበርተኞች ናቸው፤ በዚህ ሁሉ መሀከል የተከታተፈች ኢትዮጵያ ብቻዋን ነች፤
3. የቤንዚን ሀብትና ከሀብቱም ጋር የሚገኘውን ወዳጅና ጡንቻ አንርሳ፤
ይህ ማስታወሻ ለማስፈራራት አይደለም፤ ማስፈራራትን አላውቅበትም፤ እንዲያውም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ‹‹አትፍሩ›› ብሏቸዋል ተብዬ ተከስሼ ታስሬአለሁ፤ ስለዚህ አላስፈራራም፤ ጦርነት ከመጣብን ልናስቀረው እንሞክር፤ ሌላው ቢቀር እንድንዘጋጅ ጊዜ እናገኛለን፤ ገፍቶ ከመጣ ግን እንቋቋመዋለን፤ ለጦርነት አንቸኩል፤ ለኤርትራም ጊዜ ተናግሬ ነበር፤ የሰማኝ የለም፤ ጥጋብ ላይ ያሉ የሚርባቸው ዝና ነው፤ የሚያገኙት ግን ውርደትን ነው፡፡

Saturday, June 1, 2013

Egypt: Scores Protest At Ethiopia Embassy to Demand Expelling Ambassador by Abby


Scores of demonstrators staged a protest on Friday at the Ethiopian embassy headquarters in Cairo to demand expelling the Ethiopian ambassador to Egypt and call for halting the Renaissance Dam project, al-Masry al-Youm newspaper reported.
Ethiopia has begun implementing a project to build a $4.7 billion dam. The project entails diverting the Blue Nile which may affect downstream countries.
The demonstrators chanted slogans condemning Ethiopia's policies and lifted banners attacking the dam building process.
The embassy prevented the protesters from burning the Ethiopian flag after one demonstrator attempted to down the flag.
Source:al-Masry al-Youm
Abby | May 31, 2013 at 3:07 pm | Tags: Blue NileEgyptEthiopiaNile | Categories: Africa | URL: http://wp.me/p2gxmh-1VI
Comment   See all comments

Wednesday, May 29, 2013

ማንዴላ በመጨረሻዋ የፍርድ ቀን ለዘረኞች ያለው Print PDF ሉሉ ከበደ


Former South African president Nelson Mandelaኢትዮጵያን በቁጥጥሩ ስር ያዋላት የትግራይ ዱር አራዊት ቡድን ዛሬ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየጫነ ያለውን የአፓርታይድ አይነት ስራት እነ ኒልሰን ማንዴላ ከደቡብ አፍሪካ ምድር ከስሩ መንግለው ለመጣል እጅግ ብዙ መስዋእትነትና ምእተ አመት የሚጠጋ ጊዜ ነበር የወሰደባቸው።
ምእራቡም ሆነ ምስራቁ አለም ለአፍሪካውያኑ የነጻነት ትግል ፈጥኖ እውቅናና ድጋፍ አለመስጠቱና በተለይ ምእራቡ ከነጮቹ ጋር ተመሳጥሮ በተዘዋዋሪ እነሱን መደገፉ ትግሉ ረጅም ጊዜ እንዲወስድና የነጻነቱም ቀን እንዲርቅ ቢያደርገውም፤ በትግሉ መሪዎች ፍጹም ቆራጥነትና ለሞት መዘጋጀት እንዲሁም በህዝቡ አንድነትና ጽናት አፓርታይድ ተወግዶ የደቡብ አፍሪካ ህዝብ መሪ መሾምና መሻር ችሏል በነጻነት።
እርግጥ  በኢትዮጵያ የበላይነቱን የተቆጣጠሩት የህውሀት ዘረኛ ሰዎች ከደቡብ አፍሪካ ነጮች ጋር ሊያነጻጽራቸው የሚያስችል ስልጣኔና ለነጩ አለም ቀረቤታ አላቸው ባንልም፤ ለሀያላኑ መንግስታት በሎሌነት እስከቀረቡና የሚታዘዙትን እስከፈጸሙ ድረስ ድጋፋቸውን እንደማይነፍጓቸው ባይናችን እያየነው በመኖር ላይ ነን። ይሁንና ከሁሉም በላይ ለወያኔ መቅበጥና ከልከ ማለፍ፤ ለነሱ የልብልብ ማግኘትና በላያችን ላይ መግነን ተጠያቂው እራሳችን ነን። አንድ ሆነን በቶሎ እነሲህን የኢጣሊያ ጣእረመንፈስ ነጋሲያን ፋሺሽቶች ማስወገድ ተስኖን የህዝቡን ደም እየጠቡ፤ የሀገሪቱን ሀብት እየዘረፉ መወፈራቸውን ቀጥለዋል።
የደቡብ አፍሪካውን የጥቂት ነጮች አፓርታይ መንግስት ለማስወገድ ኤ ኤን ሲ በ1912 ዓም ኢ ኤ አ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ከአርባ አመት በላይ ሰላማዊ የትግል ስልት ነበር ሲከተል የቆየው። ህዝባዊ እንቢታ፤ እቤት የመዋል አድማ፤ የሥራ ማቆም አድማ፤ ይለፍ ወረቀት ሳይዙ በጅምላ ሆ ብሎ የተከለከለ ቦታ ሄዶ መታሰር፤ ወዘተ…. ያሁሉ ግማሽ ምእተ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ የተካሄደው ሰላማዊ ትግል የህዳጣኑን መንግስት ጭቆናና ጭካኔ አባባሰው እንጂ ለደቡብ አፍሪካ ህዝብ የፈየደው ነገር አልነበረም።
ኋላ ላይ ግን እነማንዴላ ሀሳባቸውን ለመቀየር ተገደዱ። ሰላማዊው ትግል በትጥቅ ትግል መደገፍ እንዳለበት አመኑ። ይህንንም ወሰኑ። የሽምቅ ውጊያ ለመጀመር በርካታ የ ኤ ኤን ሲ ታጋዮች ማንዴላን ጨምሮ ወደተለያዩ ሀገሮች ለወታደራዊ ስልጠና ተሰማሩ። ማንዴላም ወደ ኢትዮጵያ አቀና። እናም እ ኤ አ በ1961 ዓም የ ኤ ኤን ሲ ወታደራዊ ክንፍ በማንዴላ መሪነት ተመስርቶ በመንግስቱ የኢኮኖሚና ወታደራዊ ተቋማት ላይ አደጋ መጣል ጀመረ።
የነጮቹ መንግስት የትግሉ ትኩሳት እየተሰማው በመጣ ቁጥር ወያኔ እንደሚያደርገው በየጊዜው አዳዲስ ህግ ማውጣትና ድርጅቶችን ሁሉ ማገድ፤ ህዝቡንና ታጋዮቹን ማሳደድ፤ ማሰርና ማዋከቡን በሙሉ ሀይሉ ቀጠለ። የትግሉን መሪዎች የደረሰበትን በቁጥጥር ስር አዋለ ያልተያዘውም ከሀገር መሰድድና ትግሉን ከጎረቤት ሁኖ መምራት ግድ ሆነበት። የታሰሩት መሪዎች የሀገር ክህደትና መንግስትን በሀይል ለማስወገድ መሞከር  በሚል ክስ ለሞትና ለድሜልክ እስራት ያዘጋጃቸው ጀመር አፓርታይድ ።
እ ኤ አ አቆጣጠር 1962 ዓም ማንዴላ ያለፍቃድ ከሀገር ወተሀል፤ ህዝብን ለአድማ አነሳስተሀል ተብሎ አምስት አመት ተፈርዶበት እስር ላይ እንደነበረ ነበር ይህ አዲሱ ክስ የተደረበለት። ከዘረኞች ፍርድ ቤት ለነጻነት ታጋዮች ፍትህ የለምና ከረጅም ጌዜ ከንቱ ክርክር በኋላ እነማንዴላ ጥፋተኞች ናቸው ብሎ ነጩ ዳኛ ፈረደ። የፍርዱን ልክ ከመበየኑ በፊት ተካሳሾች የፍርድ ማቅለያ ክርክራቸውን እንዲያሰሙ በታዘዙት መሰረት ማንዴላ አራት ሰአት የፈጀ ታሪካዊና ድፍረትና ሀቅ የሞላበት ንግግር  በጽሁፍ  አቅርቦ ነበር።
በዚያ የመጨረሻዋ የፍርድ ቀን ለችሎቱ የተናገረውን ማንዴላ በጻፈው መጽሀፍ ውስጥ አሳጥሮ አቅርቦታል። ያ የአላማ ጽናትና ቆራጥነት የተሞላበት ንግግር አንዷለም አራጌን እስክንድር ነጋን ያስታውሳል። በሀገራችን ካለው ሁኔታ ጋር ምን ያህል እንደሚመሳሰል ለማስገንዘብ ወደ አማርኛ መልሸዋለሁ።
ማንዴላ ተከሳሽ ሳጥን ውስጥ ቆሟል። ተራው ደርሶ የክርክሩን ማክተሚያ ያነብ ጀመር።
አንደኛ ተከሳሽ ነኝ። በባችለር ኦፍ አርት የመጀመሪያ ዲግሪ አለኝ። ጆሀንስበር ውስጥ ከሚስተር ኦሊቨር ታንቦ ጋር በሽርክና ሆነን ለተወሰኑ አመታት የጥብቅና ሙያ ሰርቻለሁ። በ 1961 ግንቦት መጨረሻ ላይ ህዝብን ለአድማ ማነሳሳት እና ካለፍቃድ ከሀገር መውጣት በሚሉ ክሶች የአምስት አመት ፍርድ ተፈርዶብኝ በእስር ላይ የምገኝ ፍርደኛ ነኝ።
ነሀሴ ወር 1962 ለእስር እስከተዳረኩበት ድረስ በጉዳዩ ከፍተኛ ሚና የተጫወትኩና ኡምኮንቶ ሱዚዌ፤ የኤ ኤን ሲን ወታደራዊ ክንፍ ለማደራጀት ከረዱት መካከል አንዱ መሆኔን እቀበላለሁ።
ከሁሉ በፊት መንግስት በመግቢያው ላይ በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደው ትግል፤በውጭ ሀይሎች ወይም  በኮሙኒስቶች ተጽእኖ ስር ያለ ነው የሚለውን ሀሳብና ግምት ባጠቃላይ ስህተት ነው ለማለት እሻለሁ። ያደረኩትን ነገር አድርጌአለሁ። እንደ ግለሰብም እንደ ህዝብ  መሪነትም። ይህንን ሳደርግ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ባለኝ ተሞክሮና በፍጹም አፍሪካዊ ኩራትና ክብር እንጂ የውጭ ወገኖች ባሉትና በሚሉት ተመርቼ ተነሳስቼ አይደለም።
በወጣትነት ዘመኔ ትራንስኪ ውስጥ የጎሳችን  አረጋውያን ስላለፈው የጥንት ዘመን ታሪክ ወግ ሲነግሩን እሰማ  ነበር። ሽማግሌዎች ከሚያወሷቸው የሗላ ታሪካችን ከኔ ጋር የሚያመሳስሉት የነበረው “ ያባትን ሀገር “ ለመከላከል ያደረጓቸውን ጦርነቶች ሲያነሱ’ የእነ ደንጌ እና ባንባታ፤ ሂንሳና ማካና፤ ኩንቲና ዳላሲል፤ ሞሾሾና ሲሁሁኔ ስሞች ሲጠቀሱ፤ የመላው አፍሪካ ክብርና ኩራት ሆነው ይሞገሱ ይወደሱ ነበር። ያኔ ያን ታሪክ ሥሰማ ተስፋ አደርግ  ነበር። ለህዝባችን የነጻነት ትግል የበኩሌን ጥቂት አስትዋጾ እንዳበረክት፤ ህይወት አንድ አጋጣሚ ትቸረኝ ይሆናል እያልኩ። በዚህ ጉዳይ ላይ ክስ ሲመሰረትብኝ እንደጥፋት የተጠቀሰውን ሁሉ እንዳደርግ መነሻና ግፊት የሆነኝ ይኸው የኋላ ታሪካችን ነበር።
ይህን እያልኩ የአመጹን  ጥያቄ አነሳና ፈጥኜ ጥቂት ዘለግ ላለ አፍታ ያለውን  ነገር ላስረዳ ግድ ይለኛል። እስካሁን ለችሎቱ ከተነገሩት ነገሮች ገሚሱም እውነት ገሚሱም እውሸት ናቸው። የሆነው ይሁንና ሻጥር ( በመንግስት የኢኮኖሚ ተቋማት ላይ አደጋ መጣል) ማቀዴን አልክድም። ይህንንም ሳቅድ በግዴለሽነትና በዘፈቀደ መንፈስ ተሞልቼ ወይም ደግሞ አመጽን የምወድ ሰው ሁኜ አይደለም። የረጅም ዘመን አንባገነንነት ያስከተለውን የነጮች  ብዝበዛና ጭቆና የተንሰራፋበትን የፖለቲካ ሁኔታ በሰከነ  አእምሮና  በተረጋጋ ሁኔታ ስገመግም ከኖርኩ በኋላ ነው በውጤቱ ይህን እርምጃ ለማቀድ የወሰንኩት።
ለችሎቱ ለማስረዳት የሞከርኩት ይህን የአመጽ እርምጃ ስንወስድ ሀላፊነት ሳይሰማንና ያልተጠበቀ ውስብስብ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል  ሳናስብ ቀርተን እንዳልነበር ነው። አንድም አይነት ጉዳት በሰው ህይወት ላይ እንዳይደርስ ለማድረግ መወሰናችንን አጽንኦት ሰጥቼ ነበር።
እኛ ኤ ኤን ሲዎች ምንጊዜም የቆምነው ከዘረኝነት የጸዳ ዲሞክራሲ  እንዲሰፍን ነው። ጎሳዎችን እስካሁን ካሉበት ሁኔታ  በባሰ መልኩ ከሚያራራርቅ ማናቸውም ድርጊት እንታቀባለን። ጠጣሩ እውነታ ወይም ሀቅ ግን የሀምሳ አመት ሰላማዊ ትግል ለአፍሪካውያን ያተረፈው ያስገኘው ነገር ቢኖር እየበዛ እየበዛ የመጣ የመጨቆኛ ህግና እያነሰ እያነስ የሄደ መብት ብቻ ነው። ለዚህ ችሎት ይህን መረዳት ቀላል ላይሆን ይችላል። ህዝቡ ለረጅም ዘመን ሀይል ስለታከለበት አመጽ ሲነጋገር መኖሩ እሙን ነው። የአመጽን አማራጭ ተተው በሰላማዊ ትግሉ እንዲቀጥሉ እኛ የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች ብንመክርም፤  ከነጮች ጋር ተዋግተው የሀገራቸው ባለቤት ስለሚሆኑባት ቀን ይወያያሉ። ግንቦትና ሰኔ 1961 ዓም ገሚሶቻችን ይህን እየተነጋገርን በነበረ ወቅት ከዘረኝነት የጸዳ መንግስት እንዲኖረን ለማድረግ የሰላማዊ ትግሉ ፖሊሲ ምንም ውጤት እንዳላመጣ መካድ አልተቻለም ነበር። ተከታዮቻችን በዚህ ፖሊሲ ላይ መተማመን እያቃታቸው፤ የሀይልን አመጽ እንደአማራጭ በአእምሮ ውስጥ ማጎልበት ጀመሩ። የሚረብሽ የአሽባሪነት እሳቤ።
የ ኤ ኤን ሲ ወታደራዊ ክንፍ ህዳር 1961  ዓም ተመሰረተ። ይህን ውሳኔ ስናስተላልፍና በተከታታይ እቅዳችንን ስንነድፍ የ ኤ ኤን ሲ ሌጋሲ ከአመጽ  በጸዳ ትግል ህብረ ዘርነት እውን የሚሆንበት ሀሳብ አብሮን እንዳለና እንደያዝነው ነበር። ሀገሪቱ በጥቁሮችና   በነጮች መካከል ወደሚቀሰቀስ የርስበርስ ጦርነት በሚያስኬድ ጎዳና ላይ እየተጓዘች እንዳለች ይሰማናል። ነገሩን የምንመለከተው በማስጠንቀቂያ ደወል ነው። የርስ በርስ ጦርነት ማለት ኤ ኤን ሲ የቆመለትን እሴት ማውደም ማለት  ነው። የርስ  በርስ ጦርነት ከተነሳ ማናቸውም ዘር ሰላም የማግኘት እድሉ እጅግ የከፋ ይሆናል። ጦርነት የሚያስከትለውን የከፋ ነገር ለማወቅ በደቡብ  አፍሪካ ታሪክ ውስጥ በቂ ምሳሌ አለን። በደቡብ አፍሪካ አንግሎ – ቦር  ጦርነት ያስከተለው ጠባሳ ለመሻር ከሀምሳ አመት በላይ ወስዷል። ዘር በዘር ላይ ተነስቶ ከሁሉም በኩል በቀላል የማይገመት ህዝብ በሚያልቅበት ሁኔታ ጦርነት ቢካሄድ ጠባሳው ለመሻር ምን ያህል ዘመን ይፈጃል?
በተግባር አይተን እንዳመነው፤ አመጽ፤ ለመንግስት፤ ህዝባችንን በጅምላ መጨረስ የሚያስችል ገደብ የሌለው እድል ይሰጠዋል። በርግጥም የደቡብ አፍሪካ ምድር፤ አፈር፤ ዱሮ በንጹሀን አፍሪካውያን ደም ጨቅይቷል። ሀይልን በሀይል መክተን ራሳችንን ለመከላከል የመዘጋጀት የረጅም ጊዜ ስራ መስራት ተግባራችን እንደሆነ ይሰማናል። ጦርነት አይቀሬ ከሆነ ጦርነቱ መመራት ያለበት ለህዝባችን ሁኔታ በተመቸ መልኩ እንዲሆን እንሻለን። ለኛ አንድ ነገር ያጎናጽፋል፤ እናም በሁለቱም ወገን አነስተኛ የህይወት መስዋእትነት የሚያስከፍል ይሆናል  ብለን ያልነው የሽምቅ ውጊያ ነው። ለዚሁ ዝግጅት ለማድረግ ወሰንን።
ነጮች  በሙሉ የግዴታ ወታደራዊ ስልጠና ይሰጣቸዋል። ለጥቁሮች ይህ ነገር አይደረግም። የሽምቅ ውጊያውን ሊመሩ የሚችሉ፤ ወታደራዊ ስልጠና ያላቸው ሀይሎችን መገንባት መሰረታዊ እሳቤአችን ነው። ሳንዘገይ ለዚህ መዘጋጀት አለብን።
ውይይታችን በዚህ ደረረጃ ላይ እንዳለ በአፍሪካ ሀገሮች ልዩ ልዩ ጉባኤዎችን ለመካፈልና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ካገር እንደወጣሁ አስረዳሁ። የሽምቅ ውጊያ ቢጀመር ከህዝቤ ጋር አብሬ ለመቆም ለመዋጋት እንድችል፤ ወታደራዊ ስልጠና መውሰዴን ተናገርኩ።( ማንዴላ ወታደራዊ ስልጠና የወሰደው ኢትዮጵያ ነበር ) በ ኤ ኤን ሲና በወታደራዊ ክንፉ መካከል ያለውን የሚለያቸውን መስመር ለችሎቱ ገለጽኩ። ሁለቱ እንዴት የተለያዩ መሆን እንዳለባቸው እንዳደረግን ተናገርኩ። ፖሊሲያችን  ነበር። ተግባር ላይ ለማዋል ቀላል አልነበረም። በህግ መታገድ መታሰር ሁሉ ስለነበረ ሰዎች በሁለቱም ውስጥ መስራት  ነበረባቸው። የኮሙኒስት ፓርቲውና ኤ ኤን ሲ አንድ ዓላማ አላቸው የሚለውን የመንግስት ክስ ተከራሬዋለሁ።
የ ኤ ኤን ሲ ርእዮተ ዓለም መርህ ምን ጊዜም አፍሪካዊ  ብሄረተኝነት ነው። “ ነጭን ወደ ባህር ንዳው “ የሚለው አይነት የአፍሪካ ብሄረተኝነት ጩኽትም አይደለም። ኤ ኤን ሲ የቆመለት አፍሪካዊ ብሄረተኝነት፤ አፍሪካውያን በምድራቸው ምሉእ ሆነው በነጻነት እንዲኖሩ የሚያስችል ጽንሰ ሀሳብ ነው። የ ኤ ኤን ሲን ዓላማና አቋም የሚያንጸባርቀው ሰነድ በ ኤ ኤን ሲ የጸደቀው የነጻነት ቻርተር ሰነድ ነው። በምንም መልኩ የሶሻሊስት መንግስት እቅድ አይደለም። ለሀገሪቱ ታሪክ  ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ መዋቅር ኤ ኤን ሲ መቼም አብዮታዊ ለውጥን ደግፎ አያውቅም። እስከማውቀው የካፒታሊዝምንም ስራት አውግዞ አያውቅም።
ከኮሙኒስት ፓርቲው በተለየ መልኩ ኤ ኤን ሲ በአባልነት አፍሪካውያንን ብቻ ነው የሚቀበለው። ዋና አላማውና ግቡም አፍሪካውያን አንድነትና የተሟላ የፖለቲካ መብት እንዲቀዳጁ ማድረግ ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ ዋና አላማ  በሌላ መልኩ ካፒታሊስቶችን ማስወገድና በሰራተኛው መደብ መንግስት መተካት ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ ለመደብ ልዩነት አጽንኦት ሲሰጥ ኤ ኤን ሲ በህብር አብረው የሚጓዚበትን ሁነት ይፈልጋል።
እርግጥ ነው በ ኤ ኤን ሲና  በኮሙኒስት ፓርቲው መካከል የቅርብ ትብብር አለ። ትብብሩም የጋራ የሆነ ግብ  መኖሩን የሚያረጋግጥ ነው።  ጉዳዩ የነጮችን የበላይነት ማስወገድ  ነው። ይህ ማለት በሁሉም አቅጣጫ የጋራ አቋምና የጋራ ግብ እንዳለ ያረጋግጣል ማለት አይደለም። የአለም ታሪክ በተመሳሳይ ምሳሌዎች የተሞላ ነው። ምናልባትም ስሜት የሚሰጠው ስዕል፤ ታላቋ ብሪታንያ፤ አሜሪካና ሶቬት ህብረት ናዚ ሂትለርን ለመውጋት ያደረጉት ትብብር ነው። ሂትለር ብቻ ካልሆነ በስተቀር፤ ቸርችልን ወይም ሩዝቬልትን ወደ ኮሙኒስትነት ተቀየሩ ብሎ ማንም ሰው ለመናገር የሚደፍር አይኖርም። ወይም ደግሞ አሜሪካና እንግሊዝ የኮሙኒዝምን ስራት ለማስፈን እየሰሩ ነው የሚል አይኖርም። ልምድ ያላቸው አፍሪካውያን ፖለቲከኞች ኮሚኒስቶችን ለምን ጥሩ ወዳጅ አድርገው እንደሚቀበሏቸው ስር የሰደደ መጥፎ አመለካከት በነሱ ላይ ላላቸው የደቡብ አፍሪካ ነጮች መረዳት በጣም ሊከብዳቸው ይችላል። ለኛ ግን ምክንያቱ ግልጽ ነው። በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ለብዙ አስርት አመታት ጥቁሮችን እንደሰው ለማስተናገድ የተዘጋጁ፤ ኮሙኒስቶች ብቻ ነበሩ። እኩልነታቸውን የተቀበሉ፤ አብረውን ለመብላት ለመጠጣት የተዘጋጁ፤ አብረውን ለማውጋት፤ አብረውን ለመስራትና ለመኖር የተዘጋጁ። በዚህም ምክንያት ዛሬ ብዙ አፍሪካውያን ናቸው ኮሙኒዝምን ከነጻነት ጋር እኩል አድርገው የማየት ዝንባሌ ያላቸው።
እኔ ምንጊዜም ራሴን እንደአፍሪካዊ አርበኛ የምመለከት እንጂ ኮሙኒስት አለመሆኔን ለችሎቱ አስረዳሁ። መደብ አልባ ስራት  በሚል አስተሳሰብ መማረኬን ወይም ደግሞ የኮሙኒስት አስተሳስብ ተጽእኖ እንዳሳደረብኝ አልካድኩም።
ካነበብኳቸው የኮሙኒዝም ጽሁፎችና ከተወያየሗቸው ማርክሲስት ግለሰቦች እንደተረዳሁት ኮሙኒስቶች የምእራባውያንን የፓርላማ ስራት ኢዲሞክራሲያዊና አድሀሪ እንደሚሏቸው ተገንዝቤአለሁ። በተቃራኒው ግን እኔ የዚያ አይነቱ አሰራር አድናቂ ነኝ።
ማግና ካርታ ( መሰረታዊ መብት ማረጋገጫ ሰነድ)፤ ፔቲሽን ኦፍ ራይት፤ ቢል ኦፍ ራይትስ፤ የሚባሉት ሰነዶች  በመላው ዓለም የሚገኙ ዲሞክራቶች ዘንድ በክብር የሚያዙ ሰነዶች ናቸው። ለብሪታንያ የፖለቲካ ተቋማት ታላቅ አክብሮት አለኝ። ለሀገሪቱ የፍትህ ተቋማትም እንደዚያው። የብሪያንያን ፓርላማ በዓለም ከፍተኛው ዲሞክራሲያዊ ተቋም አድርጌ  ነው የምመለከተው። የፍትህ ተቋማቷ ራስ ገዝነትና ያለ ወገንተኝነት መስራት አድናቆቴን ሳያጭሩ የቀሩበት ጊዜ የለም። የአሜሪካን ኮንግረስ፤ የሀገሪቱ ስልጣን ክፍፍል፤ የፍትህ ተቋማቷ ራስ ገዝነት ተመሳሳይ አድናቆት በውስጤ ያጭራሉ።
በደቡብአፍሪካ ውስጥ በጥቁሮችና  በነጮች ህይወት መካከል ያለውን አስደንጋጭ ልዩነት ዘረዘረኩ። በትምህርት፤ በጤና፤ በገቢ፤ በየፈርጁ ጥቁሮች በህይወት ለመቆየት ብቻ  በሚያስችል ደረጃ ሲኖሩ፤ ነጮች በአለም ያለውን ከፍተኛ ደረጃ  ይኖራሉ። እናም ህይወት በዚሁ መልኩ እንድትቀጥል የማድረግ ዓላማ አለ። “ነጮች” አልኩ። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ያሉት ጥቁሮች በሌላው አፍሪካ ካሉት ጥቁሮች የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ ናቸው ብለው ያስባሉ። የኛ እሮሮ አልኩ፤ ከሌላው የአፍሪካ ህዝብ ጋር ስንነጻጸር ድሆች ነን አይደለም። በሀገራችን ውስጥ ካሉት ነጮች ጋር ስንነጻጸር ድሆች ነን ነው። ይህንን የተዛባ ሁኔታ እንዳናርም እንዳናስተካክል በህግ ተከልክለናል ነው።
አፍሪካውያን በሀገራቸው ክብር ያጡበት ሁኔታ ነጮችን የበላይ የማድረጉ ፖሊሲ ቀጥተኛ ውጤት ነው። የነጮች የበላይ መሆን የጥቁሮችን የበታችነት ያስከትላል። የነጩን የበላይነት ለመጠበቅ የሚወጣው ህግ ይህን እምነት ስር እንዲሰድ ያደርገዋል። በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ማናቸውም ዝቅተኛ ስራ  በጥቁሮች ነው የሚሰራው። አንድ ነገር መነሳት ወይም መጽዳት ካለበት  ያን ስራ እንዲሰራለት ነጩ ጥቁሩን ገልመጥ ገልመጥ ብሎ ይፈልገዋል። አፍሪካዊው የርሱ ተቀጣሪ ሆነም አልሆነም።
ድህነትና የቤተሰብ መፍረስ የሚያስከትሉት ነገር አለ። የሚሄዱበት ትምህርት ቤት ስለሌላቸው፤ ወይም ትምህርት   ቤት እንዲውሉ የሚያስችል ገንዘብ  ወላጆቻቸው ስለሌላቸው፤ ህጻናት በየጎዳናው ሲንከራተቱ ይውላሉ። እቤት ውስጥም ተገኝተው ልጆቻቸው የት እንደሚውሉ ሊያዩ የሚችሉ ወላጆች የሉም። እናትም አባትም ያውም ሁለቱም ካሉ ቤተሰቡን በህይወት ለማቆየት ስራ  ብለው ውጭ መዋል አለባቸው። ይህ የወደቀ የሞራል ደረጃን ያስከትላል። በፖለቲካ  ብቻ ሳይሆን  በየአቅጣጫው ህገወጥነት፤አመጽና ሁከት እንዲንሰራፋ ያደርጋል።
አፍሪካውያን   በመላዪቱ ደቡብ አፍሪካ እኩል ድርሻ እንዲኖራቸው ይሻሉ። በህብረተሰቡ ውስጥ የደህነነት ዋስትናና ድርሻ እንዲኖራቸው ይሻሉ። ከሁሉም በላይ እኩል የፖለቲካ መብት እንዲኖረን እንሻለን። ያለዚህ መብት ስንኩልነታችን ዘለአለማዊ ነው የሚሆነው። በዚህች ሀገር ውስጥ ላሉት ነጮች ይህ አብዮታዊነት እንደሚመስላቸው አውቃለሁ። ምክንያቱም ብዙሀኑ መራጭ የሚሆነው ጥቁሩ አፍሪካዊ ስለሚሆን ነው ነጩ ዲሞክራሲን እንዲፈራ የሚያደርገው።
ይህ ኤ ኤን ሲ የሚዋጋለት ጉዳይ ነው። ትግላቸውም እውነተኛ ብሄራዊነት ነው። ባፍሪካውያን በራሳቸው ተሞክሮና በደረሰባቸው ስቃይ የተቀሰቀሰ የአፍሪካ ህዝቦች ትግል ነው። በህይወት የመኖር መብት ትግል ነው።
ንግግሬን አነበብኩ። እዚህች ነጥብ ላይ እንደደረስኩ ወረቀቶቼን ተከላካይ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጥኩና ፊቴን ወደ ዳኛው መለስኩ። ችሎቱ ፍጹም ጸጥ እረጭ አለ። የመጨረሻዋን ንግግር ከትውስታዬ ስናገር ፊቴን ከዳኛ ዴዊት ላይ ዘወር አላደረኩም ነበር።
በህይወት ዘመኔ ለዚህ የአፍሪካ ህዝብ ትግል ህይወቴን አሳልፌ ሰጥቻለሁ። የነጮችን የበላይነት እየተዋጋሁ ነው። የጥቁሮችን የበላይነት እየተዋጋሁ ነው። ሁሉም ሰው ተዋህዶ፤ ሰምሮና አብሮ እኩል እድል እየተጋራ አንድ ላይ መኖር አለበት የሚል አስተሳስብ አለኝ። የምኖርለትና እንደግብም ልለቀዳጀው ተስፋ የማደርግበት አስተሳሰብ  ነው። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘም ለመሞት የተዘጋጀሁለት አስተሳሰብ ነው።
አሁን  በችሎቱ ፍጹም ጸጥታ ሆነ። የመጨረሻዋን ከተናገርኩ  በኋላ ቁጭ አልኩ። በችሎቱ ውስጥ የነበሩ ታዛቢዎች ሁሉ አይናቸው እኔ ላይ ያረፈ መሆኑ  ቢሰማኝም ቤቱ ውስጥ ወዳለው ህዝብ ዘወር ብየ አላየሁም። ጸጥታው ለበርካታ ደቂቃዎች የዘለቀ  ቢመስልም ግን ምናልባትም ከሰላሳ ሲኮንድ በላይ አልቆየም ነበር። በረጅሙ የሚተነፍስ፤ ቁናቁና የሚተነፍስ፤ የሕብር ጉምጉምታ፤ የሴቶች ለቅሶ ተከትሎ በፍርድ ቤቱ ውስጥ ይሰማ ጀመር….
“LONG WALK TO FREEDOM” NELSON MANDELA (PAGE 432-438)
lkebede10@gmail.com

Monday, May 27, 2013

TPLF Devised of its Political Manifesto in 1976 to Commit Genocide against Amhara, by Gudu Kassa


Gudu Kassa

The  Tigrayan People's  Liberation Front(TPLF), fascist group had begun to realize their   anti  _ Amhara people labeling them as ethnic group    since 1976  and devised  their   manefesto in 1976  which they pressed "The TPLF manifesto_1968 ". The present Tigrayan Republic   demarcated based on "the 1968  TPLF manifesto" included Welqayitstegedy  and,Seatu Humera of Gondar and Raya ina Qubo of Wollo  .   They (TPLFs) have been working objectively to subjugate  the Amhara people  since 1976. Since then the master mind of TPLF proceeded their devised political agenda segregate Amhara people from the rest of Ethiopians .By devising such political ploy began   committing    genocide and/or ethnic cleansing  against the Amara people most of which are systematic  genocide against the Amhara people. It is imperative  to provide the following documented  credential  evidences about the TPLF committed genocide  against Amhara people since its history at  different time and place : Ever since TPLF took power and in the history of Ethiopia ,they have been targeting people of Amhara origin TPLF after they took power in 1991, they targeted  people of  Amhara and Amhara  origin all over Ethiopia  in their campaign of ethnic cleansing. Still at this movement, they have displacing, torturing  and brutally killing  Amharas any way they can and continuing to do so.The most notable tragic genocide committed by TPLF was  the Bedeno genocide ,where they threw men,women,and children of Amhara ethnic group down a shallow hole while alive. In Arusia, Arbagugu genocide committed in the same fashion they did in Bedeno in 1992,following this  as reported by DW radio ,the TPLF regime forcefully displaced over 20,000 Amharas from a place in Southern Ethiopia called Bench maji zone.
 A census in 2007 found major discrepancy in its reports,showed out of all ethnic groups  in Ethiopia ,the  Amhara ethnic group population revealed an anomaly. According to the census carried out by the TPLF,2.4 millions  Amharas disappeared. Nevertheless, Amhara ethnic group population anomaly  had been remained unjustified  by  the Central Statistics Authority(CSA). The Central Statistics Authority(CSA) official justification explained  in   probability of   the highest infant mortality rate  and  HIVAIDS death in the respective region(Amhara) can be the most likely reasons to the 2007 census discrepancy in the Amhara region.  The justification  to the census anomaly on Amhara ethnic group population confirm the TPLF systematic and targeted genocide  against  Amhara people.The North Gondarian  Amhara people displacement  and/ or replacement by Tigrayan (especially from an areas: Armacheh , Wolket tegeday and Seatetu Humera ( since Humara Sesame seed  variety is well known in the world  market). Such  calculated , targeted and forced  displacement and/or replacement of the Amhara people  from  their birth place and farm land so as  to benefit   Tigrayan  minority ethnic group . In  2012,as reported by Ethiopian Satellite Television (ESAT) and other medias outlets approximately more than   70,000 Amhara ethnic group forced displacement from  Gura ferda in SNNR  can be the most calculated and targeted against Amhara ethnic group to accomplish the 1976 TPLF manifesto of  ethnic cleansing.  There fore, we are too late to take counter action we have to be able to defined ourselves together with other victim  citizen of Ethiopians. TPLF ruled Ethiopia with hunger ,conflict and genocide as a means of repression and deception. Ethiopia as a result of TPLF come to power become landlocked  and paid millions of dollar for the port rent. The tyranny ethnio fascist TPLF junta   had also given away  land from Ethiopia which accounts 88,000km square( 1,600 km  length boarder length with 60 kms radius(distance to  inside) from south western Sudan boarder  to Sudan government   in lack of accountability to Ethiopian people. TPLF, Tigrayians minority recently in 2013 forced evacuation of 20,000 Amhara people from Benshangule Gumeze is out of the most notable  ethnic cleansing and genocide crime against the same ethnic group identified in its 1976 manifesto   . Finally I concluded that the TPLF junta used any  means under the sun to retain their power  and continuing ehinic cleansing and  genocide crime against Amhara people in particular and the the rest of Ethiopians ingeneral regardless the prevailing situation..
Ref.http://tassew.files.wordpress.com/2011/07/tplf_manifesto_-_1968_e-c.pdf